የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
تُعد قناة የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 14 319 مشتركاً، محتلاً المرتبة 6 154 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 360 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 14 319 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 22 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 507، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 11، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 49.23%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 13.09% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 0 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 875 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 0.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
وصف القناة غير متوفر.
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 23 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.
14 319
المشتركون
+1124 ساعات
+1077 أيام
+50730 أيام
أرشيف المشاركات
"አየሁም፥ በዙፋኑም በእንስሶቹም በሽማግሌዎቹም ዙሪያ የብዙ መላእክትን ድምፅ ሰማሁ፤ ቍጥራቸውም አእላፋት ጊዜ አእላፋትና ሺህ ጊዜ ሺህ ነበር፥" ራዕ 5፡11
ኅዳር 13 በዚህች ቀን የቅዱሳን አዕላፍ መላእክት መታሰቢያ ነው። ከቅዱሳን መላእክት ረድኤት በረከት ያካፍለን። ሰናይ ሌሊት! መልካም በዓል!
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
“ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ።” ዳን 10፡13
👉🏻 #ሚካኤል ማለት መኑ ከመ አምላክ እንደ እግዚአብሔር ያለ ማነው የሚል ትርጉም አለው። ይህም እንደ እግዚአብሔር ያለ በባሕርይው ቅዱስ የሆነ ፣ እንደ እግዚአብሔር ያለ ንጹሐ ባሕርይ ፣ እንደ እግዚአብሔር ያለ ፍጹም ማነው የሚል ነው። ቅድስና ፣ ንጽሕና እና ፍጹምነት የባሕርይ ገንዘቡ የሆነ ከእግዚአብሔር በቀር የለምና።
👉🏻 ሚካኤል ፍጥረቱ በዕለተ እሑድ ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ዘፍ 1፡3 ላይ “እግዚአብሔርም ብርሃን ይሁን አለ።” ብሎ ብርሃንን በፈጠረ ጊዜ ሕልውና መላእክት ታውቋል። እንዴት ቢሉ ሰሚ በሌለበት ተናጋሪ አይናገርምና እንዲሁ ልዑል እግዚአብሔር አስቀድሞ ሰሚአን የሆኑ መላእክትን ስለፈጠረ ብርሃንን በነቢብ (በመናገር) ፈጥሯል። የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም በዛሬው ዕለት ኅዳር 12 ቀን በዓለ ሲመቱ ይታሰባል። ይህ ቅዱስ መልአክ መጋቤ ብሉይ እየተባለ ይጠራል። በብሉይ ብዙ ገቢረ ተአምራትን እየሠራ በጎላ በተረዳ አበው ነቢያትን ስለተራዳና ከእግዚአብሔር ተልኮ ድንቅ ድንቅ ሥራዎችን በማድረጉ ይህ ስያሜ ተሰጥቶታል።
👉🏻 በዘኁ 22፡21-35 ላይ የእግዚአብሔርን ሕዝብ እሥራኤል ዘሥጋን ያለአግባብ ሊራገም የወጣውና ሀብተ መርገም የተሰጠው በልአምን የተቋቋመው እሥራኤል ዘሥጋን ከእርግማን ያዳናቸው ይህ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነው።
👉🏻 ኢያ 5፡13-15 ላይ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል በጌልጌላ ለነቢዩ ኢያሱ ወልደ ነዌ ተገልጦለት ነበር። ኢያሱም የመልአኩን ማንነት ሲያረጋግጥ “ከእኛ ወገን ወይስ ከጠላቶቻችን ወገን ነህን?” አለው። መልአኩም መልሶ “እኔ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ሆኜ አሁን መጥቼአለሁ” ቢለው ኢያሱ በመልአኩ ፊት በፍርሃት ሰግዷል። “እኔና ቤቴ ግን እግዚአብሔርን እናመልካለን።” በሚለው ታላቅ የእምነት ንግግሩና ምክሩ የምናውቀው መስፍን ዝቅ ብሎ ለመልአኩ የሰገደው ስለምንድን ነው ብለን ብንጠይቅ ለቅዱሳን መላእክት የጸጋ ስግደት ስለሚገባ ነው። ቀድሞ ከሊቀ ነቢያት ሙሴ ጋር ሆኖ ሕዝቡን ሲመራ የነበረው ይህ ቅዱስ መልአክ ከኢያሱም ሳይለይ እስራኤል ዘሥጋ በጠላቶቻቸው እንዳይዋረዱ ሲረዳቸው ነበር። ዛሬም ይህ መልአክ ክርስቲያኖች በጠላት ዲያብሎስ እንዳይዋረዱ ይራዳቸዋል።
👉🏻 ዘጸ 23፡20-22 ላይ እግዚአብሔር አምላክ ለእርሱ የሚታዘዙትን ሁሉ በመንገዳቸው እየጠበቃቸውና እየተራዳቸው ወደ ርስት መንግሥተ ሰማይ መርቶ ለክብር እንዲያበቃቸው እንዲሁም አመጸኞችን ይቀጣ ዘንድ ለዚህ ቅዱስ መልአክ ክብርና ሥልጣን እንደሰጠው ይናገራል። “በመንገድህ ይጠብቅህ ዘንድ ወደ አዘጋጀሁትም ስፍራ ያገባህ ዘንድ መልአኬን በፊትህ እሰዳለው።” እንዲል። በዚህ ቃል መሠረት እግዚአብሔር በመልአኩ በቅዱስ ሚካኤል አማካኝነት እሥራኤል ዘሥጋን ከግብጽ ባርነት ወደ ምድረ ርስት ከንአን እንደሚያስገባቸው ተናግሯል። ታዲያ እሥራኤል ዘነፍሥ የሆንን እኛ ክርስቲያኖችን ደግሞ በግብጽ ከተመሰለች ሲኦል በምድረ ርስት ከንዐን ወደ ተመሰለች ገነት ርስት መንግሥተ ሰማይ በአማላጅነቱ በተራዳኢነቱ እንደ ምን አያገባን? ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በመልአኩ አማላጅነትና ተራዳኢነት ፈጣን አገልግሎቱም ርስቱን እንደምንወርስ ሲናገር “ሁሉ መዳንን ይወርሱ ዘንድ ስላላቸው ለማገዝ የሚላኩ የሚያገለግሉም መናፍስ አይደሉምን?” ብሏል። ዕብ 1፡14 እኛም ከቅዱሳን መናፍስት ወገን አንዱና አለቃቸው የሆነ ቅዱስ ሚካኤል መዳን መንግሥተ ሰማይን እንወርስ ዘንድ የሚላክ የሚያገለግል አይደለምን እንላለን። ወደ ቀደመው ነገራችን ስንመለስ ገጸ ንባቡ እንዲህ ብሎ ይቀጥላል “በፊቱ ተጠንቀቁ፥ ቃሉንም አድምጡ፤ ስሜም በእርሱ ስለ ሆነ ኃጢአት ብትሠሩ ይቅር አይልምና አታስመርሩት።” የእግዚአብሔር ስም በስሙ ላይ ላለ ለዚህ ታላቅ መልአክ የመፍረድንም ሥልጣን ከአምላካችን እንደተሰጠው ትመለከታላችሁን? ከማማለድም በላይ ኃጢአት የሚሠሩትን አመጸኞችን የመቅጣት ሥልጣንን ከእግዚአብሔር ዘንድ የተቸረው ደግ ሩህሩህ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነው። በአንጻሩ ቃሉን የሚሰሙትን እርሱን የሚያከብሩትን ደግሞ በረድኤት በበረከት ይሞላቸዋል ፣ ምድራቸውን ከበሽታ ይፈውስላቸዋል ፣ እህሉንም ውኃውንም ይባርካል ፣ ጠላቶቻቸው የሆኑ አጋንንትን ከእግራቸው በታች ይቀጠቅጥላቸዋል።
በተጨማሪም መልአሉ ቅዱስ #ሚካኤል
👉🏻 ድኅነተ ሥጋ ወነፍስ ያሰጣል። መዝ 33፡7 ፣ ዘፍ 48፡16 ፣ ዕብ 1፡14
👉🏻 ከክፉ ሁሉ ይራዳል። ዳን 10፡13 ፣ ዳን 12፡1
👉🏻 ያማልዳል ያስታርቃል። ዘካ 1፡12-13
👉🏻 ለሰው ሁሉ በጎን የሚያደርግ መልአክ ነው። ሔኖክ 6፡1-2
👉🏻 የከበረ መልአክ ነው። ከክብሩ የተነሳም ምድር ሁሉ ትበራለች። ራእ 10፡1 ፣ ራእ 18፡1
👉🏻 የትሕትና አባት ነው። ይሁ 1፡9
👉🏻 በሰዎች ድኅነት ሀሴት ደስታን የሚያደርግ ነው። ሉቃ 15፡7
👉🏻 በተጨነቅን ጊዜ የሚያበረታን የሚያረጋጋን የሚያጽናናን መልአክ ነው። ሉቃ 22፡43 ፣ ዳን 10፡20
የመልአኩ የቅዱስ ሚካኤል ረድኤቱ አማላጅነቱ ፈጣን ተራዳኢነቱ ዘወትር ከኛ ጋር ይሁን!!! መልካም በዓል!
ይቆየን።
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
"አንቺ ሱላማጢስ ሆይ፥ ተመለሽ፥ ተመለሽ!" መኃ 7:1
ሰላማጢስ ማለት ሰላማዊት የሰላም መገኛ ማለት ነው። እውነተኛዪቱ የሰላም መገኛ እናታችን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት። በባሕርይው ሰላም የሆነ ክርስቶስ ከእርሷ ተገኝቷልና ሱላማጢስ ሰላማዊት ትባላለች። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለኤፌሶን ክርስቲያኖች በላከላቸው መልእክቱ "እርሱ ሰላማችን ነው።" ብሎናል። ኤፌ 2÷14 ራሱ ጌታችንም በመዋዕለ ሥጋዌው "ሰላሜን እተውላችኋለሁ። ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም።" ዮሐ 14፡27 በማለት የሰላም ባለቤት እርሱ መሆኑን ነግሮናል። ይህ የሰላም ባለቤት የተገኘው ደግሞ ከእመቤታችን በመሆኑ እርሷም ሰላማዊት ተብላለች። "ሕፃን ተወልዶልናልና ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና አለቅነትም በጫንቃው ላይ ነው፤ ስሙም ድንቅ መካር ኃያል የዘላለም አባት የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል።" እንዲል። ኢሳ 9፡6
ሱላማጢስ የተባለች እመቤታችንን አባቷ ሰለሞን በትንቢት መነጽር የስደቷን ነገር በዘመረበት መዝሙሩ "አንቺ ሱላማጢስ ሆይ ተመለሺ" ብሏታል። ፈጣኒቱ ደመና እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የቀዳማዊቷ ሔዋንን ስደት ስደቷ አድርጋ ከልጇ ከወዳጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር በግብጽ በረሀ ለ3 ዓመት ከ6 ወር ያህል ተንከራትታለች። "ልጄን ከግብጽ ጠራሁት" ሆሴ 11፡1 የሚለው የነቢዩ የሆሴ ቃል ይፈጸም ዘንድ ከቆየችበት ከባዕድ ሀገር ግብጽ ወደ ሀገሯ ወደ ገሊላ ተመልሳለች። መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል አስቀድሞ ለዮሴፍ ወደ ግብጽ እንዲወርድ እንደነገረው ሁሉ "የሕፃኑን ነፍስ የፈለጉት ሞተዋልና ተነሣ፥ ሕፃኑን እናቱንም ይዘህ ወደ እስራኤል አገር ሂድ።" ብሎ እንዲመለስም አዝዞታል። ያን ጊዜ ሱላማጢስ እመቤታችን ከተወደደ ልጇ ጋር ወደ እስራኤል መጥታ በናዝሬት ገሊላ ኖራለች።
የእመቤታችን ከግብጽ ወደ እስራኤል መመለሷ ዛሬም በኃጢአት እና በዓለም ለተሰደድን ልጆቿ ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እና ወደ ገቢረ ጽድቅ እንድንመለስ ትልቅ ትምህርት ያስተምራል። ሰለሞን እናይሽ ዘንድ ተመለሺ እንዳላት እኛም ወደ ቅድስት እናታችን ወደ ቤተ ክርስቲያን ተመልሰን በዐይነ ልቡናችን እመቤታችንን እየተመለከትን እንድንኖር አምላካችን በቸርነቱ ይርዳን።
ይቆየን!
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
