የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
تُعد قناة የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 14 356 مشتركاً، محتلاً المرتبة 6 146 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 357 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 14 356 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 23 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 507، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 14، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 25.68%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 13.08% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 681 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 875 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 28.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
وصف القناة غير متوفر.
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 24 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.
14 356
المشتركون
+1424 ساعات
+1027 أيام
+50730 أيام
أرشيف المشاركات
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ጾመ ፍልሰታን በማስመልከት ያስተላለፉት መልእክት፣ ቃለ በረከትና ቡራኬ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይነበባል።
መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
በሀገር ውስጥና በተለያዩ ክፍለ ዓለማት የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት በሙሉ!
በማሕፀነ ማርያም በፈጸመው እውነተኛ ተዋሕዶ የሰው ልጅን ከኃሣር ወደ ክብር የመለሰ እግዚአብሔር አምላካችን፣ እንኳን ለሁለት ሺሕ ዐሥራ ስድስት ዓመተ ምሕረት ጾመ ቅድስት ማርያም በደኅና አደረሰን አደረሳችሁ!፤
‹‹ተፈሥሒ ኦ ምልእተ ጸጋ፣ ተፈሥሒ እስመ ረከብኪ ሞገሰ በኀበ እግዚአብሔር፡- ምልእተ ጸጋ ሆይ ደስ ይበልሽ፤ በእግዚአብሔ ዘንድ ሞገስን አግኝተሻልና ደስ ይበልሽ›› (ሉቃ. 1÷28-30")
የክብር አምላክ እግዚአብሔር የሰው ልጅን ከወደቀበት ዐዘቅተ ኵነኔ የሚያድንበት ዕድል እንዳዘጋጀ በብሉይ ኪዳን በስፋት ገልፆል፤ የማዳን ስራውም ከሰው ወገን ከሆነች ቅድስት ድንግል በሚወለደው መሲሕ እንደሚፈጸም አስረድቶአል፤ የማዳን ቀኑ በደረሰ ጊዜም መልእክቱን በፊቱ በሚቆመው በቅዱስ ገብርኤል በኩል ልኮአል፤ ቅዱስ ገብርኤልም የተነገረውን መልእክት ለድንግል ማርያም አድርሶአል፡፡
ቅዱስ ገብርኤል ለድንግል ማርያም እንዲነግር ከታዘዘባቸው መካከል ‹‹ጸጋን የተመላሽ ደስተኛይቱ ሆይ÷በእግዚአብሔር ዘንድ ሞገስን አግኝተሻልና ደስ ይበልሽ›› የሚል አስደናቂ መልእክት ይገኝበታል፡፡
የተወደዳችሁ ሕዝበ ክርስቲያን!
ከእግዚአብሔር መንጭቶ በቅዱስ ገብርኤል በኩል ለድንግል ማርያም የተነገረ ይህ መልእክት፣ የቅድስት ድንግል ማርያምን ክብር ከመግለጽ ባሻገር ለሰው ልጆች ሁሉ ያለው ፋይዳ በእጅጉ የላቀ ነው፤
‹‹ጸጋ›› የሚለው ቃል እንደ ቅዱስ መጽሐፍ አስተምህሮ ያልተወሰነ፣ ገደብና ቅድመ ሁኔታ የሌለው ስጦታን ሲያመለክት ‹‹ሞገስ›› የሚለው ቃል ደግሞ ተወዳጅነትን ተደማጭነትን ተሰሚነትን የሚያመለክት የክብርና የባለሟልነት መግለጫ ቃል ነው፡፡
እነዚህ ቃላት ከእግዚአብሔር ዘንድ በቅዱስ ገብርኤል በኩል ለቅድስት ድንግል ማርያም ተነግረዋል፤ የእግዚአብሔር ቃል የማይለወጥ ነውና ቃላቶቹ ለድንግል ማርያም ቃል ኪዳን ሆነው የተሰጡ ናቸው፤ የተሰጡበትም ምክንያት ሰውን ለማዳን ስራ እንዲውሉ እንጂ ለሌላ አይደለም፡፡
ምክንያቱም የእግዚአብሔር የማይናወጥ ፈቃድ ሰውን ማዳን ነውና፤ በመሆኑም ቅድስት ድንግል ማርያም ከእግዚአብሔር በተሰጣት በዚህ ገደብ የሌለው ቃል ኪዳኗ ሰውን ልትታደግ በቅታለች፤ይህም በቃና ዘገሊላ ባደረገችው ምልጃ በጭንቀት የተዋጡትን ሠርገኞች እንዴት እንደታደገች በቅዱስ ወንጌል ተጽፎ እናገኘዋለን፤ቅድስት ድንግል ማርያም ቀድሞውኑም ከፍ ያለ ሞገስ ተሰጥቶአታልና የሠርጉ አሳላፊዎችን ‹‹የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ›› በማለት ስታዝዝ እናያለን፤ ይህ ለሰው ልጆች ሁሉ የተሰጠ አስደናቂ የትድግና ስጦታ ነው፡፡
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን!
የድንግል ማርያም የጸጋ ስጦታ በብሥራተ ገብርኤል ተገልጾ፣ በቃና ዘገሊላ ተተግብሮ በዕለተ ስቅለት ‹‹እነሆ ልጅሽ፣ እነኋት እናትህ›› በሚል መለኮታዊ ማኅተም የታተመ ነው፤ ይህ ቃል እሷ እናታችን መሆኗን፤ እኛም ልጆችዋ መሆናችንን ያረጋገጠ ማኅተመ ቃል ኪዳን ነው፤ የቃል ኪዳኑ ይዘት እሷ በአማላጅነቷ እንደ ልጅ ልትንከባከበን እኛም እንደ እናት ልናከብራትና ልንማፀናት የሚገባን መሆኑን ያሳያል፤ የእናትነትና የልጅነት ማረጋገጫ የሆነ ይህንን የቃል ኪዳን ማኅተም ሊሰርዝም ሆነ ሊፍቅ ሊደመስስም የሚችል ኃይል የለም፡፡
ይህ ጸጋና ሞገስ በምድር ብቻ ሳይሆን በሰማይም የሚቀጥል እንጂ የሚገደብ አይደለም፤ ሞት፣ ቦታና ዘመንም አይወስኑትም፤ ምክንያቱም የእግዚአብሔር ቃል ኪዳን በሞት በቦታና በዘመን አይገደብምና ነው፤ ‹‹ኪዳኑንም ለዘለዓለም ያስባል›› ተብሎ የተገለጸውም ለዚህ ነው፤ (መዝ. )111÷5)
መንፈስ ቅዱስም በእሷ አንደበት ‹‹እነሆ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ነሽ ይሉኛል›› በማለት የተናገረው ይህንን ለማስረዳት እንደሆነ ማስተዋል ያሻል፡፡
በእግዚአብሔር ተሰጥቶ፣ በቃል ኪዳን ታትሞ፣ በቅዱስ ገብርኤል ተብራርቶ፣ በጌታችን ተረጋግጦና በሐዋርያት በኩል የተላለፈልን፣ ሰውን ማዳን ግቡ የሆነ የድንግል ማርያም ምልጃ ጥንታዊት፣ ሐዋርያዊት፣ በሁሉ ያለች፣ አንዲትና ቅድስት ኦርቶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ለሁለት ሺሕ ዓመታት ያህል አምና እና ተቀብላ ስትጠቀምበት ኖራለች፤ አሁንም በዚሁ ትቀጥላለች፡፡
በኦርቶዶክሱ ዓለም ዛሬ የሚጀመረው የጾመ ማርያም ሱባዔም የዚሁ ጭብጥ ማሳያ ነው፤ ዋናው መልእክቱም ድንግል ማርያም በተሰጣት ጸጋና ሞገስ በጸሎቷ ከእግዚአብሔር ዘንድ ምሕረትንና ይቅርታን የምታሰጠን ስለሆነች እሷን በመማፀን ወደ እግዚአብሔር እንቅረብ የሚል ሆኖ ይመሰጠራል፡፡
የተወደዳችሁ ሕዝበ ክርስቲያን ልጆቻችን!
ጾም ፈቃደ ሥጋን በማድከምና ፈቃደ ነፍስን በማጎልበት ምሕረተ እግዚአብሔር መሻታችንን የምናሳይበት መንፈሳዊ ማመልከቻ ነው፤ ጾም ከጥንት ጀምሮ የነበረ ከእግዚአብሔር ጋር የሚያገናኝ ድልድይ ነው፤ ቀደምት አበው በጾም ምክንያት ከጥፋት ድነዋል፤ የለመኑትንም አግኝተዋል፤ ምስጢርም ተገልጾላቸዋል፤ ዲያብሎስም ድል አድርገውበታል፡፡
እኛም ዛሬ ጾምን ስንጾም በሀገራችንም ሆነ በአካባቢያችን ብሎም በዓለም ዙሪያ ሁሉ ስጋትን እየጫረ ያለው የጥፋት እንቅስቃሴ እግዚአብሔር እንዲያስቆምልን ከልብ በመጸለይ ሊሆን ይገባል፤ ይህንንም ስናደርግ በጸሎት ብቻ ሳይሆን ንስሐ በመግባትና ቅዱስ ቁርባንን በመቀበል እንደዚሁም የሰላም የፍቅርና የዕርቅ ሰው ሆኖ በእግዚአብሔር ፊት በመቆም ሊሆን ይገባል፡፡
ችግሮችንና አለመግባባቶችን በሰላማዊ መንገድ በውይይትና በምክክር ለመፍታት የሚደረገው ጥረትም በእጅጉ ሊደገፍ ይገባል፤ ግጭትና ጦርነት ከሚያጠፋን በቀር ሊያተርፍልን የሚችል አንዳች ጥቅም የለም፡፡
በመሆኑም በየትኛውም የሀገራችን አካባቢ ያላችሁ ልጆቻችን እባካችሁ ለሰላም ለውይይትና ለሰው ልጆች መብት መከበር ቅድሚያ ስጡ፤ ግድያ፣ ዕገታ፣ አብያተ ሃይማኖትን መዳፈር፣ ዘረፋና ቅሚያ፣ የሴት ልጅን መድፈርና ሰውን ማንገላታት አቁሙ፤
እነዚህ ድርጊቶች ሰብአዊነትን ዝቅ የሚያደርጉ፣ እግዚብሔርን የሚያስቆጡ፣ በታሪክም የሚያሳፍሩ ናቸው፤ እነዚህን ሳናርም የምንጾመው ጾም ትርጉም ስለሌለው ንስሐ ገብተን ከእንደዚህ ያለው ድርጊ ርቀን ጾሙን መጾም ይገባል፤ ይህን ስናደርግ ጾማችን በእግዚአብሔር ፊት ዋጋ ይኖረዋል፡፡
በመጨረሻም
የኢትዮጵያ ሕዝብ በሙሉ በተለይም በጾመ ማርያም ሱባዔ በንስሐና በጸሎት የሚያሳልፉ ሕዝበ ክርስቲያን ስለ ሃይማኖት መጠበቅ፣ ስለሀገር ሰላምና አንድነት፣ እንደዚሁም ስለሕዝቦች ደኅንነትና ጤንነት አጥብቀው እንዲጸልዩ በእግዚአብሔር ስም መልእክታችንን እናስተላልፋለን፡፡
መልካም የሱባዔ ወቅት ያድርግልን
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም
ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ነሐሴ 1 ቀን 2016 ዓ.ም.
ዋሽንግተን ዲሲ - ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ
የካራአሎ ደ/ቅ/ደ/ቀ/መድኃኔዓለም እና ጻድቁ አቡነ ገሪማ ገዳም የፈለገ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት የ29ኛ ዓመት የምስረታ በዓልና ከቅድመ መደበኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያስተማራቸውን ተማሪዎች የምረቃ ሥነ ሥርዓት አካሔደ።
(የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) 29/11/2016 ዓ.ም
ሐምሌ 28 2016 ዓ.ም የካራ አሎ ደ/ቅ/ደ/ቀ/መድኃኔዓለም እና ጻድቁ አቡነ ገሪማ ገዳም የፈለገ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት የ29ኛ ዓመት የምስረታ በዓልና በ2016 ዓ.ም ከቅድመ መደበኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያስተማራቸውን ተማሪዎች በታላቅ ድምቀት አስመርቋል። መርሐ ግብሩን በጸሎት የከፈቱት የገዳሙ አስተዳዳሪ መልአከ ኃይል ቆሞስ አባ ኤፍሬም ሐዱሽ ሲሆኑ ከዚያ በመቀጠል በቀሲስ ልሳነ ጽድቅ ወደ እግዚአብሔር መቅረቢያ መንገድ በሚል ርእስ ቃለ ወንጌል ተላልፏል። የፈለገ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት በተለይ በአብነት ትምህርቱ ላይ በዚህ ዓመት በሊቀ ጠበብት ጸጋዬ ደምሴ መምህርነት 18 ተማሪዎችን ለመዓረገ ዲቁና እንዲሁም አንድ ዲያቆን ደግሞ ለመዓረገ ቅስና እንዲበቁ በማድረግ ተተኪ ካህናትን አፍርተዋል። የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ያዘጋጀውን ሥርዓተ ትምህርት በመተግበር ግንባር ቀደም የሆነው ፈለገ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት በዘንድሮ ዓመት ከቅድመ መደበኛ እስከ 12ኛ ክፍል ከ350 በላይ የሚሆኑ ተማሪዎችን አስተምሮ አስመርቋል። በትናንትናው ዕለት በነበረው የምረቃ መርሐ ግብር ላይ በሥርዓተ ትምህርቱ ላይ ሲያስተምሩ ለነበሩ 60 መምህራን የእውቅና ሰርተፊኬት ሰጥቷል። በተጨማሪም በዓለማዊና በመንፈሳዊ ትምህርት ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን እንዲሁም በርቀት ሲማሩ የቆዩትን የማበረታቻ ሽልማት አበርክተዋል። ለሰንበት ትምህርት ቤቱ በተለያዩ መንገዶች ከፍተኛ አስተዋጽዖ ላደረጉ ምዕመናን የክብር አባል ሰርተፊኬት ተበርክቶላቸዋል። በመጨረሻም በደብሩ አስተዳዳሪ አባታዊ ቡራኬ እና ቃለ ምዕዳን ተሰጥቶ የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል።
(የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት)
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
+4
የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ለአንድ ወራት ያሠለጠናቸውን 44 ተተኪ ሰባክያነ ወንጌል ሠልጣኞችን አስመረቀ።
(የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) 28/11/2016 ዓ.ም
በማዕ/ጎንደር ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት አስተባባሪነት ለአንድ ወራት ያክል በዝግ ሲሰጥ የነበረው የተተኪ ሰባክያነ ወንጌል ሥልጠና የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ኅሩያን አባ ዮሴፍ ደስታ፣ የምዕራብ ጎንደር ሀ/ስብከት ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ኅሩያን አባ ኃ/ማርያም፣ የሀገረ ስብከት የመምሪያ ኃላፊዎች እንዲሁም የሰ/ት/ቤት አባላት በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተመርቀዋል።
በጠቅላላ 34 ወንዶች እና 10 እኅቶች ሥልጠናውን የወሰዱ ሲሆን በዚህ ወርም ከ11 በላይ ተከታታይ ትምህርቶች እና ሥልጠናዎች ተሰጥተዋቸዋል።
የምረቃ መርሐ ግብሩም በክቡር ሥራ አስኪያጁ አባታዊ መልዕክት እና የአደራ ቃል በመስጠት በታላቅ ድምቀት በዛሬው ዕለት ተከናውኗል።
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
ኹለተኛው የአኅጉረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና የምርቃት መርሐ ግብር ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ተከናወነ።
(የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) 27/11/2016 ዓ.ም
ኹለተኛው የአኅጉረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና የምርቃት መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ አብርሃም በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መ/ፖ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅና የባ/ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ ብፁዕ አቡነ ቀለሚንጦስ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፤ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ የስብከተ ወንጌልና ሐዋሪያዊ ተልዕኮ መምሪያ የበላይ ሊቀ ጳጳስ፤ ብፁዕ አቡነ ኤርሚያስ የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፤ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የባሌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፤ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የማደራጃና የድርጅት ሐላፊዎች ፤ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ሐላፊዎች አባቶች ካህናት መምህራንና ተመራቂ ተማሪዎች በተገኙበት በዛሬው ዕለት በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ መሰብሰቢያ አዳራሽ ተካሒዷል።
በመርሐ ግብሩም የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሐላፊ የሆኑት መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወ/ትንሣኤ የእንኳን አደረሳቹ መልዕክት ለተማሪዎች ያስተላለፉ ሲሆን የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተ/ም/ሰብሳቢ የሆኑት ዲያቆን ስንታየሁ ምስጋናውም የሥልጠናውን ዓላማና ጠቀሜታ በአጭሩ ለታዳሚዎች ገለፃ አድርገዋል።
"ለራሳችሁ አይደላችኹም ስለዚህ፥በሥጋችኹ እግዚአብሔርን አክብሩ።" 1ቆሮ 6፥20 መነሻ በማድረግ የዕለቱን ቃለ ወንጌል ብፁዕ አቡነ ማርቆስ ሰጥተዋል።
በመጨረሻም ብፁዕ አቡነ አብርሃም "ቤተ ክርስቲያን ከናንተ ብዙ ትጠብቃለች በሔዳቹበት ሁሉ አገልግሎታችሁ በትዕግስትና በፍቅር ይሁን" በማለት አባታዊ ቡራኬና መመሪያ ለተመራቂ ተማሪዎች አስተላልፈው ለተማሪዎች የምሥክር ወረቀት ሰጥተዋል።
ተመራቂ ተማረዎች መሠረተ ሃይማኖት ፣ አስተዳደር፣ ክህሎትና ሥርዓተ ት/ትን በሚመለከቱ 3 ዘርፎች ከ 20 በላይ ኮርሶችን በተከታታይ ለ20 ቀናት በቀንና በማታ መርሐ ግብር የወሰዱ ሲሆን በምርቃት መርሐ ግብራቸውም ላይ አጠቃላይ ቆይታቸውን በሪፖርት መልክ እንዲሁም ያሬዳዊ ዝማሬ አቅርበዋል።
(የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት)
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
+4
የሲዳማ ሀገር ሰብከት በሰንበት ት/ቤት መምሪያ ክፍል ከሀገረ ሰብከቱ የሰንበት ት/ቤት አንድነት ጉባኤ ጋር በመቀናጀት ሐምሌ 20 እና 21 ቀን 2016 ዓ.ም የ2ኛ ወሰነ ትምህርት ማጠቃለያ ፈተና በ8ቱም ወረዳ በተለይ በርዕሰ ከተማው በሀዋሳ በሁሉም አጥብያ የ4ኛ ክፍል እና የ10ኛ ፈተና አስፈትነዋል።
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
የ2016ዓ.ም የሰንበት ትምህርት ቤቶች የ12ኛ ክፍል የሞዴል ፈተና የፊታችን ቅዳሜና እሑድ እንደሚሰጥ ተገለጠ።
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 25/11/2016ዓ.ም
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፖትርያርክ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ2ኛ ጊዜ የሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና የሞዴል ፈተና ለመስጠት ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ገለጠ።
በሥርዓተ ትምህርቱ መሠረት እየተማሩ 12ኛ ክፍል ለደረሱ በአዲስ አበባና ከአዲስ አበባ ውጪ ላሉ ሀገገረ ስብከቶች ሥር ለሚገኙ አጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ሐምሌ 27 እና 28 2016 ዓ.ም ፤ የሚሰጥ እንደሆነ የሀገር አቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ትምህርት ክፍል ሓላፊ መምህር መኩርያ ጌታቸው ገልጠዋል።
አያይዘውም የማጠቃለያ ፈተናው በተመረጡ የፈተና ጣቢያዎች ነሐሴ 18 እና 19/2016 ዓ.ም እነደሚሰጥ ተናግረዋል።
(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በሀገረ ስብከቱ ለሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሠረት የ4ኛ የ6ኛ እና የ10ኛ ክፍል የማጠቃለያ ምዘና ሰጠ።
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 21/11/2016 ዓ.ም
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በማዕከል ደረጃ ለ4ኛ ጊዜ በሀገረ ስብከቱ ለሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሠረት የ4ኛ የ6ኛ እና የ10ኛ ክፍል የማጠቃለያ ምዘና በዛሬው ዕለት ሰጥቷል።
በሀገረ ስብከቱ በ4ኛ በ6ኛ እና በ10ኛ ክፍል ሥርዓተ ትምህርቱን በሚገባ በመተግበር ላይ የሚገኙ 119 የሚሆኑ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ምዘናውን የወሰዱ ሲሆን በጠቃላላ ከ8400 በላይ ተፈታኝ ተማሪዎች በምዘናው ላይ ተቀምጠዋል።
የምዘናውን ሂደት በቦሌ ሰሚት መካነ ሰላም መድኃኔዓለምና መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን የምዘና ጣቢያ ተገኝተው የጎበኙት የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ማዕምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ ከሚዲያችን ጋር በነበራቸው ቆይታ ሥርዓቱን በጠበቀ መልኩ ምዘናው እንደተሰጠ ጠቁመው ሰንበት ትምህርት ቤቶች ዋነኛ የሰው ኃይል ምንጮች እንዲሆኑ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን በመግለጽ መላው የቤተክርስቲያኒቱ ምዕመናን ልጆቻቸውን ወደ ሰንበት ትምህርት ቤቶች እንዲልኩ ፣ በሰንበት ትምህርት ቤትም እየተሰጡ ያሉ ትምህርቶች ተጠናክረው እንዲቀጠሉና ሰንበት ትምህርት ቤቶች የነገ ካህናትና የቤተ ክርስቲያን መሪዎች መፍለቂያ በመሆናቸውን ጠንክረው መሥራት እንደሚጠበቅባቸው መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
ከማጠቃለያ ምዘና በኋላም በሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ የዕውቅና መስጠት መርሐ ግብር እንደሚሰጥ ከሀገረ ስብከቱ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
+1
ብፁዕ አቡነ አብርሃም በድጋሚ በኹለተኛው የአኅጉረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና ላይ በመገኘት አባታዊ ቡራኬና መልዕክት አስተላለፉ።
(የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) 18/11/2016 ዓ.ም
ብፁዕ አቡነ አብርሃም የኢ/ኦ/ተ/ቤ መ/ፓ/ጠ/ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት እና የሰሜን ጎጃም ሊቀ ጳጳስ በድጋሚ የአኅጉረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና ላይ በመገኘት አባታዊ ቡራኬና መልዕክት አስተላልፈዋል።
ብፁዕነታቸው <<ንቁ ፥ በሃይማኖት ቁሙ ፥ ጎልምሱ ጠንክሩ። በእናንተ ዘንድ ፥ሁሉ በፍቅር ይሁን>> የሚለውን በ 1ኛ ቆሮ 16፥13 የተጠቀሰውን ቃለ ወንጌል መነሻ በማድረግ <<የእናት ቤተ ክርስቲያን አደራ አለባቹ ነቅታቹ በሃይማኖት ቁሙ ÷ ጎልምሱ ጠንክሩ ይሔንን ስታደርጉ ግን እርስ በእርሳቹ በመዋደድ በፍቅር ይሁን>> በማለት ለሰንበት ት/ቤት መምህራኑ አባታዊ ምክርና ቡራኬያቸውን ሰጥተዋል።
ከተለያየ አኅጉረ ስብከት የመጡት የሰንበት ት/ቤት መምህራንም ለብፁዕ አቡነ አብርሃም በየአካባቢያቸው ስለሚስተዋለው ችግሮች ጥያቄ አቅርበው ብፁዕነታቸው ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተውባቸዋል።
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
