es
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Ir al canal en Telegram

📈 Análisis del canal de Telegram የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

El canal የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 14 319 suscriptores, ocupando la posición 6 154 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 360 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 14 319 suscriptores.

Según los últimos datos del 22 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 507, y en las últimas 24 horas de 11, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 49.23%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 13.09% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 0 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 875 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 0.

📝 Descripción y política de contenido

No se ha proporcionado la descripción del canal.

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 23 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

14 319
Suscriptores
+1124 horas
+1077 días
+50730 días
Archivo de publicaciones
"አየሁም፥ በዙፋኑም በእንስሶቹም በሽማግሌዎቹም ዙሪያ የብዙ መላእክትን ድምፅ ሰማሁ፤ ቍጥራቸውም አእላፋት ጊዜ አእላፋትና ሺህ ጊዜ ሺህ ነበር፥" ራዕ 5፡11 ኅዳር 13 በዚህች ቀን የቅዱሳን አዕላፍ
"አየሁም፥ በዙፋኑም በእንስሶቹም በሽማግሌዎቹም ዙሪያ የብዙ መላእክትን ድምፅ ሰማሁ፤ ቍጥራቸውም አእላፋት ጊዜ አእላፋትና ሺህ ጊዜ ሺህ ነበር፥" ራዕ 5፡11 ኅዳር 13 በዚህች ቀን የቅዱሳን አዕላፍ መላእክት መታሰቢያ ነው። ከቅዱሳን መላእክት ረድኤት በረከት ያካፍለን። ሰናይ ሌሊት! መልካም በዓል! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

“ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ።” ዳን 10፡13 👉🏻 #ሚካኤል ማለት መኑ ከመ አምላክ እንደ እግዚአብሔር ያለ ማነው የሚል ትርጉም አለው። ይህም እንደ እግዚአብሔር ያለ በባሕርይው ቅዱስ የሆነ ፣ እንደ እግዚአብሔር ያለ ንጹሐ ባሕርይ ፣ እንደ እግዚአብሔር ያለ ፍጹም ማነው የሚል ነው። ቅድስና ፣ ንጽሕና እና ፍጹምነት የባሕርይ ገንዘቡ የሆነ ከእግዚአብሔር በቀር የለምና። 👉🏻 ሚካኤል ፍጥረቱ በዕለተ እሑድ ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ዘፍ 1፡3 ላይ “እግዚአብሔርም ብርሃን ይሁን አለ።” ብሎ ብርሃንን በፈጠረ ጊዜ ሕልውና መላእክት ታውቋል። እንዴት ቢሉ ሰሚ በሌለበት ተናጋሪ አይናገርምና እንዲሁ ልዑል እግዚአብሔር አስቀድሞ ሰሚአን የሆኑ መላእክትን ስለፈጠረ ብርሃንን በነቢብ (በመናገር) ፈጥሯል። የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም በዛሬው ዕለት ኅዳር 12 ቀን በዓለ ሲመቱ ይታሰባል። ይህ ቅዱስ መልአክ መጋቤ ብሉይ እየተባለ ይጠራል። በብሉይ ብዙ ገቢረ ተአምራትን እየሠራ በጎላ በተረዳ አበው ነቢያትን ስለተራዳና ከእግዚአብሔር ተልኮ ድንቅ ድንቅ ሥራዎችን በማድረጉ ይህ ስያሜ ተሰጥቶታል። 👉🏻 በዘኁ 22፡21-35 ላይ የእግዚአብሔርን ሕዝብ እሥራኤል ዘሥጋን ያለአግባብ ሊራገም የወጣውና ሀብተ መርገም የተሰጠው በልአምን የተቋቋመው እሥራኤል ዘሥጋን ከእርግማን ያዳናቸው ይህ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነው። 👉🏻 ኢያ 5፡13-15 ላይ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል በጌልጌላ ለነቢዩ ኢያሱ ወልደ ነዌ ተገልጦለት ነበር። ኢያሱም የመልአኩን ማንነት ሲያረጋግጥ “ከእኛ ወገን ወይስ ከጠላቶቻችን ወገን ነህን?” አለው። መልአኩም መልሶ “እኔ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ሆኜ አሁን መጥቼአለሁ” ቢለው ኢያሱ በመልአኩ ፊት በፍርሃት ሰግዷል። “እኔና ቤቴ ግን እግዚአብሔርን እናመልካለን።” በሚለው ታላቅ የእምነት ንግግሩና ምክሩ የምናውቀው መስፍን ዝቅ ብሎ ለመልአኩ የሰገደው ስለምንድን ነው ብለን ብንጠይቅ ለቅዱሳን መላእክት የጸጋ ስግደት ስለሚገባ ነው። ቀድሞ ከሊቀ ነቢያት ሙሴ ጋር ሆኖ ሕዝቡን ሲመራ የነበረው ይህ ቅዱስ መልአክ ከኢያሱም ሳይለይ እስራኤል ዘሥጋ በጠላቶቻቸው እንዳይዋረዱ ሲረዳቸው ነበር። ዛሬም ይህ መልአክ ክርስቲያኖች በጠላት ዲያብሎስ እንዳይዋረዱ ይራዳቸዋል። 👉🏻 ዘጸ 23፡20-22 ላይ እግዚአብሔር አምላክ ለእርሱ የሚታዘዙትን ሁሉ በመንገዳቸው እየጠበቃቸውና እየተራዳቸው ወደ ርስት መንግሥተ ሰማይ መርቶ ለክብር እንዲያበቃቸው እንዲሁም አመጸኞችን ይቀጣ ዘንድ ለዚህ ቅዱስ መልአክ ክብርና ሥልጣን እንደሰጠው ይናገራል። “በመንገድህ ይጠብቅህ ዘንድ ወደ አዘጋጀሁትም ስፍራ ያገባህ ዘንድ መልአኬን በፊትህ እሰዳለው።” እንዲል። በዚህ ቃል መሠረት እግዚአብሔር በመልአኩ በቅዱስ ሚካኤል አማካኝነት እሥራኤል ዘሥጋን ከግብጽ ባርነት ወደ ምድረ ርስት ከንአን እንደሚያስገባቸው ተናግሯል። ታዲያ እሥራኤል ዘነፍሥ የሆንን እኛ ክርስቲያኖችን ደግሞ በግብጽ ከተመሰለች ሲኦል በምድረ ርስት ከንዐን ወደ ተመሰለች ገነት ርስት መንግሥተ ሰማይ በአማላጅነቱ በተራዳኢነቱ እንደ ምን አያገባን? ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በመልአኩ አማላጅነትና ተራዳኢነት ፈጣን አገልግሎቱም ርስቱን እንደምንወርስ ሲናገር “ሁሉ መዳንን ይወርሱ ዘንድ ስላላቸው ለማገዝ የሚላኩ የሚያገለግሉም መናፍስ አይደሉምን?” ብሏል። ዕብ 1፡14 እኛም ከቅዱሳን መናፍስት ወገን አንዱና አለቃቸው የሆነ ቅዱስ ሚካኤል መዳን መንግሥተ ሰማይን እንወርስ ዘንድ የሚላክ የሚያገለግል አይደለምን እንላለን። ወደ ቀደመው ነገራችን ስንመለስ ገጸ ንባቡ እንዲህ ብሎ ይቀጥላል “በፊቱ ተጠንቀቁ፥ ቃሉንም አድምጡ፤ ስሜም በእርሱ ስለ ሆነ ኃጢአት ብትሠሩ ይቅር አይልምና አታስመርሩት።” የእግዚአብሔር ስም በስሙ ላይ ላለ ለዚህ ታላቅ መልአክ የመፍረድንም ሥልጣን ከአምላካችን እንደተሰጠው ትመለከታላችሁን? ከማማለድም በላይ ኃጢአት የሚሠሩትን አመጸኞችን የመቅጣት ሥልጣንን ከእግዚአብሔር ዘንድ የተቸረው ደግ ሩህሩህ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነው። በአንጻሩ ቃሉን የሚሰሙትን እርሱን የሚያከብሩትን ደግሞ በረድኤት በበረከት ይሞላቸዋል ፣ ምድራቸውን ከበሽታ ይፈውስላቸዋል ፣ እህሉንም ውኃውንም ይባርካል ፣ ጠላቶቻቸው የሆኑ አጋንንትን ከእግራቸው በታች ይቀጠቅጥላቸዋል። በተጨማሪም መልአሉ ቅዱስ #ሚካኤል 👉🏻 ድኅነተ ሥጋ ወነፍስ ያሰጣል። መዝ 33፡7 ፣ ዘፍ 48፡16 ፣ ዕብ 1፡14 👉🏻 ከክፉ ሁሉ ይራዳል። ዳን 10፡13 ፣ ዳን 12፡1 👉🏻 ያማልዳል ያስታርቃል። ዘካ 1፡12-13 👉🏻 ለሰው ሁሉ በጎን የሚያደርግ መልአክ ነው። ሔኖክ 6፡1-2 👉🏻 የከበረ መልአክ ነው። ከክብሩ የተነሳም ምድር ሁሉ ትበራለች። ራእ 10፡1 ፣ ራእ 18፡1 👉🏻 የትሕትና አባት ነው። ይሁ 1፡9 👉🏻 በሰዎች ድኅነት ሀሴት ደስታን የሚያደርግ ነው። ሉቃ 15፡7 👉🏻 በተጨነቅን ጊዜ የሚያበረታን የሚያረጋጋን የሚያጽናናን መልአክ ነው። ሉቃ 22፡43 ፣ ዳን 10፡20 የመልአኩ የቅዱስ ሚካኤል ረድኤቱ አማላጅነቱ ፈጣን ተራዳኢነቱ ዘወትር ከኛ ጋር ይሁን!!! መልካም በዓል! ይቆየን። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

ቅድስት ሐና እመ ማርያም ወላዲተ አምላክ ኅዳር 11 በዚህች ቀን አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም እናት የሆነችው ቅድስት ሐና የዕረፍት በዓል መታሰቢያ ነው። ልመናዋ ይደረግል
ቅድስት ሐና እመ ማርያም ወላዲተ አምላክ ኅዳር 11 በዚህች ቀን አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም እናት የሆነችው ቅድስት ሐና የዕረፍት በዓል መታሰቢያ ነው። ልመናዋ ይደረግልን በቅድስት ሐና ጸሎት ይማረን በረከትዋም ይደርብን! መልካም በዓል! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

"ልቤ መልካም ነገርን አፈለቀ፥ እኔ ሥራዬን ለንጉሥ እነግራለሁ፤ አንደበቴ እንደ ፈጣን ጸሓፊ ብርዕ ነው።" መዝ 44(45)፡1 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ
"ልቤ መልካም ነገርን አፈለቀ፥ እኔ ሥራዬን ለንጉሥ እነግራለሁ፤ አንደበቴ እንደ ፈጣን ጸሓፊ ብርዕ ነው።" መዝ 44(45)፡1 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በሥርዓተ ትምህርቱ መሠረት የ4ተኛ ክፍል ተግባራዊ ትምህርት

እንኳን ለቁስቋም ማርያም በሰላም አደረሳችሁ! እንኳን አደረሳችሁ! መልካም በዓል! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉
እንኳን ለቁስቋም ማርያም በሰላም አደረሳችሁ! እንኳን አደረሳችሁ! መልካም በዓል! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

"አንቺ ሱላማጢስ ሆይ፥ ተመለሽ፥ ተመለሽ!" መኃ 7:1 ሰላማጢስ ማለት ሰላማዊት የሰላም መገኛ ማለት ነው። እውነተኛዪቱ የሰላም መገኛ እናታችን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት። በባሕርይው ሰላም የሆነ ክርስቶስ ከእርሷ ተገኝቷልና ሱላማጢስ ሰላማዊት ትባላለች። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለኤፌሶን ክርስቲያኖች በላከላቸው መልእክቱ "እርሱ ሰላማችን ነው።" ብሎናል። ኤፌ 2÷14 ራሱ ጌታችንም በመዋዕለ ሥጋዌው "ሰላሜን እተውላችኋለሁ። ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም።" ዮሐ 14፡27 በማለት የሰላም ባለቤት እርሱ መሆኑን ነግሮናል። ይህ የሰላም ባለቤት የተገኘው ደግሞ ከእመቤታችን በመሆኑ እርሷም ሰላማዊት ተብላለች። "ሕፃን ተወልዶልናልና ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና አለቅነትም በጫንቃው ላይ ነው፤ ስሙም ድንቅ መካር ኃያል የዘላለም አባት የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል።" እንዲል። ኢሳ 9፡6 ሱላማጢስ የተባለች እመቤታችንን አባቷ ሰለሞን በትንቢት መነጽር የስደቷን ነገር በዘመረበት መዝሙሩ "አንቺ ሱላማጢስ ሆይ ተመለሺ" ብሏታል። ፈጣኒቱ ደመና እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የቀዳማዊቷ ሔዋንን ስደት ስደቷ አድርጋ ከልጇ ከወዳጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር በግብጽ በረሀ ለ3 ዓመት ከ6 ወር ያህል ተንከራትታለች። "ልጄን ከግብጽ ጠራሁት" ሆሴ 11፡1 የሚለው የነቢዩ የሆሴ ቃል ይፈጸም ዘንድ ከቆየችበት ከባዕድ ሀገር ግብጽ ወደ ሀገሯ ወደ ገሊላ ተመልሳለች። መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል አስቀድሞ ለዮሴፍ ወደ ግብጽ እንዲወርድ እንደነገረው ሁሉ "የሕፃኑን ነፍስ የፈለጉት ሞተዋልና ተነሣ፥ ሕፃኑን እናቱንም ይዘህ ወደ እስራኤል አገር ሂድ።" ብሎ እንዲመለስም አዝዞታል። ያን ጊዜ ሱላማጢስ እመቤታችን ከተወደደ ልጇ ጋር ወደ እስራኤል መጥታ በናዝሬት ገሊላ ኖራለች። የእመቤታችን ከግብጽ ወደ እስራኤል መመለሷ ዛሬም በኃጢአት እና በዓለም ለተሰደድን ልጆቿ ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እና ወደ ገቢረ ጽድቅ እንድንመለስ ትልቅ ትምህርት ያስተምራል። ሰለሞን እናይሽ ዘንድ ተመለሺ እንዳላት እኛም ወደ ቅድስት እናታችን ወደ ቤተ ክርስቲያን ተመልሰን በዐይነ ልቡናችን እመቤታችንን እየተመለከትን እንድንኖር አምላካችን በቸርነቱ ይርዳን። ይቆየን! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

"ልጄንም ከግብጽ ጠራሁት።" ሆሴ 11፡1 ሰናይ ማኅሌት መልካም ዕለተ ሰንበት! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Yo
"ልጄንም ከግብጽ ጠራሁት።" ሆሴ 11፡1 ሰናይ ማኅሌት መልካም ዕለተ ሰንበት! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

"ናሁ ተፈጸመ ማኅሌተ ጽጌ ፤ እነሆ የተወደደ ማኅሌተ ጽጌ ተፈጸመ።" ሰናይ ማኅሌት መልካም ዕለተ ሰንበት! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህር
"ናሁ ተፈጸመ ማኅሌተ ጽጌ ፤ እነሆ የተወደደ ማኅሌተ ጽጌ ተፈጸመ።" ሰናይ ማኅሌት መልካም ዕለተ ሰንበት! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

"የኢትዮጵያ ድንኳኖች ሲጨነቁ አየሁ፤ የምድያም አገር መጋረጃዎች ተንቀጠቀጡ።" ዕምባ 3፡7 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! (የሰንበት ትምህር
"የኢትዮጵያ ድንኳኖች ሲጨነቁ አየሁ፤ የምድያም አገር መጋረጃዎች ተንቀጠቀጡ።" ዕምባ 3፡7 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

አማኑኤል እንኳን ለቅዱስ አማኑኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! "ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል፤ እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋ
አማኑኤል እንኳን ለቅዱስ አማኑኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! "ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል፤ እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች።" ኢሣ 7፡14 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! ሰናይ ሌሊት! መልካም በዓል! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok