ch
Feedback
ዲያቆን ሚካኤል እሸቱ

ዲያቆን ሚካኤል እሸቱ

前往频道在 Telegram

ይህ የዲያቆን ሚካኤል እሸቱ ይፋዊ ገጽ ነው። ለጥያቄዎችና ለአስተያየት @Dnmichael12

显示更多
1 706
订阅者
+324 小时
+187
+4730
帖子存档
ለበለጠ መረጃ ፦ 📞 0986545581 | 0911672171
ለበለጠ መረጃ ፦ 📞 0986545581 | 0911672171

Repost from N/a
ሰኔ 12 ቅዱስ ሚካኤል ቅድስት አፎምያን ከሰይጣን እጅ እንደ አዳናት ✨ በዚህ ልዩ ቪዲዮ የቅዱስ ሚካኤልን ረዳትነትና ድንቅ ተአምር የምንማርበትን የቅድስት አፎምያን ታሪክ ይዘንላችሁ ቀርበናል። ሙሉ
ሰኔ 12 ቅዱስ ሚካኤል ቅድስት አፎምያን ከሰይጣን እጅ እንደ አዳናት ✨ በዚህ ልዩ ቪዲዮ የቅዱስ ሚካኤልን ረዳትነትና ድንቅ ተአምር የምንማርበትን የቅድስት አፎምያን ታሪክ ይዘንላችሁ ቀርበናል። ሙሉውን ቪዲዮው ይመልከቱ!👉🏻 link Youtube | Telegram | Instagram | Tiktok #ቅዱስሚካኤል #ሰኔ12 #ቅድስትአፎምያ #ሚካኤል #ኦርቶዶክስተዋህዶ #የቅዱሳንታሪክ #መንፈሳዊትረካ #መርሻ #SilondisTube #የቤተክርስቲያንታሪክ #ስብከት #ኦርቶዶክስ

ዕጣ አውጥተው ልብስህን የተካፈሉህ ፣ ዕጣ ሳታወጣ ግን ሁሉንም ወደድካቸው። ኦ ለዚህ ፍቅር አንክሮ ይገባል።
ዕጣ አውጥተው ልብስህን የተካፈሉህ ፣ ዕጣ ሳታወጣ ግን ሁሉንም ወደድካቸው። ኦ ለዚህ ፍቅር አንክሮ ይገባል።

+1
ፖለቲካ ነው ብለው አይኔ ግንባር ነው ሚሉ ኡስታዞች ፕለቲካ ከሆነኮ አላህ ዋክበር ማለት አያስፈልግም አላህ ዋክበር ሲባልኮ ነገሩ ሃይማኖታዊ ጭፍጨፋ መሆኑን ነው ሚያሳያን ሙስሊሞች የአሸባሪ ቡድን አባላት ሆነው ሲገድሉ በራሳቸው እንደ ግለሰብ ሙስሊሞች ተነሳስተው ብቻ ሳይሆን በኡስታዞቻቸውም የሚደገፍ ነው በውጭ ሕዝቡ እንዳያውቅ እውነተኛ ማንነታቸውን አዝነናል ይላሉ በየ መስጊድቻቸው ግን እውነተኛው ማንነት እንደዚ አይነት ነው

Some went down to the sea in ships, doing business on the great waters; they saw the deeds of the LORD, his wondrous works in
Some went down to the sea in ships, doing business on the great waters; they saw the deeds of the LORD, his wondrous works in the deep. For he commanded, and raised the stormy wind, which lifted up the waves of the sea. They mounted up to heaven, they went down to the depths; their courage melted away in their evil plight; they reeled and staggered like drunken men, and were at their wits’ end. Then they cried to the LORD in their trouble, and he delivered them from their distress; he made the storm be still, and the waves of the sea were hushed. Then they were glad because they had quiet, and he brought them to their desired haven.
(Psalm 107:23-30)

እንኳን እግዚአብሔር አስፈታሕ ወንድሜ መምህር ዘላለም።
እንኳን እግዚአብሔር አስፈታሕ ወንድሜ መምህር ዘላለም።

ታስሯል ዲያቆን ዘላለም ታዬ በወቅታዊ ጉዳይ መታሰሩን ከመሸ መረጃው ደርሶናል። ዲያቆን ዘላለም ታዬ ትናንት ምሽት 4:00 በሕግ አካላት "ለጥያቄ ትፈለጋለህ" ብለው ወደ ማዕከላዊ እንደወሰዱት እና በ
ታስሯል ዲያቆን ዘላለም ታዬ በወቅታዊ ጉዳይ መታሰሩን ከመሸ መረጃው ደርሶናል። ዲያቆን ዘላለም ታዬ ትናንት ምሽት 4:00 በሕግ አካላት "ለጥያቄ ትፈለጋለህ" ብለው ወደ ማዕከላዊ እንደወሰዱት እና በዚያው በማዕከላዊ እንደታሰረ ይገኛል።

ነገር ግን፥ ለዓለም ከሚመች ከከንቱ መለፍለፍ ራቅ፤ ኀጢአተኝነታቸውን ከፊት ይልቅ ይጨምራሉና፥ ቃላቸውም እንደ ጭንቍር ይባላል፤
2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 2፥16

"ግድየለም አትዘን ፤ አታልቅስ" አይባልም! ሀዘን ላይ ስንሆን አምላካችንን ለምን ተዉከኝ እንላለን ዲያቆን አቤል ... https://youtube.com/watch?v=rJwpA_15Sx0&si=sX2TX3K1kWaH8A9Z

Repost from N/a
ኦ ቀለሟ ! ያሳደደችኝ ሴት ከአስርት ዓመታት በኋላ አሜሪካ ድረስ መጣችብኝ! 😱 የዮዲት እና የሄኖክ ፍቅር አደጋ ላይ ነው! ሙሉ ቪዲዮውን ለማየት ሊንኩን ተጭነው አሁኑኑ ይመልከቱ! 👉🏻 link
ኦ ቀለሟ ! ያሳደደችኝ ሴት ከአስርት ዓመታት በኋላ አሜሪካ ድረስ መጣችብኝ! 😱 የዮዲት እና የሄኖክ ፍቅር አደጋ ላይ ነው! ሙሉ ቪዲዮውን ለማየት ሊንኩን ተጭነው አሁኑኑ ይመልከቱ! 👉🏻 link Youtube | Telegram | Instagram | Tiktok       #MershaKahali #YoftaheKasa#ኦቀለሟ #የፍቅርታሪክ #የሀበሻ #ኢትዮጵያ #ትረካ #ለናንተ #ethiopia #storytime

አርሲ የደም ምድር

Repost from Milkyanimates
ሰላም እንዴት ሰነበታችሁ? ሰላም ናችሁ? ማኅበረ ቅዱሳን ከዚህ ቀደም በ2 ዙሮች የግራፊክስ ዲዛይን ሥልጠና ሰጥቷል አሁንም ደግሞ በ3ተኛ ዙር ቪዲዮ ኤዲቲንግንም አካቶ "የግራፊክስ ዲዛይንና የቪዲዮ
ሰላም እንዴት ሰነበታችሁ? ሰላም ናችሁ? ማኅበረ ቅዱሳን ከዚህ ቀደም በ2 ዙሮች የግራፊክስ ዲዛይን ሥልጠና ሰጥቷል አሁንም ደግሞ በ3ተኛ ዙር ቪዲዮ ኤዲቲንግንም አካቶ "የግራፊክስ ዲዛይንና የቪዲዮ ኤዲቲንግ ትምህርት" ሊሰጥ ዝግጅቱን አጠናቆ ምዝገባ ጀምሯል። መመዝገቢያ ሊንክ https://docs.google.com/forms/d/1h1i2KU0vG3rZnCCX-SzS9lCeAzVckuaXq-x77o04n6k/edit ☎️ 0921530282 ☎️ 0935213944

እነዚያ እንደ እሳት ላንቃ የተከፋፈሉት ልሳኖች ከመታየትም አልፈው በሐዋርያቱ ላይ መቀመጣቸው፣ ደቀ መዛሙርቱ የሚያዩት ነገር ሁሉ ቅዠት ወይም ምናባዊ ሳይሆን እውነተኛ የእግዚአብሔር ድንቅ ሥራ መሆኑን እንዲገነዘቡ ነው፡፡ ከዚያም በኋላ በሁሉም ላይ መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው፡፡ የእግዚአብሔርን ልጅ በረገጡና አመጽ ወዳድ በነበሩት አይሁድ ቅንዓትና ቁጣ ሲሞላ፣ የሰላም ልጆች በነበሩት ሐዋርያት ግን መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው፡፡ ስለዚህም መንፈስ ቅዱስ ይናገሩ ዘንድ (በየአቅማቸው) እንደ ሰጣቸው በሌሎች ቋንቋዎች ይናገሩ ጀመር፡፡   እግዚአብሔር አሕዛብ ያለ ሐዋርያት ስብከት በሥላሴ ማመን እንደማይችሉ፣ ሐዋርያትም ያለ መንፈስ ቅዱስ መውረድ በየአገሩ ቋንቋዎች ሁሉ መስበክ እንደማይችሉ ዐወቀ፡፡ ስለዚህም በሰናዖር ሜዳ የተበተኑትን የዓለምን ቋንቋዎች በሐዋርያት አንደበት ሰብስቦ ያኖር ዘንድ ቅዱስ መንፈሱን ላከ፡፡ የተላከውም መንፈስ ያለ አንድ ቋንቋ የማይናገረውን የሐዋርያቱን አንደበት በቅጽበት አሰለጠነው። በእውነት እንደ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ያለ አስማሪ ማን ነው?!በዚህችም እለት ሐዋርያቱ በዓለም ሁሉ ቋንቋዎች ተሞልተው ከእርሷ የወጡባት የጽዮን አዳራሽ (ጽርሐ ጽዮን) እንደ ምን ያለች ናት?! መንፈስ ቅዱስ ከዚያም በፊት ከዚያም በኋላ ታይታ የማትታወቅ ልዩ ትምህርት ቤት አደረጋት፡፡ ሐዋርያቱም በመንፈስ ቅዱስ ተሟሙቀው በሰበኩት በመጀመሪያ ዕለት ስበከት ብዙዎችን አሳምነው አጠመቁ። በዚህ የመከር በዓል አይሁድ ከአዲሱ እህል ለእግዚአብሔር ቁርባን ሲያቀርቡ፣ ሐዋርያቱ ግን የክርስቶስ አካል ለሆነችው ለሐዲሲቷ ቤተ ክርስቲያን ከእህል ቁርባን ይልቅ የሚወደዱ ምእመናንን ስጦታ አድርገው አቀረቡ። በአይሁድ የመከር በዓል ቀን በሐዋርያቱ በተሰጠ ትምህርት የእግዚአብሔር እርሻ የሆኑ ምዕመናን በዝተው አብበው ተገኙ። እውነትም የመከር በዓል!!! ዲያቆን አቤል ካሳሁን abelzebahiran@gmail.com

+++"እውነትም የመከር በዓል"+++ ጌታችን ከትንሣኤው በኋላ በጋራም በተናጠልም ለሐዋርያቱ እየታያቸው የትንሣኤውን አማናዊነትና ‹ስለ እግዚአብሔር መንግሥት ነገር እየነገራቸው› አርባ ቀን ቆይቷል፡፡(ሐዋ 1:3) በአርባኛውም ቀን ሲያርግ ‹የሚያጸና፣ የሚያነጻ እና የሚያጽናና መንፈስ ቅዱስን› እንደሚልክላቸው ተስፋን ሰጣቸው፡፡ ነገር ግን ከላይ ኃይልን እስከሚቀበሉባት ቀን ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ እንዲቆዩ አዘዛቸው፡፡ (ሉቃ 24፡49-51) ሐዋርያቱም ከጌታ ዕርገት በኋላ በጽዮን አዳራሽ (ጽርሐ ጽዮን) ውስጥ በአንድ ልብ ሆነው በጸሎት ይተጉ ጀመር፡፡    ለሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ የወረደበት ቀን ማለት አይሁድ በዓመት ውስጥ ከሚያከብሯቸው ታላላቅ በዓላት መካከል አንዱ የሆነውን ‹በዓለ ሃምሳ› የሚውልበት ዕለት ነበር፡፡ ይህም በዓል አይሁድ ፋሲካቸውን ካከበሩ ከሰባት ሳምንታት በኋላ ባለው ሰንበት ማግስት (በእሁድ፣ በ50ኛው ቀን) ስለሚከበር ‹‹ጰንጠቆስጤ››/‹‹በዓለ ሃምሳ›› ተብሎ ይጠራል፡፡ በዚህም ቀን እስራኤላውያን አርሰው ካመረቱት ላይ አዲሱን የእህል ቁርባን ለእግዚአብሔር የሚያቀርቡበትም ዕለት ስለሆነ በሌላ ስያሜ ‹የመከር በዓል› ተብሎ ይጠራል፡፡ በተጨማሪም የእስራኤል መስፍን የነበረው ሊቀ ነቢያት ሙሴ በሲና ተራራ ከአምላኩ ዘንድ ሕገ ኦሪት መቀበሉንም የሚያስቡበት ቀን ነው፡፡   በተለያዩ የዓለም ክፍላት የሚኖሩ አይሁድ ከያሉበት አገር ተጉዘው በመምጣት የፋሲካንና የመቅደስ መታደስ በዓላትን በኢየሩሳሌም ተሰብስበው ለማክበር ይቸገሩ ነበር፡፡ የችግሩም ምክንያት እነዚህ በዓላት በሚውሉበት ወቅት ያለው የአየር ጠባይ በጣም አስቸጋሪና ነፋሱም ማዕበል የሚቀሰቅስ በመሆኑ ነው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በዚሁ ጊዜ ወደ ኢጣልያ ለመሄድ በመርከብ በተሳፈረ ጊዜ ስላጋጠመው እንግልትና ስቃይ በሐዋርያት ሥራ ላይ ተጽፏል፡፡(ሐዋ 27፡9) እርሱ ራሱም በመንገዱ መካከል አብረውት ይጓዙ የነበሩትን ሰዎች ‹‹እናንተ ሰዎች ሆይ ይህ ጉዞ በጥፋትና በብዙ ጉዳት እንዲሆን አያለሁ፤ ጥፋቱም በገዛ ሕይወታችን ነው እንጂ በጭነቱና በመርከቡ ብቻ አይደለም›› ሲል ጉዞውን ለጥቂት ጊዜ እንዲያዘገዩት መክሯቸው ነበር፡፡ በዓለ ሃምሳ ግን የመጀመሪያዎቹ የፀደይና የመከር ወቅት ላይ ስለሚውል የአየሩ ሁኔታ ለመርከብ ጉዞ የተመቸ ነው፡፡ ስለዚህም የፋሲካና የመቅደስ መታደስ በዓላት ላይ በኢየሩሳሌም መገኘት ያልቻሉ አይሁድ ሁሉ በጉጉት የሚጠባበቁትና ወደ ቅድስቲቱ ከተማ በመግባት ተሰብስበው የሚያከብሩት ታላቅ በዓል ነው፡፡   "በዓለ ሃምሳ" የሚለው መጠሪያ አስቀድመን እንደ ተናገርነው በኦሪቱ ለሚከበረው በዓል መታወቂያነት የሚያገለግል ስያሜ ቢሆንም፣ የጌታ ሐዋርያትም መንፈስ ቅዱስን የተቀበሉት ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ በተነሣ በሃምሳኛው ቀን በመሆኑ ለሐዲስ ኪዳኑም ታላቅ በዓል መጠሪያነት ቢውል የሚያውክ አይሆንም፡፡ ይሁን እንጂ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ይህንን ቀን ‹በዓለ ጰራቅሊጦስ› ስትል ለሐዋርያት በወረደው ቅዱስ መንፈስ ልዩ ስም ትጠራዋለች፡፡ ‹‹ጰራቅሊጦስ›› የሚለው የግሪክ ቃል ሲሆን ‹‹መጽንዒ፣ መንጽሒ››/‹‹የሚያጸና፣ የሚያነጻ›› የሚል ትርጉም አለው፡፡   ወደ ቀደመ ነገራችን እንመስና ሐዋርያቱ በጽርሐ ጽዮን ተሰብስበው ሲጸልዩ ሳሉ ድንገት እንደሚነጥቅ ዓውሎ ነፋስ ከሰማይ ድምጽ መጣ፣ ተቀምጠው የነበሩበትንም ቤት ሁሉ ሞላው፡፡(ሐዋ 2፡2) በዚህ ክፍል ይህን ታሪክ የሚጽፍልን ቅዱስ ሉቃስ የመንፈስ ቅዱስ መውረድ ‹ድንገት› እንደ ሆነ ይነግረናል፡፡ ለመሆኑ ‹ድንገት› ሲል ምን ለማለት ፈልጎ ነው? ጸሐፊው ቅዱስ ሉቃስ ‹ድንገት› የሚለውን ቃል የተጠቀመው ነገሩ በሰው ቀጠሮ ሳይሆን ‹በእግዚአብሔር ጊዜ› የተፈጸመ መሆኑን ለማሳየት ነው፡፡ ሐዋርያት አጽናኙ መንፈስ እንደሚላክላቸው ቢነገራቸውም በየትኛው ቀን ግን እንደሚወርድ የሚያውቁት ነገር አልነበረም፡፡ ስለዚህም ‹ድንገት› የሚለው ቃል ሐዋርያቱ ቀኑን ፈጽመው አለማወቃቸውን ያሳያል፡፡ ሁል ጊዜ ጸጋን የሚሰጠው እግዚአብሔር ስለሆነ የሚሰጥበት ቀነ ቀጠሮ በሰጪው እንጂ በተቀባዩ አይወሰንም፡፡ ስለዚህ የተቀባዩ ሰው ድርሻ ሳይዝል ተስፋም ሳይቆርጥ የአምላኩን የሥራ ቀን በትዕግሥት መጠባበቅ ነው፡፡   የዓውሎ ነፋሱም ድምፅ ልክ ኤልያስ የምድሩን መናወጥና እሳቱን ሲመለከት በመጎናጸፊያው ተሸፍኖ ከዋሻው በመውጣት እግዚአብሔርን ለማናገር ራሱን እንዳዘጋጀ፣ ሐዋርያቱም የመንፈስ ቅዱስን መውረድ እንዲያስተውሉና ለዚያም ራሳቸውን እንዲያዘጋጁ የተሰማ የማንቂያ ድምፅ ነው፡፡(1ኛ ነገ 19፡12) በተጨማሪም ድምፅ ‹ኃይልን› ያመለክታል፡፡ ስለዚህ እንደሚነጥቅ ዓውሎ ነፋስ የተሰማው ድምጽ ሐዋርያቱ ከመንፈስ ቅዱስ ኃይል መቀበላቸውን የሚያሳይ ነው፡፡ እዚህ ላይ ጌታችን በዮርዳኖስ ወንዝ ከተጠመቀ በኋላ መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል ወርዶ በእርሱ ላይ ሲያርፍ ያሰማው አንዳች ድምፅ አለመኖሩን ልብ ይሏል፡፡(ማቴ 3፡16) ይህም እርሱ ለደካሞች ጽንዕ የሚሆን እንጂ እንደ ፍጡር ኃይል የሚቀበል አለመሆኑን የሚያመለክት ነው፡፡ አስቀድሞ መድኃኒታችን ለኒቆዲሞስ ‹‹ነፋስ ወደሚወደው ይነፍሳል›› ሲል እንዳስተማረው፣ በዚህች ቀን በነፋስ የተመሰለ መንፈስ ቅዱስ በወደዳቸው በሐዋርያት ሰውነት ያድር ዘንድ ወደ ጽርሐ ጽዮን ነፈሰ(መጣ፣ ወረደ)፡፡ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ መንፈስ ቅዱስን ከነፋሳትም መርጦ ከደቡብ አቅጣጫ በሚነፍሰው ነፋስ ይመስለዋል፡፡ ብዙ ጊዜ ከሰሜኑ የሚነሣው ነፋስ ቀዝቃዛና ሰብል የሚያጠፋ በመሆኑ በመካከለኛው ምሥራቅ የሚኖሩ ገበሬዎች ይፈሩታል፡፡ ከደቡብ አቅጣጫ የሚነፍሰው ነፋስ ግን ከምድር ወገብ የሚወጣውን ሞቃታማ አየር ይዞ ስለሚነፍስ የተዘራውን ሰብል ያበስለዋል፡፡ በዚህም ገበሬዎቹ ደስ ይሰኙበታል፡፡ ሊቁ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ መንፈሳዊ ብስለትን የሚሰጠው መንፈስ ቅዱስ ልክ በደቡብ እንደሚነፍሰውና ሰብሎችን እንደሚያበስለው ያለ ተወዳጅ ነፋስ ነው ይላል፡፡   ቀጥሎም ለሐዋርያቱ እንደ እሳት የተከፋፈሉ ልሳኖች ታዩአቸው፡፡ በያንዳንዳቸውም ላይ ተቀመጡባቸው፡፡ በሁሉም ላይ መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው፡፡ አስተውሉ በዚህ አንድ ታሪክ ውስጥ መንፈስ ቅዱስ በእሳትም በነፋስም ተመስሎ ሲቀርብ እናገኛለን፡፡ ታዲያ መንፈስ ቅዱስ የተመሰለባቸው ምሳሌዎች መብዛታቸው ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ እንዳብራራው የመንፈስ ቅዱስ ባሕርይ በምልዓት የማይታወቅ መሆኑን ያመለክታል፡፡ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን በእሳት መመሰል አዲስ ነገር አይደለም፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም በዕብራውያን መልእክቱ ‹‹አምላካችን በእውነት የሚያጠፋ እሳት ነውና›› ሲል ስለ እርሱ ተናግሯል፡፡(ዕብ 12፡29) መንፈስ ቅዱስ በእሳት መመሰሉ፣ ከከርሰ ምድር መዓድናትን የሚያወጣ ባለሙያ ከመሬት ቆፍሮ ያወጣውን መዓድን ከትቢያው የሚለየው በእሳት እንደ ሆነ እንዲሁ፣ መንፈስ ቅዱስም ነፍሳችንን ትቢያ ከተባለ ኃጢአት ሁሉ ለይቶ ያነጻታልና በእሳት ተመሰለ፡፡ ይህንንም በተመለከተ ነቢየ እግዚአብሔር ኢሳይያስ ‹‹የእስራኤልም ብርሃን እንደ እሳት፣ ቅዱሱም እንደ ነበልባል ይሆናል፡፡ እሾኹንና ኩርንችቱን በአንድ ቀን ያቃጥላል›› ሲል ይናገራል።(ኢሳ 10፡17) አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫም በመጽሐፈ ምሥጢሩ ለሐዋርያቱ በሃምሳኛው ቀን በእሳት አምሳል የወረደው መንፈስ ቅዱስ ‹‹ሥጋቸውን ሳይሆን የኃጢአታቸውን እሾኽ አቃጠለ›› በማለት ይገልጻል፡፡