ar
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

الذهاب إلى القناة على Telegram

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

إظهار المزيد
2 755
المشتركون
-124 ساعات
+57 أيام
+4130 أيام
أرشيف المشاركات
አምስተኛ ዙር የተልዕኮ ትምህርት ምዝገባ ተጀመረ!! በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ በአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት
አምስተኛ ዙር የተልዕኮ ትምህርት         ምዝገባ ተጀመረ!!                    በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ በአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት  የጽርሐ ጽዮን  ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት አምስተኛ ዙር  የተልዕኮ ትምህርት       ለማስተማር ምዝገባ ጀምረናል ዘመኑን ያማከለ የትምህርት አሰጣጥን በመከተል በሥራ፣በትዳር፣ በጊዜ ማጣት፣ እንዲሁም በተለያዩ ምክንያቶች የቤተክርስቲያንን መሰረታዊ ትምህርቶች መማር ያልቻላችሁ ሃገር ውስጥም ከሃገር ውጭም ያላችሁ ምዕመናን እነሆ አምስተኛ ዙር ምዝገባ ተጀመረ "በጉብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ'' እንዲል መጽ.መክ.12፥1 በወር አንድ ቀን እሑድ ከጠዋቱ 3:30-6:30  በአካል በመገኘት በመማሪያ መጻሕፍት በመታገዝ ያለብዎትን የጊዜ እጥረት ታሳቢ  በማድረግ መሠረታዊ የቤተክርስቲያን ትምህርት እንዲማሩ ተጋብዘዋል!!! ምዝገባው  የጀመረው ሐምሌ 19 ሲሆን ነሐሴ 30 ያበቃል። እግዚአብሔር ቢፈቅድልን የመክፈቻ መርሐ ግብራችን  መስከረም 18/2018 ዓ.ም ይከናወናል            ለመመዝገብ ስም ስልክ አድራሻ በዚሁ ሊንክ በተከፈተው የቴሌግራም ግሩፕ👇 https://t.me/+MUgwPMxZscswYjBk በመጻፍ መመዝገብ ይቻላል እንዲሁም                 በ 0911458862                 በ 0978105980                 በ 0939115233                 በ 0991312409                 በ 0941530185 በመደወል መረጃ ማግኘት ይቻላል።

ደብረ  ታቦር ነሐሴ ዐሥራ ሦስት በዚች ቀን ክብር ይግባውና ከዘጠኙ የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታላቅና ዐበይት በዓላት አንዱ የሆነው የደብረ ታቦር በዓል ነው። መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሦስቱን ደቀ መዛሙርቶቹን ጴጥሮስን፣ ያዕቆብንና ዮሐንስን ይዞ ወደ ታቦር ተራራ ላይ አወጣቸው። መልኩም በፊታቸው ተለወጠ ልብሱም እንደ በረዶ ነጭ ሆነ። ስለ እነርሱም ጌታችን የሰው ልጅ በጌትነቱ ሲመጣ እስከሚያዩት ድረስ በዚህ ከቆሙት መካከል ሞትን የማይቀምሱት አሉ አለ። ሰዎች ሁሉ እርሱ ለሙሴ ጌታውና ከሞት ያስነሣው እንደሆነ ለኤልያስም ፈጣሪው እንደሆነና ካሳረገበትም ያወረደው እርሱ እንደሆነ ያውቁ ዘንድ እነሆ ከጌታ ከኢየሱስ ጋራ እየተነጋገሩ ሙሴና ኤልያስ ወደርሱ መጡ። ስለዚህም ጴጥሮስ ጌታችንን እንዲህ አለው አቤቱ በዚህ ትኖር ዘንድ ትወዳለህን ሦስት ሰቀላዎችንም አንድ ላንተ፣ አንድ ለሙሴ፣ አንድ ለኤልያስ እንሠራ ዘንድ። በዚህም ቃል የደካማነትና የትሕትና ምልክት አለበት። ደካማነት የተባለ ጴጥሮስ ጌታችን ከሰማይ የወረደበትን ሥራ ትቶ በተራራ ላይ ይኖር ዘንድና ራሱን የሚሠውርበትን ቤት ይሠራለት ዘንድ የተናገረው ነው። ትሕትና ያልነውም ጴጥሮስ ለራሱና ለባልንጀሮቹ ሐዋርያት ቤት ይሠራ ዘንድ ስለ አላሰበ ነው። ራሱንና ባልንጀሮቹ ሐዋርያትን እንደ ባሮች ነቢያትን ደግሞ እንደ ጌቶች አድርጎ አስቧልና። ስለ ሐዋርያትም የእውቀት ማነስ አታድንቅ በዚያን ጊዜ ፍጹማን አልሆኑምና። እንዲህም በሚልበት ጊዜ ጌታችን በሰው እጅ የተሠራ ማደሪያን የማይሻ መሆኑን ለጴጥሮስ ያሳየው ዘንድ እነሆ ደመና ጋረዳቸው። የጌታችንን ጌትነቱን የሚገልጽ በሐዋርያትም ልቡና እምነትን የሚያጸና እንዲህ የሚል ቃል ከደመና ውስጥ መጣ። ይህ የምወደው በእርሱ ደስ የሚለኝ ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት። ሙሴና ኤልያስም ከእርሱ ጋራ ሲነጋገሩ ተሰሙ ስለ እርሱ መምጣት የተናገሩትን ትንቢታቸውንም በቸርነቱ አረጋገጠ። ወደ ተራራ ላይ በመውጣቱም ነቢያትና ሐዋርያት ደስ አላቸው። ሁለተኛም የአብን ቃል በሰሙ ጊዜ ከእነርሱ ሥውር የነበረ የወልድ ዋሕድን በእውነት ሰው መሆን በዚያን ጊዜ ተረዱ ያን ጊዜ የጌትነቱ ክብር ተገልጦአልና። ሐዋርያትም ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው የሆነ እርሱ ሙሴን ከመቃብር ያስነሣው ኤልያስንም ያሳረገው አውርዶም ያመጣው እርሱ እንደሆነ አወቁ። ከእርሱ በቀር ማንም ማን የሙሴን መቃብር የሚያውቅ የለምና ከዐሳረገው ከእርሱ በቀር ማንም ማን ኤልያስ ያለበትን የሚያውቅ የለምና። በሰማይና በምድር ሥልጣን ካለው ከሁሉ ጌታ በቀር ሙታንን አድኖ ሊያስነሣቸው ማንም አይችልም። ደብረ ታቦርም የቤተ ክርስቲያን አምሳል ሆነች ከብሉይና ከሐዲስ በውስጧ ሰብስባለችና። የአብንም ቃል በሰሙ ጊዜ በግምባራቸው ፍግም ብለው በምድር ላይ ወደቁ እንደ ሙታንም ሆኑ። ከዓለም አስቀድሞ ከእርሱ ጋራ በህልውና እንዳለ ለልጁ አብ ምስክር ሆነ ወዲያውኑ ሙሴ ወደ መቃብሩ ኤልያስም ወደ ቦታው ተመለሱ። ሐዋርያትንም በአነቃቸው ጊዜ ከብቻው ጌታችን በቀር ማንንም አላገኙም። ከባሕርያችን የተዋሐደና ሥጋችንን የለበሰ ፍጹም አምላክ እንደሆነ በዚህ ሐዋርያት አስተማሩ። እንግዲህ እናስተውል ሰው ካልሆነ ቅዱስ ገብርኤል እመቤታችን ድንግል ማርያምን በአበሠራት ጊዜ እግዚአብሔር ከአንቺ ጋራ ነው እንዴት አላት። አምላክ ካልሆነስ ለመንግሥቱ ፍጻሜ የለውም እንዴት አላት። ሰው ካልሆነ በበረት እንዴት አስተኙት። አምላክስ ካልሆነ መላእክት ከሰማይ ወርደው ለእግዚአብሔር በሰማያት ምስጋና በምድርም ሰላም ለሰውም ግዕዛኑ ሊሰጠው እያሉ እንዴት አመሰገኑ። ሰው ካልሆነ ዮሐንስ በውኃ እንዴት አጠመቀው አምላክስ ካልሆነ አልዓዛርን ከመቃብር እንዴት ሊያስነሣው ቻለ። ይህ ተቀዳሚ ተከታይ የሌለው አንድ ልጅ አካላዊ ቃል እግዚአብሔር እርሱ ያለ መለወጥ ያለ መለየት አንድ አካል አንድ ባሕርይ በመሆን ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው እንደሆነ እናምንበታለን። እርሱም ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ ሁል ጊዜ አንድ ህላዌ ነው ዛሬም ዘወትርም ለዘላለሙ አሜን። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ሰላም ለከ መልአከ ኪዳኑ ወምክሩ፣ ለእግዚአብሔር ልዑል ዘግሩም ግብሩ፣ በረድኤትከ ረዋጺ ዘአሠረ ነፋስ አሠሩ፣ ሶበ ላዕሌየ እኩየ መከሩ ፣ ጉባኤ ፀርየ ሚካኤል ዝሩ። ሥራህ የሚደንቅ የልዑል እግዚአብ
ሰላም ለከ መልአከ ኪዳኑ ወምክሩ፣ ለእግዚአብሔር ልዑል ዘግሩም ግብሩ፣ በረድኤትከ ረዋጺ ዘአሠረ ነፋስ አሠሩ፣ ሶበ ላዕሌየ እኩየ መከሩ ፣ ጉባኤ ፀርየ ሚካኤል ዝሩ። ሥራህ የሚደንቅ የልዑል እግዚአብሔር የቃል ኪዳኑ ባለሟል ቅዱስ ሚካኤል ሆይ ሰላም እልሃለሁ። ጠላቶቼ ሤራቸውን በአሤሩ ጊዜ ከነፋስ ፍጥነት ይልቅ እጅግ በፈጠነ ረድኤትህ የጠላቶቼን ጉባኤ በትነው።

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። የሕጻናትና የማዕከላውያን ጉዞ ነሐሴ 25 /2017ዓ.ም እንደሚከናወን ይታወቃል ለዚህም ጉዞ የተመደበው ክፍያ 150 እስከ እሑድ ነሐሴ 11 ድረ
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። የሕጻናትና የማዕከላውያን ጉዞ ነሐሴ 25 /2017ዓ.ም እንደሚከናወን ይታወቃል ለዚህም ጉዞ የተመደበው ክፍያ 150 እስከ እሑድ ነሐሴ 11 ድረስ ብቻ ለከፈለ ሲሆን ከሰኞ ነሐሴ 12 ቀን ጀምሮ የሚከፍሉ 250 የሚደረግ ስለሆነ ያልከፈላችሁ አስቀድማችሁ ክፍያውን እንድትከፍሉ ይሁን። የጉዞ ኮሚቴ ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

''ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው'' ሐዋ.20፥35 የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት በጎ አድራጎት ክፍል በየዓመቱ በምዕመናን እገዛ ለተቸገሩ ሕጻናት የትምህርት መሣሪያ ድጋፍ ያደርጋል። እርስዎም የቻሉ
''ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው'' ሐዋ.20፥35 የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት በጎ አድራጎት ክፍል በየዓመቱ በምዕመናን እገዛ ለተቸገሩ ሕጻናት የትምህርት መሣሪያ ድጋፍ ያደርጋል። እርስዎም የቻሉትን የአቅምዎትን በመለገስ እንዲሳተፉ በትህትና እንጠይቃለን። ዝርዝራቸውም - 1 ደርዘን ደብተር--------800 - 1 ደርዘን እስክርቢቶ -----300 - 1 ደርዘን እርሳስ ---------150 - 1 ቦርሳ -------------------900 - 1 ኮምፓስ ----------------120 ጠቅላላ ፓኬጅ ---------2270 ብር በተናጠል መለገስ ይቻላል። 100065853292 ተስፋዬ፣ሙሉጌታ እና ሸዋንግዛው ለበለጠ መረጃ:- 09 13 00 60 86 - 09 12 41 97 72 - 09 31 14 44 44 ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

''ነገረ ክርስቶስ '' ክፍል ሁለት በዲ/ን ሞገስ አብርሃም የቅዳሜ የትምህርት መርሐግብር የፊታችን ቅዳሜ ነሐሴ 10/2017 ዓ.ም ከምሽቱ 11:45 ሰዓት ላይ ቀጠሮዎትን በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ
''ነገረ ክርስቶስ ''           ክፍል ሁለት                 በዲ/ን ሞገስ አብርሃም የቅዳሜ የትምህርት መርሐግብር  የፊታችን ቅዳሜ  ነሐሴ 10/2017 ዓ.ም ከምሽቱ  11:45 ሰዓት ላይ ቀጠሮዎትን በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ያድርጉ  ይምጡ ይማሩ በብዙ ያተርፋሉ እንዳይቀሩ። የቴሌግራም ቻናላችን https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com