የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
تُعد قناة የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 14 319 مشتركاً، محتلاً المرتبة 6 154 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 360 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 14 319 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 22 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 507، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 11، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 49.23%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 13.09% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 0 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 875 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 0.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
وصف القناة غير متوفر.
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 23 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.
14 319
المشتركون
+1124 ساعات
+1077 أيام
+50730 أيام
أرشيف المشاركات
+9
የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ኅዳር 14 እና 15 ቀን 2017 ዓ.ም የዓመቱን የመጀመሪያ ጠቅላላ ጉባኤና የ3ኛ ዙር ሀገረ ስብከት አቀፍ የሰንበት የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መንፈሳዊ ተማሪዎች የምረቃ ሥነ ሥርዓት የጠቅላይ ቤተክህነት የሰንበት ት/ቤቶች ማ/መምሪያ እና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በተገኙበት በታላቅ ሥነ ሥርዓት ተከብሯል።
መረጃው የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ነው።
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
የአ/አ/ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ከልማት ጋር ተያይዞ የመኖሪያ አካባቢ ለቀዉ ወደ ሌላ አካባቢዎች የተዘዎወሩ እና የሚዘዋወሩ አባላትን መንፈሳዊ ትምህርታቸው እና አገልግሎታቸው ለማስቀጠል ውይይት ተደረገ።
(የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) ኅዳር 16/03/ 2017 ዓ/ም
የአ/አ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ኅዳር 15/2017 ዓ.ም ባደረገው ውይይት በኮሪደር ልማት ምክንያት ከየአጥቢያው የተነሱ ምእመናን እና የሰንበት ት/ቤት አባላቶቻቸው ወደ ሌሎች አካባቢዎች በመዘዋወራቸው በአጥቢያ ቤተክርስቲያኑ ብሎም በሰንበት ት/ቤቱ አባላቶቻቸው ቁጥር ማነስ እና በአገልግሎት ላይ የሚያሳድረውን እና እያመጣ ያለውን ተግዳሮት አሳሳቢ መሆኑን በውይይቱ ላይ በሰንበት ት/ቤቶቹ ተነስቷል።
በዚህም ሰንበት ት/ቤቶቹ ከአባላት ከአካባቢው መነሳት ጋር ተያይዞ ከአምስት ፐርሰንት እስከ ሰማንያ ፐርሰንት አባላቶቻቸው መቀነሳቸው እና በሥርዓተ ትምህርት እየተማሩ ከነበሩ ተማሪዎች ከአንድ አጥቢያ ከ500 በላይ ተማሪ የነበረበት ወደ 30 የመቀነስ ሁኔታዎች እንደገጠሙ በውይይቱ ተነስቷል ከዛም ባለፈ ከሳምንታዊ ጉባኤያት ወደ ወርሐዊ ጉባኤ ለመዘዋወር የተገደዱ እንዳሉ እና በቀጣይም ሙሉ በሙሉ የሕፃናት ጉባኤያት በአዲስ ሌላ ተማሪ እስኪመጣ ሊቋርጥ የሚችልበት ስጋት መኖሩን ገልጸዋል።
በልማት አገልጋዮቻቸው እና አባላቶቻቸው የተነሱባችው ሰንበት ት/ቤቶችም አሁን ያለውን የአገልግሎት ችግር ለመቅረፍ እና አባላቶቻቸው በሄዱበት አካባቢ በሚገኝ አጥቢያ አገልግሎታቸውን ለማሰቀጠል እና ከቤተክርስትያን እንዳይርቁ የሚያደርጉበትን ዋና ዋና ምክረ ሐሳቦችን ተወያይተዋል። ይህ ሁኔታ ቀጣይ ከመሆኑ አንጻር ሌሎችም ወደፊት ይህ ተግዳሮት ሲመጣ እንዴት ይለፉት ለሚለው ጥናቶች በችግሮቹ እና መፍትሔዎቻቸው ዙሪያ እንዲጠኑ ከባለድርሻ አካላት እና ከቤተክርስትያን የመዋቅር አመራር አባቶች ጋር ውይይት መደረግ እንዳለበት በጉባኤው ሐሳብ ተነስቷል
አንድነቱም ከክ/ከተማ ከሰንበት ትቤቶች አንድነት አመራሮች እና ከተነሺ እና ተቀባይ አጥቢያ ሰንበት ት/ቤት አመራሮች ጋር በመወያየት እና በማስተባበር አባላቱ ባሉበት መንፈሳዊ ትምህርታቸውን እና አገልግሎታቸውን ለማስቀጠል እንደሚሰራ እና የግንዛቤ መፍጠሪያ ውይይቶችን በቀጣይም እንደሚደረግ ተገልጿል። በማጠቃለያውም ሁሉም በጋራ በመተባበር በአጭር ጊዜ በመካከለኛ እና በረጅም ጊዜ መሠራት ያለባቸውን ጉዳዮች ጥናት ላይ ተሞርኩዞ ተግዳሮቶቹን ለመቀነስ የሚፈጠሩ እድሎችን ለማስፋት ሁሉም የበኩሉን ድርሻ ለነገ ሳይል ከዛሬ ጀምሮ በጸሎት እና በተግባር ሥራ ርብርብ እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቧል።
ዘገባው የአ/አ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት ቤቶች አንድነት ነው።
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ሰንበት ትምህርት ቤትን ከመጣንበት መንገድ ይልቅ በተሻለ መንገድ ልናደራጀውና ልንጠቀምበት ይገባል በማለት መመሪያ አስተላለፉ።
(የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) ኅዳር 15 /03/ 2017 ዓ/ም
ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የሰሜን ወሎ መንበረ ጵጵስና ሀገረ ስብከት ቤተክህነት ሊቀ ጳጳስ ሰንበት ትምህርት ቤትን በተሻለ መንገድ ማደራጀትና መጠቀም እንደሚገባ አባታዊ መመሪያ አስተላልፈዋል።
ብፁዕነታቸው ይኽን መመሪያ ያስተላለፉት የወልድያ መንበረ ንግሥት ደብረ ገሊላ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ የ2016 በጀት ዓመት የእቅድ አፈጻጸም እና የ2017 በጀት ዓመት የትግበራ እቅድ ባቀረበበት መርሐግብር ላይ ተገኝተው ቃለምእዳን ባስተላለፉበት ወቅት ነው።
ከዚኽ በፊት የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት የሚማሩበት ሥርዓተ ትምህርት ያልነበረ መኾኑን የጠቀሱት ብፁዕነታቸው፥ በአኹኑ ጊዜ ግን ሀገራችን ላይ "አሉ" የተባሉ ምሁራን የተሳተፉበት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ተዘጋጅቶ አገልግሎት ላይ የዋለ ምርሆኑንና እስከ 4ኛ ክፍል ድረስ የሚያገለግሉ የመማሪያ መጻሕፍት ታትመው መጥተዋል ብለዋል።
የሰንበት ትምህርት ቤት ልጆቻችንን ማን ያስተምር እና ምን ላይ ይማሩ የሚለውን ሰበካ ጉባኤው ከእናንተ ከምእመናን ጋር በመመካከር ያመቻቻል ያሉት ብፁዕነታቸው፥ በዋናነት ግን ወላጆች ልጆቻችሁን ተቸግራችሁ ወደ ዘመናዊ ትምህርት እንደምታስገቧቸው ኹሉ ወደ ቤተክርስቲያን መጥተው እንዲማሩ ክርስቲያናዊ ግዴታችሁን ተወጡ በማለት የአደራ መልእክት አስተላልፈዋል።
ለውጥ የሚመጣው ሰንበት ትምህርት ቤት ላይ በቊርጠኝነት ስንሠራ ነው ያሉት ብፁዕነታቸው፥ እንደ ሀገረ ስብከትም ሥርዐተ ትምህርቱ በሚገባ እንዲተገበር 5 መምህራንን ለሥልጠና ልከን በአኹኑ ሰዓት በ14ቱም ወረዳ አብያተክህነት እየተዘዋወሩ እንዲያሠለጥኑ እያደረግን ነው በማለት ገልጸዋል።
ብፁዕነታቸው፥ ሰንበት ትምህርት ቤትን በመደገፍ ልጆቻችን ለሰማይ ቤታቸው ዋስትና እንዲኖራቸው በዓላማ ወደ ሰንበት ትምህርት ቤት መላክ ይገባችኋል ሲሉም ጥሪ አስተላልፈዋል።
ሰንበት ትምህርት ቤቱ ከ2012 ዓ/ም ጀምሮ ሥርዐተ ትምህርቱ በሚያዘው መሠረት መምህራንን በመመደብ የማስተማሪያ ማኑዋል እያዘጋጀ ያስተምር እንደነበርና በ2017 ዓ/ም ደግሞ ከ1ኛ-4ኛ ክፍል የማስተማሪያ መጻሕፍት ተረክቦ ሙሉ ለሙሉ ውጤታማ ሊያደርግ በሚችል መንገድ እያስተማረ እንደሚገኝ ሰበካ ጉባኤው በሪፖርቱ አመላክቷል።
ዘገባው የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ነው።
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
+5
የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ሥር የሚገኙ የቅዱስ ማቴዎስ ምድብ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ፣ የቅዱስ ሉቃስ ምድብ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ፣ የቅዱስ ዮሃንስ ምድብ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ አካሄዱ።
(የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) ኅዳር 1 /03/ 2017 ዓ/ም
በጠቅላላ ጉባኤው ባለፋት ሦስት ዓመት በምድብ አንድነት አመራር የተከናወኑ ስራዎች ሪፓርት ቀርበው ውይይት በማድረግ በጠቅላላ ጉባኤው እንዲጸድቅ ተደርጎል። በተለይ በሥርዓተ ትምህርት ትግበራ ዙሪያ ሰፊ ውይይት በማድረግ ሥርዓተ ትምህርቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አቅጣጫ ተቀምጧል። የምድብ አንድነት ምርጫ ተወካይ የላኩ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ምርጫ እንዲደርግ እና ተወካይ ያላኩ ሰንበት ትምህርት ቤቶች በአጭር ጊዜ አንድ አንድ ተወካይ በመላክ እንዲዋዋቀር ተወስኖል።
የማቴዎስ ምድብ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ከሁለት ይከፈልልን የሚል እና ከቦታ እርቀት የተነሳ ለአገልግሎት ተቸግረና በሚል ለቀረበው የውሳኔ ሐሳብ መሰረት ዘንዘልማ ላይ የቅዱስ ማርቆስ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት እንዲቋቋም እና ከሁለት እንዲከፈል ተወስኖል። ጉባኤው ቅዱስ ማቴዎስ ምድብ አንድነት የሚመሩ ስራ አስፈጻሚዎች ምርጫ በመምረጥ ተጠናቋል።
ዘገባው የባሕረዳር ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ነው።
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
አዲሱ ሥርዓተ ትምህርትን የማስተዋወቅ ግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ ተካሄደ።
(የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) ኅዳር 13 /03/ 2017 ዓ/ም
ኤክቱስ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት በሰንበት ት/ቤት ማደራጃ መምሪያ ለሰንበት ት/ቤት ተማሪዎች የተዘጋጀውን ሥርዓተ ትምህርት ብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል በተገኙበት ለወረዳ ቤተክህነት ሠራተኞች ፣ ለአድባራት አስተዳዳሪዎች ፣ ለሰበካ ጉባኤ ም/ሊቃነ መናብርት ፣ ለሰንበት ት/ቤት ተወካዮችና የስብከተ ወንጌል ክፍል ሐላፊዎች የግንዛቤ መፍጠሪያ ሥልጠና ተካሂዷል። መርሐ ግብሩን ብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል በጸሎት አስጀምረዋል።
በሥርዓተ ትምህርትና የሰንበት ት /ቤት መዋቅራዊ ሒደትን በተመለከተ የተዘጋጀውን ሰነድ ያቀረቡት የሀገረ ስብከቱ የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ ክፍል እና የሰንበት ት/ቤት ማደራጃ ክፍል ሐላፊ መልአከ ብርሃን ቀሲስ ዳንኤል ነቢዩ ናቸው። በገለጻቸው የሥርዓተ ትምህርት ምንነት እና የሰንበት ት/ቤት አደረጃጀት ተቋማዊ መዋቅርን በተመለከተ ሥልጠናውን ሰጥተዋል።
በመጨረሻም በብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ ቃለ ምዕዳንና ጸሎተ ቡራኬ ተሰጥቶ የሥልጠናው መርሐ ግብር ተፈጽሟል። የሰንበት ት/ቤት ሥርዓተ ትምህርት ለየአድባራቱ መጽሐፍቱን የማሰራጨት ሂደትም ተከናውኗል ።
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
የወልድያ ከተማ አስተዳደር ቤተክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት አተገባበር ላይ ኹለተኛ ዙር የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሐግብር አከናወነ።
(የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) ኅዳር 13 /03/ 2017 ዓ/ም
የወልድያ ከተማ አስተዳደር ቤተክህነት ጽ/ቤት የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዐተ ትምህርት አተገባበርን አስመልክቶ ለኹለተኛ ጊዜ የግንዛቤ ማስጨበጫ እና የምክክር መርሐግብር አካሂዷል።
በግንዛቤ ማስጨበጫ መርሐግብሩ 12 የአድባራት አስተዳዳሪዎች፣ 7 የሰንበት ትምህርት ቤት አንድነት ተወካዮች፣ 7 የየሰንበት ትምህርት ቤት አመራሮች፣ 1 የማኅበረ ቅዱሳን ተወካይ፣ 8 የአድባራት የስብከተ ወንጌል ኀላፊዎች፣ 2 የወረዳው የክፍል ኀላፊዎች በአጠቃላይ 37 የሚመለከታቸው አካላት የተሳተፉ ሲኾን ሥርዓተ ትምህርቱ ውጤታማ ኾኖ ከሚሔድበት (ከሚተገበርበት) ከበጀት፣ ከሰው ኀይል፣ ከጊዜ፣ ከመዋቅር አደረጃጀትና ከመሳሰሉት አንጻር አጠቃላይ ኹኔታዎችን ትኩረት አድርጎ መሥራት እንደሚገባ በምክክር መርሐ ግብሩ የጋራ አቋም ተይዟል።
በመርሐ ግብሩ ተገኝተው የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናውን የሰጡት የሰሜን ወሎ መንበረ ጵጵስና ሀገረ ስብከት ቤተክህነት የስብከተ ወንጌልና የሰንበት ትምህርት ቤቶች ዋና ክፍል ኀላፊ መ/ር ኤርምያስ አዳነ ሲኾኑ ምክክርን የመሩት ደግሞ የከተማ አስተዳደሩ ቤተክህነት ሥራ አስኪያጅ የኾኑት መጋቤ ጥበባት አክሊለብርሃን ተመስገን ናቸው። የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ መልአከ ብርሃን ፍሥሓ ጌታነህም የማጠቃለያ መልእክት አስተላልፈዋል።
የነገዋ ቤተክርስቲያንና የነገዋ ሀገር ተረካቢ ከኾኑት መካከል የሰንበት ትምህርት ቤት ልጆች ዋነኞቹ ናቸው ያሉት ሥራ አስኪያጁ፥ ሰው ላይ መሥራት አማራጭ የሌለው መንገድ ነው በማለት የገለጹ ሲኾን በቀጣይም መመሪያ ከማስተላለፍ በላይ ሀገረ ስብከቱ የሚጠበቅበትን ድጋፍና ክትትል ኹሉ ያደርጋል ብለዋል።
መረጃው የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ነው።
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
