ዲያቆን ሚካኤል እሸቱ
الذهاب إلى القناة على Telegram
ይህ የዲያቆን ሚካኤል እሸቱ ይፋዊ ገጽ ነው። ለጥያቄዎችና ለአስተያየት @Dnmichael12
إظهار المزيد1 756
المشتركون
-124 ساعات
+137 أيام
+4730 أيام
أرشيف المشاركات
1 756
“ለሰው ሁሉ ከሚሆነው በቀር ምንም ፈተና አልደረሰባችሁም፤ ነገር ግን ከሚቻላችሁ መጠን ይልቅ ትፈተኑ ዘንድ የማይፈቅድ እግዚአብሔር የታመነ ነው፥ ትታገሡም ዘንድ እንድትችሉ ከፈተናው ጋር መውጫውን ደግሞ ያደርግላችኋል”1ኛ ቆሮ. 10:13
1 756
“ለሰው ሁሉ ከሚሆነው በቀር ምንም ፈተና አልደረሰባችሁም፤ ነገር ግን ከሚቻላችሁ መጠን ይልቅ ትፈተኑ ዘንድ የማይፈቅድ እግዚአብሔር የታመነ ነው፥ ትታገሡም ዘንድ እንድትችሉ ከፈተናው ጋር መውጫውን ደግሞ ያደርግላችኋል” ይላል መጽሐፍ:: 1ኛ ቆሮ. 10:13
1 756
የምናሴ ጸሎት (፪ ዜና መዋዕል ፴፫ ፥ ፲፬-፳፮)
ዓለምን ሁሉ የምትገዛ ፥ የአባቶቻችን የአብርሃምና የይስሐቅ የያዕቆብም የጻድቃን ልጆቻቸውም አምላክ ሆይ ፥ ሰማይንና ምድርን ከዓለሞቻቸው ጋር የፈጠርህ ፥ በቃልህ ትእዛዝ ባሕርን የገሠጽሃት ፥ ቀላዮችን የዘጋህ የሚያስፈራውንም የወሰንህ ፥ ይኸውም በተመሰገነው ስምህ ነው ፥ ኀይልህ ከመገለጡ የተነሣ ሁሉ የሚርድና የሚንቀጠቀጥ ፥ ለክብርህ ከፍተኛነት ፍጻሜ የለውምና ፥ የቁጣህም መቅሰፍት በኃጥአን ላይ ግሩም ነው። በትእዛዝህ ለሚሆነው ይቅርታ ስፍር ቍጥር የለውም ፤ ገናና እግዚአብሔር አንተ ብቻ ነህና ፥ ይቅር ባይ ፥ ከቁጣ የራቅህ ፥ ይቅርታህ የበዛ ፥ የሰውንም ኅጢአት የምታስተሰርይ አንተ ነህ። አሁንም አቤቱ ፥ የጻድቃን አምላካቸው አንተ ነህ። ንስሓን የፈጠርህ ለጻድቅ ሰው አይደለምና ፥ አንተን ላልበደሉ ለአብርሃምና ለይስሐቅ ለያዕቆብም አይደለምና ፤ ነገር ግን የኔን የኃጥኡን ንስሓ ወደ ማየት ተመለስ። ቍጥሩ ከባሕር አሸዋ የሚበልጥ በደልን በድያለሁና ፥ ኀጢአቴም ብዙ ነውና ፤
ከበደሌም ብዛት የተነሣ ቀና ብዬ የሰማይን ርዝመት አይ ዘንድ አገባቤ አይደለም። ሰውነቴን ከኀጢአቴ አሳርፋት ዘንድ በብረት ቀፎ ደከምሁ ፤ በዚህም ደግሞ አላረፍሁም ፤ መዓትህን አነሣሥቻለሁና ፥
ከንቱውን ስመለከት የማይጠቅመኝንም ነገር ሳበዛ በፊትህ ክፉ ሥራን ሠርቻለሁና። አሁንም ቸርነትህን እየለመንሁ በልቤ ጉልበት እሰግዳለሁ። አቤቱ ፥ ጌታዬ ፥ ፈጽሜ በደልሁ ፤ ኀጢአቴንም አምናለሁ። አንተንም እማልዳለሁ ፤ እለምንህማለሁ ፤ ይቅር በለኝ ፤ አቤቱ ፥ ይቅር በለኝ ፤ ለኀጢአቴም አሳልፈህ አትስጠኝ። ለዘለዓለም ክፋቴን አትመልከትብኝ ፤ በምድር ጥልቀት አትበቀለኝ ፤
አቤቱ ፥ በንስሓ ለሚመለሱ ሰዎች ፥ አምላካቸው አንተ ነህና ፥ ቸርነትህ በኔ ላይ ይገለጥ ፤
መዳን የማይገባኝ ሲሆን በይቅርታህ ብዛት አዳንኸኝ። በየጊዜውና በሕይወቴ ዘመን ሁሉ አመሰግንሃለሁ። የሰማያት ኀይል ሁሉ አንተን ያመሰግናሉና ፤ ለዘለዓለምም ምስጋና ለአንተ ይገባል ፤ አሜን።
1 756
Repost from Dn Abel Kassahun Mekuria
የቤተ ክርስቲያን ትምህርት እና ሥርዓት እንዴት አሁን ያለበትን ዓይነት ቅርጽ ሊይዝ ቻለ? በዚህ ሂደት ውስጥስ በቤተ ክርስቲያን የተካሄዱ ዓለማቀፉዊ ጉባኤያት (Ecumenical Councils) ድርሻቸው ምን ነበር?
ይህን አጠር ባለ መንገድ ለመረዳት “ጉባኤ ኒቅያ” የተሰኘውን ሦስት ክፍሎች ያሉትን ተከታታይ ትምህርት ከማስታወሻ ጋር እንድትመለከቱ እጋብዛለሁ።
https://youtu.be/Epd_EC5diLI?si=JlViJ7yVxsPkpyHA
1 756
የመንገድህ ዋስትና እኔ ነኝ ። በበረሃ ልጥልህ ከቤት አላወጣሁህም ። ስጸዳ እመጣለሁ ብለህ ከቤቴ አትራቅ ። ካልሞትህ በቀር ከቤቴ አትቅር ። ጥያቄዎችህን ሳይሆን እኔን አስብ ። የሁሉም ነገር መልስ በዓለም ላይ የለም ። የሁሉም ነገር መልስ ግን እኔ ነኝ ። አንድ ቃል ልንገርህ፡- ዋጋ ያለህ ፍጥረቴ ነህ ።
1 756
Repost from N/a
1 756
Repost from የአእላፋት ዝማሬ | Melody of Myriads
+4
በኢጃት ጃን አግናጥዮስ የሚዘጋጀው ጉባኤ
አግናጥዮስ የአዳጊ ልጆች የክረምት ትምህርት ላይ ለመሳተፍ ከስር የተቀመጠውን ቅጽ በመሙላት መመዝገብ ትችላላችሁ።
https://forms.gle/AdLs7RHSqPhVvfjD9
1 756
የተዘጋውን የገነት በር በደሙ የከፈተ ፣ ወንበዴን ይቅር ብሎ የመጀመሪያ ተጋባዥ ያደረገ ፣ ለምሕረቱ ልክ ፣ ለይቅርታው ወሰን የሌለው ዛሬ የምንሰብከው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ።
1 756
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
ተማሪዎች ውጤታቸው መመልከት ይችላሉ።
በ2018 የትምህርት ዘመን በ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና 95.85% ተማሪዎች 50 እና ከዛ በላይ ውጤት ማስመዝገባቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።
የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤትን ይፋ ተደርጓል።
ተማሪዎች ውጤታቸውን ይህንን ማስፈንጠሪያ https://aa.ministry.et/#/result በመጫን መመልከት ይችላሉ።
ሰኔ 22 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
1 756
ሴቶች “ሱሪ” መልበስ ይችላሉ?
ቀሲስ ኅብረት የሺጥላን የምታውቋቸው ሁሉ ትወዷቸዋላችሁ ብዬ አስባለሁ። በርግጥ እሳቸውን አለመውድድ አይቻልም። በስብከተ ወንጌል የደከሙ በድካማቸው ልክ ያልታወቁ ብርቱ ዐርአያ ካህን ናቸው። እና ከዚህ በታች ያለው ጽሑፍ የርሳቸው ነው። አኬ በቅርቡ የተናገረውን ነገር የዛሬ 20 ዓመት ገደማ (1997) እንዲህ ብለው ጽፈውት ነበር ፦
"በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስለ ወንድና ስለ ሴት አለባበስ ብዙ መግለጫዎች አሉ ። ለምሳሌ ከወንዶች አልባሳት ተርታ ከተጠቀሱት ውስጥ መታጠቂያ፣ መደረቢያ፣ መጎናጸፊያ፣ ስናፊል፣ ቀሚስ፣ እጀ ጠባብ ካባና ድግ ይገኙበታል፡፡ ፩ሳሙ ፲፰÷፬፣ ፪÷፲፱፤ ዳን. ፫÷፳፩፤ ምሳ. ፴፩÷፳፬፤ ዮሐ. ፲፱፥፳፫፧ ኢያ. ፯፥፳፩ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ከተጠቀሱት የሴቶች አልባሳት መካከል ደግሞ የሚከተሉት ይገኙበታል፡፡ እነርሱም፡- ልግም በገላ፣ መታጠቂያ፣ መጎናጸፊያ፣ ራስ ማሠሪያ፣ ቀጸላና ዓይነ ርግብ ናቸው፡፡ ኢሳ. ፫÷፳-፳፬
“ሱሪ” ግን በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ለወንዶች ይልቁንም ለካህናት ብቻ ተጠቀሶ እናገኛለን፡፡ ዘጸ. ፴፱÷፳፱ ያም ቢሆን በተለይ በሀገራችን አብዛኛው ማኅበረ ሰብእ “ሱሪ”ን ያለ አንዳች ተደራቢ ነገር መልበስ የወንዶች መደበኛ አለባበስ አድርጎ መቀበሉን ማረጋገጫ አያስፈልገውም፡፡ ስለዚህ ተገቢ ያልሆነን አለባበስ መርምሮ እንኳን “ሱሪ” ይቅርና ቀሚስም ቢሆን አለመልበስ ለሴቶች የተገባ ነው፡፡ ወንዶችም ቢሆኑ ሱሪ ስለ ሆነ ብቻ ሳይሆን በልዩ ልዩ መንገድ መዝኖ ሊያደርጉት የማይገባ ከሆነ መተው ይጠበቅባቸዋል፡፡
" በተረፈ ሴቶች “ሱሪ” መልበሱን ካልተውት ሲብስ ነው እንጂ “ሱሪ” በመሆኑ ብቻ ለባሾቹን ከመተቸት መተው ይመረጣል፡፡ እንዲህ የተባለው “ሴቶች ሱሪ መልበስ አይተዉም' በማለት ተስፋ ከመቁረጥ የመነጨ ሳይሆን “ሱሪ” መልበስ እጅግም የሚነቅፉት ነገር ባለመሆኑ ነው፡፡ ምክንያቱም አንደኛ አርአያን መለወጥ ከሚለው ምሥጢር ከመነሣት ካልሆነ በቀር “ሱሪ" በመሆኑ ብቻ “ሱሪ” መልበስን ለመንቀፍ በቂ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት አይኖረንም፡፡ ሁለተኛ ሁሉም ባይሆኑ አንዳንድ ሴቶች ሱሪ የሚለብሱበት የጤና መታወክን ጨምሮ አፍን የሚያስይዝ በቂ ምክንያት አላቸው፡፡ ሦስተኛ ደግሞ መሠረት በሌለው ነገር ለመተቸት መሞከር የሚጎዳው የሚለብሱትን ሳይሆን ሐሜተኞቹንና እንተቻለን ባዮቹን በመሆኑ ነው፡፡ "
ሕይወተ ወራዙት ክፍል አንድ፣ ገጽ 230
