ch
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

前往频道在 Telegram

📈 Telegram 频道 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU 的分析概览

频道 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 359 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 6 129,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 349

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 359 名订阅者。

根据 24 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 522,过去 24 小时变化为 23,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 27.03%。内容发布后 24 小时内通常能获得 N/A% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 880 次浏览,首日通常累积 0 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 33

📝 描述与内容策略

尚未提供频道描述。

凭借高频更新(最新数据采集于 25 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

14 359
订阅者
+2324 小时
+1087
+52230
帖子存档
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ጾመ ፍልሰታን በማስመልከት ያስተላለፉት መልእክት፣ ቃለ በረከትና ቡራኬ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይነበባል። መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! በሀገር ውስጥና በተለያዩ ክፍለ ዓለማት የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት በሙሉ! በማሕፀነ ማርያም በፈጸመው እውነተኛ ተዋሕዶ የሰው ልጅን ከኃሣር ወደ ክብር የመለሰ እግዚአብሔር አምላካችን፣ እንኳን ለሁለት ሺሕ ዐሥራ ስድስት ዓመተ ምሕረት ጾመ ቅድስት ማርያም በደኅና አደረሰን አደረሳችሁ!፤ ‹‹ተፈሥሒ ኦ ምልእተ ጸጋ፣ ተፈሥሒ እስመ ረከብኪ ሞገሰ በኀበ እግዚአብሔር፡- ምልእተ ጸጋ ሆይ ደስ ይበልሽ፤ በእግዚአብሔ ዘንድ ሞገስን አግኝተሻልና ደስ ይበልሽ›› (ሉቃ. 1÷28-30") የክብር አምላክ እግዚአብሔር የሰው ልጅን ከወደቀበት ዐዘቅተ ኵነኔ የሚያድንበት ዕድል እንዳዘጋጀ በብሉይ ኪዳን በስፋት ገልፆል፤ የማዳን ስራውም ከሰው ወገን ከሆነች ቅድስት ድንግል በሚወለደው መሲሕ እንደሚፈጸም አስረድቶአል፤ የማዳን ቀኑ በደረሰ ጊዜም መልእክቱን በፊቱ በሚቆመው በቅዱስ ገብርኤል በኩል ልኮአል፤ ቅዱስ ገብርኤልም የተነገረውን መልእክት ለድንግል ማርያም አድርሶአል፡፡ ቅዱስ ገብርኤል ለድንግል ማርያም እንዲነግር ከታዘዘባቸው መካከል ‹‹ጸጋን የተመላሽ ደስተኛይቱ ሆይ÷በእግዚአብሔር ዘንድ ሞገስን አግኝተሻልና ደስ ይበልሽ›› የሚል አስደናቂ መልእክት ይገኝበታል፡፡ የተወደዳችሁ ሕዝበ ክርስቲያን! ከእግዚአብሔር መንጭቶ በቅዱስ ገብርኤል በኩል ለድንግል ማርያም የተነገረ ይህ መልእክት፣ የቅድስት ድንግል ማርያምን ክብር ከመግለጽ ባሻገር ለሰው ልጆች ሁሉ ያለው ፋይዳ በእጅጉ የላቀ ነው፤ ‹‹ጸጋ›› የሚለው ቃል እንደ ቅዱስ መጽሐፍ አስተምህሮ ያልተወሰነ፣ ገደብና ቅድመ ሁኔታ የሌለው ስጦታን ሲያመለክት ‹‹ሞገስ›› የሚለው ቃል ደግሞ ተወዳጅነትን ተደማጭነትን ተሰሚነትን የሚያመለክት የክብርና የባለሟልነት መግለጫ ቃል ነው፡፡ እነዚህ ቃላት ከእግዚአብሔር ዘንድ በቅዱስ ገብርኤል በኩል ለቅድስት ድንግል ማርያም ተነግረዋል፤ የእግዚአብሔር ቃል የማይለወጥ ነውና ቃላቶቹ ለድንግል ማርያም ቃል ኪዳን ሆነው የተሰጡ ናቸው፤ የተሰጡበትም ምክንያት ሰውን ለማዳን ስራ እንዲውሉ እንጂ ለሌላ አይደለም፡፡ ምክንያቱም የእግዚአብሔር የማይናወጥ ፈቃድ ሰውን ማዳን ነውና፤ በመሆኑም ቅድስት ድንግል ማርያም ከእግዚአብሔር በተሰጣት በዚህ ገደብ የሌለው ቃል ኪዳኗ ሰውን ልትታደግ በቅታለች፤ይህም በቃና ዘገሊላ ባደረገችው ምልጃ በጭንቀት የተዋጡትን ሠርገኞች እንዴት እንደታደገች በቅዱስ ወንጌል ተጽፎ እናገኘዋለን፤ቅድስት ድንግል ማርያም ቀድሞውኑም ከፍ ያለ ሞገስ ተሰጥቶአታልና የሠርጉ አሳላፊዎችን ‹‹የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ›› በማለት ስታዝዝ እናያለን፤ ይህ ለሰው ልጆች ሁሉ የተሰጠ አስደናቂ የትድግና ስጦታ ነው፡፡ የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን! የድንግል ማርያም የጸጋ ስጦታ በብሥራተ ገብርኤል ተገልጾ፣ በቃና ዘገሊላ ተተግብሮ በዕለተ ስቅለት ‹‹እነሆ ልጅሽ፣ እነኋት እናትህ›› በሚል መለኮታዊ ማኅተም የታተመ ነው፤ ይህ ቃል እሷ እናታችን መሆኗን፤ እኛም ልጆችዋ መሆናችንን ያረጋገጠ ማኅተመ ቃል ኪዳን ነው፤ የቃል ኪዳኑ ይዘት እሷ በአማላጅነቷ እንደ ልጅ ልትንከባከበን እኛም እንደ እናት ልናከብራትና ልንማፀናት የሚገባን መሆኑን ያሳያል፤ የእናትነትና የልጅነት ማረጋገጫ የሆነ ይህንን የቃል ኪዳን ማኅተም ሊሰርዝም ሆነ ሊፍቅ ሊደመስስም የሚችል ኃይል የለም፡፡ ይህ ጸጋና ሞገስ በምድር ብቻ ሳይሆን በሰማይም የሚቀጥል እንጂ የሚገደብ አይደለም፤ ሞት፣ ቦታና ዘመንም አይወስኑትም፤ ምክንያቱም የእግዚአብሔር ቃል ኪዳን በሞት በቦታና በዘመን አይገደብምና ነው፤ ‹‹ኪዳኑንም ለዘለዓለም ያስባል›› ተብሎ የተገለጸውም ለዚህ ነው፤ (መዝ. )111÷5) መንፈስ ቅዱስም በእሷ አንደበት ‹‹እነሆ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ነሽ ይሉኛል›› በማለት የተናገረው ይህንን ለማስረዳት እንደሆነ ማስተዋል ያሻል፡፡ በእግዚአብሔር ተሰጥቶ፣ በቃል ኪዳን ታትሞ፣ በቅዱስ ገብርኤል ተብራርቶ፣ በጌታችን ተረጋግጦና በሐዋርያት በኩል የተላለፈልን፣ ሰውን ማዳን ግቡ የሆነ የድንግል ማርያም ምልጃ ጥንታዊት፣ ሐዋርያዊት፣ በሁሉ ያለች፣ አንዲትና ቅድስት ኦርቶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ለሁለት ሺሕ ዓመታት ያህል አምና እና ተቀብላ ስትጠቀምበት ኖራለች፤ አሁንም በዚሁ ትቀጥላለች፡፡ በኦርቶዶክሱ ዓለም ዛሬ የሚጀመረው የጾመ ማርያም ሱባዔም የዚሁ ጭብጥ ማሳያ ነው፤ ዋናው መልእክቱም ድንግል ማርያም በተሰጣት ጸጋና ሞገስ በጸሎቷ ከእግዚአብሔር ዘንድ ምሕረትንና ይቅርታን የምታሰጠን ስለሆነች እሷን በመማፀን ወደ እግዚአብሔር እንቅረብ የሚል ሆኖ ይመሰጠራል፡፡ የተወደዳችሁ ሕዝበ ክርስቲያን ልጆቻችን! ጾም ፈቃደ ሥጋን በማድከምና ፈቃደ ነፍስን በማጎልበት ምሕረተ እግዚአብሔር መሻታችንን የምናሳይበት መንፈሳዊ ማመልከቻ ነው፤ ጾም ከጥንት ጀምሮ የነበረ ከእግዚአብሔር ጋር የሚያገናኝ ድልድይ ነው፤ ቀደምት አበው በጾም ምክንያት ከጥፋት ድነዋል፤ የለመኑትንም አግኝተዋል፤ ምስጢርም ተገልጾላቸዋል፤ ዲያብሎስም ድል አድርገውበታል፡፡ እኛም ዛሬ ጾምን ስንጾም በሀገራችንም ሆነ በአካባቢያችን ብሎም በዓለም ዙሪያ ሁሉ ስጋትን እየጫረ ያለው የጥፋት እንቅስቃሴ እግዚአብሔር እንዲያስቆምልን ከልብ በመጸለይ ሊሆን ይገባል፤ ይህንንም ስናደርግ በጸሎት ብቻ ሳይሆን ንስሐ በመግባትና ቅዱስ ቁርባንን በመቀበል እንደዚሁም የሰላም የፍቅርና የዕርቅ ሰው ሆኖ በእግዚአብሔር ፊት በመቆም ሊሆን ይገባል፡፡ ችግሮችንና አለመግባባቶችን በሰላማዊ መንገድ በውይይትና በምክክር ለመፍታት የሚደረገው ጥረትም በእጅጉ ሊደገፍ ይገባል፤ ግጭትና ጦርነት ከሚያጠፋን በቀር ሊያተርፍልን የሚችል አንዳች ጥቅም የለም፡፡ በመሆኑም በየትኛውም የሀገራችን አካባቢ ያላችሁ ልጆቻችን እባካችሁ ለሰላም ለውይይትና ለሰው ልጆች መብት መከበር ቅድሚያ ስጡ፤ ግድያ፣ ዕገታ፣ አብያተ ሃይማኖትን መዳፈር፣ ዘረፋና ቅሚያ፣ የሴት ልጅን መድፈርና ሰውን ማንገላታት አቁሙ፤ እነዚህ ድርጊቶች ሰብአዊነትን ዝቅ የሚያደርጉ፣ እግዚብሔርን የሚያስቆጡ፣ በታሪክም የሚያሳፍሩ ናቸው፤ እነዚህን ሳናርም የምንጾመው ጾም ትርጉም ስለሌለው ንስሐ ገብተን ከእንደዚህ ያለው ድርጊ ርቀን ጾሙን መጾም ይገባል፤ ይህን ስናደርግ ጾማችን በእግዚአብሔር ፊት ዋጋ ይኖረዋል፡፡ በመጨረሻም የኢትዮጵያ ሕዝብ በሙሉ በተለይም በጾመ ማርያም ሱባዔ በንስሐና በጸሎት የሚያሳልፉ ሕዝበ ክርስቲያን ስለ ሃይማኖት መጠበቅ፣ ስለሀገር ሰላምና አንድነት፣ እንደዚሁም ስለሕዝቦች ደኅንነትና ጤንነት አጥብቀው እንዲጸልዩ በእግዚአብሔር ስም መልእክታችንን እናስተላልፋለን፡፡ መልካም የሱባዔ ወቅት ያድርግልን እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ! ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ነሐሴ 1 ቀን 2016 ዓ.ም. ዋሽንግተን ዲሲ - ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ

የካራአሎ ደ/ቅ/ደ/ቀ/መድኃኔዓለም እና ጻድቁ አቡነ ገሪማ ገዳም የፈለገ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት የ29ኛ ዓመት የምስረታ በዓልና ከቅድመ መደበኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያስተማራቸውን ተማሪዎች የምረቃ ሥነ ሥርዓት አካሔደ። (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) 29/11/2016 ዓ.ም ሐምሌ 28 2016 ዓ.ም የካራ አሎ ደ/ቅ/ደ/ቀ/መድኃኔዓለም እና ጻድቁ አቡነ ገሪማ ገዳም የፈለገ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት የ29ኛ ዓመት የምስረታ በዓልና በ2016 ዓ.ም ከቅድመ መደበኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያስተማራቸውን ተማሪዎች በታላቅ ድምቀት አስመርቋል። መርሐ ግብሩን በጸሎት የከፈቱት የገዳሙ አስተዳዳሪ መልአከ ኃይል ቆሞስ አባ ኤፍሬም ሐዱሽ ሲሆኑ ከዚያ በመቀጠል በቀሲስ ልሳነ ጽድቅ ወደ እግዚአብሔር መቅረቢያ መንገድ በሚል ርእስ ቃለ ወንጌል ተላልፏል። የፈለገ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት በተለይ በአብነት ትምህርቱ ላይ በዚህ ዓመት በሊቀ ጠበብት ጸጋዬ ደምሴ መምህርነት 18 ተማሪዎችን ለመዓረገ ዲቁና እንዲሁም አንድ ዲያቆን ደግሞ ለመዓረገ ቅስና እንዲበቁ በማድረግ ተተኪ ካህናትን አፍርተዋል። የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ያዘጋጀውን ሥርዓተ ትምህርት በመተግበር ግንባር ቀደም የሆነው ፈለገ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት በዘንድሮ ዓመት ከቅድመ መደበኛ እስከ 12ኛ ክፍል ከ350 በላይ የሚሆኑ ተማሪዎችን አስተምሮ አስመርቋል። በትናንትናው ዕለት በነበረው የምረቃ መርሐ ግብር ላይ በሥርዓተ ትምህርቱ ላይ ሲያስተምሩ ለነበሩ 60 መምህራን የእውቅና ሰርተፊኬት ሰጥቷል። በተጨማሪም በዓለማዊና በመንፈሳዊ ትምህርት ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን እንዲሁም በርቀት ሲማሩ የቆዩትን የማበረታቻ ሽልማት አበርክተዋል። ለሰንበት ትምህርት ቤቱ በተለያዩ መንገዶች ከፍተኛ አስተዋጽዖ ላደረጉ ምዕመናን የክብር አባል ሰርተፊኬት ተበርክቶላቸዋል። በመጨረሻም በደብሩ አስተዳዳሪ አባታዊ ቡራኬ እና ቃለ ምዕዳን ተሰጥቶ የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል። (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ለአንድ ወራት ያሠለጠናቸውን 44 ተተኪ ሰባክያነ ወንጌል ሠልጣኞችን አስመረቀ። (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) 28/11/2016 ዓ.ም በማዕ/
+4
የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ለአንድ ወራት ያሠለጠናቸውን 44 ተተኪ ሰባክያነ ወንጌል ሠልጣኞችን አስመረቀ። (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) 28/11/2016 ዓ.ም በማዕ/ጎንደር ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት አስተባባሪነት ለአንድ ወራት ያክል በዝግ ሲሰጥ የነበረው የተተኪ ሰባክያነ ወንጌል ሥልጠና የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ኅሩያን አባ ዮሴፍ ደስታ፣ የምዕራብ ጎንደር ሀ/ስብከት ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ኅሩያን አባ ኃ/ማርያም፣ የሀገረ ስብከት የመምሪያ ኃላፊዎች እንዲሁም የሰ/ት/ቤት አባላት በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተመርቀዋል። በጠቅላላ 34 ወንዶች እና 10 እኅቶች ሥልጠናውን የወሰዱ ሲሆን በዚህ ወርም ከ11 በላይ ተከታታይ ትምህርቶች እና ሥልጠናዎች ተሰጥተዋቸዋል። የምረቃ መርሐ ግብሩም በክቡር ሥራ አስኪያጁ አባታዊ መልዕክት እና የአደራ ቃል በመስጠት በታላቅ ድምቀት በዛሬው ዕለት ተከናውኗል። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት 7 በጉራጌ ሀገረ ስብከት ደግሞ 1 በጠቅላላ 8 ሰንበት ትምህርት ቤቶች በዛሬው ዕለት በሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መሠረት ያስተማሯቸውን የ12ኛ ክፍል ተማሪ
+7
በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት 7 በጉራጌ ሀገረ ስብከት ደግሞ 1 በጠቅላላ 8 ሰንበት ትምህርት ቤቶች በዛሬው ዕለት በሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መሠረት ያስተማሯቸውን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የሞዴል ፈተናን አስፈትነዋል። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

ኹለተኛው የአኅጉረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና የምርቃት መርሐ ግብር ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ተከናወነ። (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) 27/11/2016 ዓ.ም ኹለተኛው የአኅጉረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና የምርቃት መርሐ ግብር  ብፁዕ አቡነ አብርሃም በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መ/ፖ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅና የባ/ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ ብፁዕ አቡነ ቀለሚንጦስ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፤ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ የስብከተ ወንጌልና ሐዋሪያዊ ተልዕኮ መምሪያ የበላይ ሊቀ ጳጳስ፤ ብፁዕ አቡነ ኤርሚያስ የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፤ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የባሌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፤ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የማደራጃና የድርጅት ሐላፊዎች ፤ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ሐላፊዎች አባቶች ካህናት መምህራንና ተመራቂ ተማሪዎች በተገኙበት በዛሬው ዕለት በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ መሰብሰቢያ አዳራሽ ተካሒዷል። በመርሐ ግብሩም የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሐላፊ የሆኑት መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወ/ትንሣኤ የእንኳን አደረሳቹ መልዕክት  ለተማሪዎች ያስተላለፉ ሲሆን የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተ/ም/ሰብሳቢ የሆኑት ዲያቆን ስንታየሁ ምስጋናውም የሥልጠናውን ዓላማና ጠቀሜታ በአጭሩ ለታዳሚዎች ገለፃ አድርገዋል። "ለራሳችሁ አይደላችኹም ስለዚህ፥በሥጋችኹ እግዚአብሔርን አክብሩ።" 1ቆሮ 6፥20 መነሻ በማድረግ የዕለቱን ቃለ ወንጌል ብፁዕ አቡነ ማርቆስ ሰጥተዋል። በመጨረሻም ብፁዕ አቡነ አብርሃም  "ቤተ ክርስቲያን ከናንተ ብዙ ትጠብቃለች በሔዳቹበት ሁሉ አገልግሎታችሁ በትዕግስትና በፍቅር ይሁን" በማለት አባታዊ ቡራኬና መመሪያ ለተመራቂ ተማሪዎች አስተላልፈው  ለተማሪዎች የምሥክር ወረቀት ሰጥተዋል። ተመራቂ ተማረዎች መሠረተ ሃይማኖት ፣ አስተዳደር፣ ክህሎትና ሥርዓተ ት/ትን በሚመለከቱ 3 ዘርፎች ከ 20 በላይ ኮርሶችን በተከታታይ ለ20 ቀናት በቀንና በማታ መርሐ ግብር የወሰዱ ሲሆን በምርቃት መርሐ ግብራቸውም ላይ አጠቃላይ ቆይታቸውን በሪፖርት መልክ እንዲሁም ያሬዳዊ ዝማሬ አቅርበዋል። (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የሲዳማ ሀገር ሰብከት በሰንበት ት/ቤት መምሪያ ክፍል ከሀገረ ሰብከቱ የሰንበት ት/ቤት አንድነት ጉባኤ ጋር በመቀናጀት ሐምሌ 20 እና 21 ቀን 2016 ዓ.ም የ2ኛ ወሰነ ትምህርት ማጠቃለያ ፈተና በ
+4
የሲዳማ ሀገር ሰብከት በሰንበት ት/ቤት መምሪያ ክፍል ከሀገረ ሰብከቱ የሰንበት ት/ቤት አንድነት ጉባኤ ጋር በመቀናጀት ሐምሌ 20 እና 21 ቀን 2016 ዓ.ም የ2ኛ ወሰነ ትምህርት ማጠቃለያ ፈተና በ8ቱም ወረዳ በተለይ በርዕሰ  ከተማው በሀዋሳ  በሁሉም አጥብያ የ4ኛ ክፍል እና የ10ኛ ፈተና አስፈትነዋል። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የ2016ዓ.ም የሰንበት ትምህርት ቤቶች የ12ኛ ክፍል የሞዴል ፈተና የፊታችን ቅዳሜና እሑድ እንደሚሰጥ ተገለጠ። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 25/11/2016ዓ.ም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋ
የ2016ዓ.ም የሰንበት ትምህርት ቤቶች የ12ኛ ክፍል የሞዴል ፈተና የፊታችን ቅዳሜና እሑድ እንደሚሰጥ ተገለጠ። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 25/11/2016ዓ.ም   በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፖትርያርክ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ2ኛ ጊዜ የሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና የሞዴል ፈተና ለመስጠት ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ገለጠ። በሥርዓተ ትምህርቱ  መሠረት እየተማሩ 12ኛ ክፍል ለደረሱ በአዲስ አበባና ከአዲስ አበባ ውጪ ላሉ ሀገገረ ስብከቶች ሥር ለሚገኙ አጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች  ሐምሌ 27 እና 28 2016 ዓ.ም ፤ የሚሰጥ እንደሆነ የሀገር አቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ትምህርት ክፍል ሓላፊ መምህር መኩርያ ጌታቸው ገልጠዋል። አያይዘውም  የማጠቃለያ ፈተናው በተመረጡ የፈተና ጣቢያዎች ነሐሴ 18 እና 19/2016 ዓ.ም  እነደሚሰጥ  ተናግረዋል። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በሀገረ ስብከቱ ለሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሠረት የ4ኛ የ6ኛ እና የ10ኛ ክፍል የማጠቃለያ ምዘና ሰጠ። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 21/11/2016 ዓ.ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በማዕከል ደረጃ ለ4ኛ ጊዜ በሀገረ ስብከቱ ለሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሠረት የ4ኛ የ6ኛ እና የ10ኛ ክፍል የማጠቃለያ ምዘና በዛሬው ዕለት ሰጥቷል። በሀገረ ስብከቱ በ4ኛ በ6ኛ እና በ10ኛ ክፍል ሥርዓተ ትምህርቱን በሚገባ በመተግበር ላይ የሚገኙ 119 የሚሆኑ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ምዘናውን የወሰዱ ሲሆን በጠቃላላ ከ8400 በላይ ተፈታኝ ተማሪዎች በምዘናው ላይ ተቀምጠዋል። የምዘናውን ሂደት በቦሌ ሰሚት መካነ ሰላም መድኃኔዓለምና መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን የምዘና ጣቢያ ተገኝተው የጎበኙት የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ማዕምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ ከሚዲያችን ጋር በነበራቸው ቆይታ ሥርዓቱን በጠበቀ መልኩ ምዘናው እንደተሰጠ ጠቁመው ሰንበት ትምህርት ቤቶች ዋነኛ የሰው ኃይል ምንጮች እንዲሆኑ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን በመግለጽ መላው የቤተክርስቲያኒቱ ምዕመናን ልጆቻቸውን ወደ ሰንበት ትምህርት ቤቶች እንዲልኩ ፣ በሰንበት ትምህርት ቤትም እየተሰጡ ያሉ ትምህርቶች ተጠናክረው እንዲቀጠሉና ሰንበት ትምህርት ቤቶች የነገ ካህናትና የቤተ ክርስቲያን መሪዎች መፍለቂያ በመሆናቸውን ጠንክረው መሥራት እንደሚጠበቅባቸው መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። ከማጠቃለያ ምዘና በኋላም በሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ የዕውቅና መስጠት መርሐ ግብር እንደሚሰጥ ከሀገረ ስብከቱ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ያገኘነው መረጃ ያሳያል። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

"አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነ።" ሉቃ 1፡28 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! ሰናይ ሌሊት! መልካም ዕለተ ሰንበት! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነ
"አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነ።" ሉቃ 1፡28 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! ሰናይ ሌሊት! መልካም ዕለተ ሰንበት! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

"እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ!" እንኳን ለመልአኩ ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ
+1
"እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ!" እንኳን ለመልአኩ ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! መልካም በዓል! ሰናይ ሌሊት! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

ብፁዕ አቡነ አብርሃም በድጋሚ በኹለተኛው የአኅጉረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና ላይ በመገኘት አባታዊ ቡራኬና መልዕክት አስተላለፉ። (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) 18/11
+1
ብፁዕ አቡነ አብርሃም በድጋሚ በኹለተኛው የአኅጉረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና ላይ በመገኘት አባታዊ ቡራኬና መልዕክት አስተላለፉ። (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) 18/11/2016 ዓ.ም ብፁዕ አቡነ አብርሃም የኢ/ኦ/ተ/ቤ መ/ፓ/ጠ/ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት እና የሰሜን ጎጃም ሊቀ ጳጳስ በድጋሚ የአኅጉረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና ላይ በመገኘት አባታዊ ቡራኬና መልዕክት አስተላልፈዋል። ብፁዕነታቸው <<ንቁ ፥ በሃይማኖት ቁሙ ፥ ጎልምሱ ጠንክሩ። በእናንተ ዘንድ ፥ሁሉ በፍቅር ይሁን>> የሚለውን በ 1ኛ ቆሮ 16፥13 የተጠቀሰውን ቃለ ወንጌል መነሻ በማድረግ <<የእናት ቤተ ክርስቲያን አደራ አለባቹ ነቅታቹ በሃይማኖት ቁሙ ÷ ጎልምሱ ጠንክሩ ይሔንን ስታደርጉ ግን እርስ በእርሳቹ በመዋደድ በፍቅር ይሁን>> በማለት ለሰንበት ት/ቤት መምህራኑ አባታዊ ምክርና ቡራኬያቸውን ሰጥተዋል። ከተለያየ አኅጉረ ስብከት የመጡት የሰንበት ት/ቤት መምህራንም ለብፁዕ አቡነ አብርሃም በየአካባቢያቸው ስለሚስተዋለው ችግሮች ጥያቄ አቅርበው ብፁዕነታቸው ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተውባቸዋል። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok