ar
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

الذهاب إلى القناة على Telegram

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

إظهار المزيد
2 756
المشتركون
+124 ساعات
+17 أيام
+4230 أيام
أرشيف المشاركات
ወቅታዊ መልእክት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች  ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት !!    በቅድሚያ ብፁዕ ወቅዱስ አባታችን ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እንኳን ለ፳፻፲ወ፯ ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህናት  ምልዓተ ጉባኤ በሰላምና በጤና አደረሳችሁ። በመንፈስ ቅዱስ አጋዥነት ለቤተ ክርስቲያን ጠቃሚ የሆነ ውይይት እንድታከናውኑ የልጅነት ጸሎታችን ነው።   የቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህናት ምልዓተ ጉባኤ የሚወያይበትን አጀንዳ ተመልክተነዋል። የተያዘውም አጀንዳ  ጠቃሚ እንደሆነ ተረድተናል። ነገር ግን አሁን የቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ላይ የሚስተዋሉ ቁልፍ መፍትሔ የሚሹ ጉዳዮች ለውይይት ቀርበዋል ብለን አናምንም። ምክንያቱም ከአጥቢያ እስከ መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ድረስ የሚስተዋሉ፤ በቅዱስ ሲኖዶስ በቁርጠኝነት ዘላቂ መፍትሔ ሊበጅላቸው የሚገቡ ዘርፈ ብዙ አስተዳደራዊ እና ተያያዥ ጉዳዮች ለውይይት ሳይቀርቡ ታልፈዋል። በመሆኑም በሀገር አቀፍ ደረጃ ተለይተው፣ በማስረጃ ዳብረው እና  በመጨረሻም ግንቦት ፮ ቀን ፳፻፲ወ፯ ዓ.ም የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ከበርካታ አህጉረ ስብከት ከተውጣጡ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት አመራር አባላት እና ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ከተውጣጡ የክፍለ ከተማ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አመራሮች፣ የገዳማት እና አድባራት ሰንበት ት/ቤት ሊቃነ መናብርት ጋር በአካልና በቴክኖሎጂ በመታገዝ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።  በመሆኑም በአካልና በቴክኖሎጂ በአመራሮች ውይይት  የተደረገባቸው፤ የጋራ አቋም የተያዘባቸው እንዲሁም በቀጥታ የኦርቶዶክሳዊያን ምእመናንና ምእመናት ጥያቄም ጭምር የሆኑትን፤ እኛ  የነገይቱ ቤተ ክርስቲያን ተረካቢ ወጣቶች በልጅነት አንደበት እንደሚከተለው ለማቅረብ እንወዳለን ። እነርሱም፦ 1. የቤተ ክርስቲያንን ሲኖዶሳዊ ልዕልና እና አንድነትን ማስጠበቅ ፤ ሀ. ታላቂቱ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ከትናንቱ ይልቅ ዛሬ ተቋማዊ ህልውናዋ እና ልዕልናዋ አስጊ ደረጃ ላይ የሚገኝ በመሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስ ሕገ ቤተ ክርስቲያን እና መዋቅራዊ አሠራርን በመፈተሽ እና በማስጠበቅ የቤተ ክርስቲያንን ሁለንተናዊ ፈተና በፍጥነት ሊያስቆም ይገባል፡፡ ለ. በነገረ ሃይማኖት ላይ እየተሰነዘሩ ያሉ ሐሰተኛ ትምህርቶች ቤተ ክርስቲያን የጠራ ትምህርቷን በተገቢው ሁኔታ፣ በሚገባው ዐውድ እና በሚመለከተው አካል ምላሽ እንዲሰጥባቸው፤ ሐ. ሐሰተኛ ትምህርት ያስተላለፉ ከመምህራን እስከ ሊቃነ ጳጳሳት ያሉ አካላት ላይ ተገቢው ቀኖናዊ ሥራ እንዲሠራ፤ መ. እየተድበሰበሰ ያለው የነገረ ቅብዓት ጉዳይ የማያዳግም እልባት ሊሰጠው ይገባል። ሠ. በትግራይ ክልል የሚገኙ ኦርቶዶክሳዊያን ነፍስ ጉዳይ በእጅጉ ያሳስበናል። በክልሉ ከሚገኙ አህጉረ ስብከት  አስተዳደራዊ ግንኙነት መቋረጥ እና እስከ አሁንም ይኽ ችግር ተገቢ የኾነ መፍትሔ ባለማግኘቱ፤ መለያየቱ ሥር ሰዶ፤ የጥፋቱ ጉዳት እየጨመረ እና የቤተ ክርስቲያኒቱን አንድነት ለማይፈልጉ አካላት ሰርግና ምላሽ ሆኖ ነፍሳት በኑፋቄ እየተነጠቁ ይገኛሉ። ከተፈጠረው የአስተዳድር ልዩነት በኋላ የተስተዋሉ የኑፋቄ እና ስልታዊ ጥፋትን አስመልክቶ ያዘጋጀነውን ዝርዝር የማስረጃ ሰነድ ለቋሚ ሲኖዶስና ለቅዱስ ፓትርያርኩ ብናቀርብም ተጨባጭ ምላሽ አልተሰጠም። በመሆኑም በትግራይ ያለ ኦርቶዶክሳዊ ምእመን በሚያስደነግጥ ፍጥነት በኑፋቄ እየተነጠቀ መሆኑን በመረዳት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት አስቸኳይ መፍትሔ ካልተሰጠው በፈጣሪ ፊት፣ በኅሊና እና በታሪክ ያስጠይቃል። አደገኛ ሰብራትም የሚያስከትል በመሆኑ አፋጣኝ መፍትሔ እንዲሠጥበት፤ ረ. በኦሮሚያ ክልል በሚገኙ አህጉረ ስብከት ወቅታዊ ችግር፣ ሌሎች የከረሙ አስተዳደራዊ ችግሮች እና ተያያዥ ምክንያቶች አብያተ ክርስቲያናት እየተዘጉ አገልጋይ ካህናት እና ተከታይ ምእመናን ወደ ሌላ እየፈለሱ እና እየተሰደዱ መሆናቸው የሚታይ የአደባባይ ሐቅ ነው። ይኸንኑ ችግር በጥናት ላይ ተመሥርቶ ከመመለስ ይልቅ ጳጳስ በመሾም ጥያቄዎቹ እንደተመለሱ የመቁጠር ከፍተኛ ዝንባሌ ተስተውሏል። በእርግጥ እርሱም ውጤታማ አይደለም። ችግሩን ከሥሩ ተረድቶ ምላሽ ባለመሰጠቱ የክልሉን ኦርቶዶክሳዊ በሌላ ዐውቅልሀለው ባይ አካል እንዲናወጽ ሆኗል:: በቅዱስ ሲኖዶሱም ለቋንቋዎች አገልግሎት የተመደበው በጀት እዚህ ግባ የሚባል ሥራ ሲሠራበት አልታየም። በአጠቃላይ በክልሉ የሚገኘውን የቤተ ክርስቲያኒቱን አገልግሎት በማጠናከር የሚፈለገውን ውጤት ለማምጣት የካህናት ማሠልጠኛ ማዕከላትን ማስፋፋት፣ መምህራንና አገልጋዮችን በማፍራት ተደራሽነትን የማስፋት ተጨባጭ ሥራ መሥራት ይገባል። 2. የቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊ ችግሮችን (ለጥፋት የዳረገንን ብልሹ አሠራርን) በተመለከተ፦ የሰበካ መንፈሳዊ ሥራ አስፈጻሚ ፣ ጠቅላላ ጉባኤ እና ከመንፈሳዊ ዘርፍ ውጪ ያሉ አስተዳደራዊ ጉዳዮች በቃለ ዐዋዲው እና  በተገቢው የዘርፉ ባለሙያ እንዲመሩ አለማድረግ ለጥፋት እና ለብልሹ አሠራር ዳርጎናል። ታላቂቱን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ከማይመጥን እና ብዙ ዋጋ ካስከፈላት አስተዳደራዊ ድክመት በመላቀቅ እና ዘመኑን በመዋጀት  እናት ቤተ ክርስቲያንን  መታደግ ለነገ የማያድር ሥራ ነው ። በመሆኑም :- ሀ. የቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ አገልግሎት ተደራሽ እንዳይሆን፣ የምእመናን ነፍስ እንዲነጠቅ፣  የኢኮኖሚ አስተዋጽዖዋ እንዲደበዝዝ ፣ ተሰሚነቷና ተቀባይነቷ ጥያቄ ውስጥ እንዲገባ ምክንያት የሆነው በብቁ የአስተዳደር ባለሙያ የመፈጸም ችግር የገነገነ ነው። መንፈሳዊ ዕውቅት ብቻ ባላቸው ነገር ግን የአስተዳደር ክህሎት በሌላቸው፣ ዘመኑን የመዋጀት ክፍተት ባለባቸው ሊቃነ ጳጳሳት እና በዘመድ አዝማድ ደጅ ጥናት ሙያ ሳይኖራቸው በተመደቡ ሓላፊዎች መመራቱ ዋናው የችግሩ አካል ስለሆነ የጠቅላይ ቤተ ክህነት  ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅነት፣ የአህጉረ ስብከት ጽ/ቤቶች  የአስተዳደር ዘርፍ ከሊቃነ ጳጳሳት ውጪ በብቁ ባለሙያዎች እንዲመሩ እና ሊቃነ ጳጳሳት በሕግ አውጪነት እና ቤተ ክርስቲያንን በመጠበቅ ፤ ቤተ ክርስቲያንን እንዲመሩ፤ሕገ ቤተ ክርስቲያን ላይ ማሻሻያ  ማድረግ ይገባል :: ለ. በሕገ ቤተ ክርስቲያን እና በቃለ ዐዋዲ የተደነገገው የሰበካ ጉባኤ የአስፈጻሚነት እና የሰበካ መንፈሳዊ ጠቅላላ ጉባኤያት ሚና መገሰስ ፦ በቃለ ዐዋዲው የተደነገገው የካህናት፣ የምእመናን እና የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች የአስፈጻሚነት ተሳትፎ ማለትም በወረዳ ቤተ ክህነት፣ በሀገረ ስብከት መንበረ ጵጵስና እና በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ተግባራዊ እንዳይደረግ ተገፍቷል። በዚህም ምክንያት የክፍል እና የመምሪያ ሓላፊዎች  በቤተ ክርስቲያን ሕግ በግልጽ ከተደነገገው ከሦስቱ አካላት ተዋጽዖ ውጪ በሕግ  የማይታወቅ  የመደበኛ ቅጥር ሠራተኞች ስብስብ " የአስተዳደር ጉባኤ " የሚባል መሥርተው ቤተ ክርስቲያኒቱን እየበደሉ ይገኛሉ።  ካህናት፣ ምእመናን ፣ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች የአስፈፃሚነት ሚናቸውን እንዲወጡ በሕገ ወጥ  ስብስብ የተነጠቀው የአስፈጻሚነት ድርሻ በየመዋቅሩ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ተመልሶ ተግባራዊ ሊደረግ ይገባል ።

" የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ለተፈጠሩት ችግሮች መፍትሔ በመስጠት ሐዋርያዊ አደራውን እንዲወጣ በልጅነት መንፈስ ዝቅ ብለን እንማፀናለን! " የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ግንቦት 6 ቀን 2017 ዓ.ም በተደረገ ስብሰባ የዘንድሮ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በርካታ ሥር ነቀል ለውጦችን ማምጣት የሚችል ፤ ለነገይቱ የቤተክርስቲያን ተረካቢ ወጣቶች መሰረት የጣለ እንዲሆን ያለመ ምክረ ሐሳብ ተወያይቶ ማቅረቡን አስታውቋል። ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ቀርበው መፍትሔ እንዲሰጥባቸው ከቀረቡት ውስጥ ፦ የቤተክርስቲያንን ሲኖዶሳዊ ልዕልና እና አንድነትን ማስጠበቅ ፣ የቤተክርስቲያንን አስተዳደራዊ ችግሮችን በመለየት መፍታት ፣ የሥነ ምግባር ግድፈት እና የቀኖና ጥሰት መበራከት ፣ በሀገራዊና ዓለም አቀፍ ጉዳይ ላይ የሚኖሩ ተሳትፎዎች ዋና ዋና ጉዳዮች ስለመሆናቸው በመልእክቱ ተላልፏል። ሐሰተኛ የሆኑ የኑፋቄ ትምህርቶች ፣ በሰላም እጦት የሚገኙ አህጉረ ስብከቶች ፣ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ሚና ፣የሀብት ብክነት ፣ ዘመኑን የዋጀ የአሠራር መንገድ መዘርጋት ፣ መንፈሳዊ አገልግሎት ላይ የሚስተዋሉ እና አፈንግጠው የወጡ ሥርዓቶች ፣ በከተማ ልማት መስፋፋት የምእመናን ከአምልኮ ሥፍራ መራቅ ፣ ሀገራዊ የችግር አፈታት መንገዶች ላይ ምልዓተ ጉባኤውም በስፋት እንዲወያይ አንድነቱ በዝርዝር ካስቀመጣቸው ሐሳቦች መሐል ይገኙበታል። እነዚህን እና ሌሎች የውይይት ሐሳቦችን በዝርዝር በማቅረብ " የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ መፍትሔ በመስጠት ሐዋርያዊ አደራውን እንዲወጣ በልጅነት መንፈስ ዝቅ ብለን እንማፀናለን! " በማለት አንድነቱ መልእክቱን አጋርቷል። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

በሰንበት ትምህርት ቤታችን ማዕከላውያን ክፍል የተዘጋጀው ዝክረ ቅዱስ ያሬድ ዓውደ ርዕይ መርሐ ግብር በዛሬው እለት ተከናወነ። እንኳን ለአባታችን ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ዓመታዊ ክብረ በዓል ዋዜማ በሰላም
+9
በሰንበት ትምህርት ቤታችን ማዕከላውያን ክፍል የተዘጋጀው ዝክረ ቅዱስ ያሬድ ዓውደ ርዕይ መርሐ ግብር  በዛሬው እለት ተከናወነ። እንኳን ለአባታችን ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ዓመታዊ ክብረ በዓል ዋዜማ በሰላም አደረሳችሁ። እንደዚሁም ነገ ግንቦት 10 እና 11 ከምሽቱ 11:00 ጀምሮ በደብራችን ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ አውደ ምሕረት ልዩ የዝማሬ እና የምስጋና መርሐ ግብር ተዘጋጅቷል እና እንዳይቀሩ ጥሪያችንን በአምላከ ቅዱስ ያሬድ ስም እናስተላልፋለን።    በረከተ ቅዱስ ያሬድ በሁላችንም ላይ ይደር። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ዓለም ከሚያውቃቸው የዜማ ደራሲያን አስቀድሞ ቅዱስ ያሬድ ግእዝ፣ ዕዝልና ዓራራይ በተሰኙ የዜማ ስልቶች የማይሰለችና ዘመን ተሻጋሪ ዜማን፣ የዜማ ምልክቶችንና የተለያዩ ድርሰቶችን በመድረስ ሃገራችን የ
ዓለም ከሚያውቃቸው የዜማ ደራሲያን  አስቀድሞ ቅዱስ ያሬድ ግእዝ፣ ዕዝልና ዓራራይ በተሰኙ የዜማ ስልቶች የማይሰለችና ዘመን ተሻጋሪ ዜማን፣ የዜማ ምልክቶችንና የተለያዩ ድርሰቶችን በመድረስ ሃገራችን የዚህ ታላቅ መንፈሳዊ ሀብት ባለቤት እንድትሆን አድርጓል፡፡ ቅዱስ ያሬድ ዛሬ በጉባኤ ቤት ለዜማ ትምህርት ቤተክርስቲያን የምትገለገልበትን ሥርዓተ ትምህርትና የመማሪያ መጻሕፍትን የደረሰ ታላቅ ሊቅ ነው፡፡ የዚህን ታላቅ ሊቅ ስራዎች ድርሰቶች ግንቦት 09 እና 10  በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ስብከተ ወንጌል አዳራሽ በመገኘት የመርሐ ግብሩ ተሳታፊ ይሁኑ። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናላችን https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ዓለም ከሚያውቃቸው የዜማ ደራሲያን አስቀድሞ ቅዱስ ያሬድ ግእዝ፣ ዕዝልና ዓራራይ በተሰኙ የዜማ ስልቶች የማይሰለችና ዘመን ተሻጋሪ ዜማን፣ የዜማ ምልክቶችንና የተለያዩ ድርሰቶችን በመድረስ ሃገራችን የ
ዓለም ከሚያውቃቸው የዜማ ደራሲያን አስቀድሞ ቅዱስ ያሬድ ግእዝ፣ ዕዝልና ዓራራይ በተሰኙ የዜማ ስልቶች የማይሰለችና ዘመን ተሻጋሪ ዜማን፣ የዜማ ምልክቶችንና የተለያዩ ድርሰቶችን በመድረስ ሃገራችን የዚህ ታላቅ መንፈሳዊ ሀብት ባለቤት እንድትሆን አድርጓል፡፡ ቅዱስ ያሬድ ዛሬ በጉባኤ ቤት ለዜማ ትምህርት ቤተክርስቲያን የምትገለገልበትን ሥርዓተ ትምህርትና የመማሪያ መጻሕፍትን የደረሰ ታላቅ ሊቅ ነው፡፡ የዚህን ታላቅ ሊቅ ስራዎች ድርሰቶች ግንቦት 09 እና 10  በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ስብከተ ወንጌል አዳራሽ በመገኘት የመርሐ ግብሩ ተሳታፊ ይሁኑ።

''ዕቅበተ እምነት'' ክፍል ሁለት በመ/ር ዲ/ን ዳንኤል ታደለ የቅዳሜ የትምህርት መርሐግብር የፊታችን ቅዳሜ ግንቦት 09/2017 ዓ.ም ከምሽቱ 11:45 ሰዓት ላይ ቀጠሮዎትን በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ
''ዕቅበተ እምነት''                   ክፍል ሁለት    በመ/ር ዲ/ን ዳንኤል ታደለ የቅዳሜ የትምህርት መርሐግብር  የፊታችን ቅዳሜ ግንቦት 09/2017 ዓ.ም ከምሽቱ  11:45 ሰዓት ላይ ቀጠሮዎትን በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ያድርጉ  ይምጡ ይማሩ በብዙ ያተርፋሉ እንዳይቀሩ። የቴሌግራም ቻናላችን https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

++++ሰማያዊው ዜማ++++ ''ዝክረ ቅዱስ ያሬድ'' ልዩ የምስጋና እና የዝማሬ መርሐግብር ግንቦት 10 እና 11 በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ከ11:00 ጀምሮ በደብራችን አውደ ምሕረት የፍኖተ ብር
++++ሰማያዊው ዜማ++++            ''ዝክረ ቅዱስ ያሬድ'' ልዩ የምስጋና እና የዝማሬ መርሐግብር ግንቦት 10 እና 11 በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ከ11:00 ጀምሮ በደብራችን አውደ ምሕረት          የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ሰማያዊው ዜማ ''ዝክረ ቅዱስ ያሬድ'' ልዩ የምስጋና እና የዝማሬ መርሐግብር ግንቦት 10 እና 11 በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ከ11:00 ጀምሮ በደብራችን አውደ ምሕረት የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤ
ሰማያዊው ዜማ            ''ዝክረ ቅዱስ ያሬድ'' ልዩ የምስጋና እና የዝማሬ መርሐግብር ግንቦት 10 እና 11 በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ከ11:00 ጀምሮ በደብራችን አውደ ምሕረት          የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

በትላንትናው እለት ቅዱስ ሲኖዶስ የሚወያይባቸውን ፳፬ አጀንዳዎችን መርምሮ አጸደቀ። የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ምልዓተ ጉባኤ  የግንቦት ፮ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም ውሎን አስመልክቶ መጋቤ ሃይማኖት አባ አብርሃም የቅዱስ ሲኖዶስ ምክትል ጸሐፊና የሰሜን አፍሪካ ሀገረ ስብክት ሥራ አስኪያጅ  ማምሻውን ማብራሪያ ሰጥቷል። በማብራሪያቸው ላይ  ምልዓተ ጉባኤው ሰባት አባላት ያሉት የአጀንዳ አርቃቂ ኮሚቴ መሰየሙ  አስታውሰው  በቋሚ ሲኖዶስ ተዘጋጅቶ የቀረበውን አጀንዳ በመመርመርና በማሻሻል ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በማቅረብ 24 አጀንዳዎችን ጉባኤው አጽድቆ ወደ ውይይት ገብቷል ብለዋል። በዚህም በዛሬው የጉባኤው ውሎ አጀንዳ 1. ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ያስተላለፉትን መልእክት በማጽደቅ የሥራ መመሪያ ሆኖ እንዲያገለግል ወስኗል። አጀንዳ 2. የቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤትን ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትን ከግንቦት ፳፻፲፮ እስከ ግንቦት ፳፻፲፯ ዓ.ም በቋሚ ሲኖዶስና በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የተወሰኑ ውሳኔዎችን በተመለከተ የአፈጻጸም ሪፖርት በመጋቤ ብርሃናት አባ ተክለ ያሬድ ተክለ ጎርጎርዮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ምክትል ጸሐፊ በንባብ ተደምጦ ጉባኤውም ያለውን ሪፖርት አዳምጦ አጽድቋል፡፡ "በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ።”   ሐዋርያት ፳፥፳፰ ©የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

በትላንታው እለት ቅዱስ ሲኖዶስ የሚወያይባቸውን ፳፬ አጀንዳዎችን መርምሮ አጸደቀ። የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ምልዓተ ጉባኤ የግንቦት ፮ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም ውሎን አስመልክቶ መጋቤ ሃይማኖት አባ አብርሃም የቅዱስ ሲኖዶስ ምክትል ጸሐፊና የሰሜን አፍሪካ ሀገረ ስብክት ሥራ አስኪያጅ  ማምሻውን ማብራሪያ ሰጥቷል። በማብራሪያቸው ላይ  ምልዓተ ጉባኤው ሰባት አባላት ያሉት የአጀንዳ አርቃቂ ኮሚቴ መሰየሙ  አስታውሰው  በቋሚ ሲኖዶስ ተዘጋጅቶ የቀረበውን አጀንዳ በመመርመርና በማሻሻል ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በማቅረብ 24 አጀንዳዎችን ጉባኤው አጽድቆ ወደ ውይይት ገብቷል ብለዋል። በዚህም በዛሬው የጉባኤው ውሎ አጀንዳ 1. ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ያስተላለፉትን መልእክት በማጽደቅ የሥራ መመሪያ ሆኖ እንዲያገለግል ወስኗል። አጀንዳ 2. የቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤትን ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትን ከግንቦት ፳፻፲፮ እስከ ግንቦት ፳፻፲፯ ዓ.ም በቋሚ ሲኖዶስና በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የተወሰኑ ውሳኔዎችን በተመለከተ የአፈጻጸም ሪፖርት በመጋቤ ብርሃናት አባ ተክለ ያሬድ ተክለ ጎርጎርዮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ምክትል ጸሐፊ በንባብ ተደምጦ ጉባኤውም ያለውን ሪፖርት አዳምጦ አጽድቋል፡፡ "በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ።”   ሐዋርያት ፳፥፳፰ ©የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ሰባት አባላት ያሉት የአጀንዳ አርቃቂ ኮሚቴን ሰየመ ግንቦት ፮/፳፻፲፯ ዓ.ም ለ፳፻ ፲ወ፯ ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህናት ጉባኤ አጀንዳ በማርቀቅ እንዲያቀርቡ ሰባት ሊቃነ ጳጳሳትን የሰየመ ሲሆን ኮሚቴው በቋሚ ሲኖዶስ ተዘጋጅቶ የቀረበውን አጀንዳ በመመርመርና በማሻሻል ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በማቅረብ የሚያጸድቅ ይሆናል። የኮሚቴው አባላትም፦ ፩.አቡነ ጎርጎርዮስ ፪.አቡነ ቀሌምንጦስ ፫.አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ፬.አቡነ ኤልያስ (አርባ ምንጭ) ፭.አቡነ ሩፋኤል ፮.አቡነ ዜና ማርቆስ ፯.አቡነ ኤልሳዕ ሲሆኑ ምልአተ ጉባኤው  ከአጀንዳዎቹ መጽደቅ በኋላ የቅዱስ ፓትርያርኩን የመግቢያ መልእክትና የቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤትን ሪፖርት ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል። ምንጭ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ሰባት አባላት ያሉት የአጀንዳ አርቃቂ ኮሚቴን ሰየመ ግንቦት ፮/፳፻፲፯ ዓ.ም ለ፳፻ ፲ወ፯ ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህናት ጉባኤ አጀንዳ በማርቀቅ እንዲያቀርቡ ሰባት ሊቃነ ጳጳሳትን የሰየመ ሲሆን ኮሚቴው በቋሚ ሲኖዶስ ተዘጋጅቶ የቀረበውን አጀንዳ በመመርመርና በማሻሻል ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በማቅረብ የሚያጸድቅ ይሆናል። የኮሚቴው አባላትም፦ ፩.አቡነ ጎርጎርዮስ ፪.አቡነ ቀሌምንጦስ ፫.አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ፬.አቡነ ኤልያስ (አርባ ምንጭ) ፭.አቡነ ሩፋኤል ፮.አቡነ ዜና ማርቆስ ፯.አቡነ ኤልሳዕ ሲሆኑ ምልአተ ጉባኤው  ከአጀንዳዎቹ መጽደቅ በኋላ የቅዱስ ፓትርያርኩን የመግቢያ መልእክትና የቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤትን ሪፖርት ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል። ምንጭ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ሰማያዊው ዜማ ''ዝክረ ቅዱስ ያሬድ'' ልዩ የምስጋና እና የዝማሬ መርሐግብር ግንቦት 10 እና 11 በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ከ11:00 ጀምሮ በደብራችን አውደ ምሕረት የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤ
ሰማያዊው ዜማ            ''ዝክረ ቅዱስ ያሬድ'' ልዩ የምስጋና እና የዝማሬ መርሐግብር ግንቦት 10 እና 11 በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ከ11:00 ጀምሮ በደብራችን አውደ ምሕረት          የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com