es
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Ir al canal en Telegram

📈 Análisis del canal de Telegram የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

El canal የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 14 309 suscriptores, ocupando la posición 6 161 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 365 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 14 309 suscriptores.

Según los últimos datos del 21 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 502, y en las últimas 24 horas de 16, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 48.88%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 13.10% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 0 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 875 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 0.

📝 Descripción y política de contenido

No se ha proporcionado la descripción del canal.

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 22 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

14 309
Suscriptores
+1624 horas
+1117 días
+50230 días
Archivo de publicaciones
“እርሱም በእውነት ክርስቶስ የዓለም መድኃኒት እንደ ሆነ እናውቃለን" ዮሐ 4፡42 ሰናይ ሌሊት! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አ
“እርሱም በእውነት ክርስቶስ የዓለም መድኃኒት እንደ ሆነ እናውቃለን" ዮሐ 4፡42 ሰናይ ሌሊት! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

“የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።” መዝ 115(116)፡15 እንኳን ለጻድቁ አቡነ ሀብተማርያም በዓለ ዕረፍት በሰላም አደረሳችሁ! መልካም በዓል! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ
“የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።” መዝ 115(116)፡15 እንኳን ለጻድቁ አቡነ ሀብተማርያም በዓለ ዕረፍት በሰላም አደረሳችሁ! መልካም በዓል! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

"ጸሎቴን በፊትህ እንደ ዕጣን ተቀበልልኝ፤ እጅ መንሳቴንም እንደ ሠርክ መሥዋዕት ትሁን።" መዝ 140(141)፡2 ሰናይ ሌሊት! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
"ጸሎቴን በፊትህ እንደ ዕጣን ተቀበልልኝ፤ እጅ መንሳቴንም እንደ ሠርክ መሥዋዕት ትሁን።" መዝ 140(141)፡2 ሰናይ ሌሊት! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

"እግዚአብሔር ጽዮንን መርጦአታልና፥ ማደሪያውም ትሆነው ዘንድ ወድዶአታልና።" መዝ 131(32)፡13 እንኳን ለጽዮን ማርያም በሰላም አደረሳችሁ! መልካም በዓል! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ
"እግዚአብሔር ጽዮንን መርጦአታልና፥ ማደሪያውም ትሆነው ዘንድ ወድዶአታልና።" መዝ 131(32)፡13 እንኳን ለጽዮን ማርያም በሰላም አደረሳችሁ! መልካም በዓል! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

"በጾምና በጸሎትም ሌሊትና ቀን እያገለገለች ከመቅደስ አትለይም ነበር።" ሉቃ 2:37 ሰናይ ሌሊት! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች
"በጾምና በጸሎትም ሌሊትና ቀን እያገለገለች ከመቅደስ አትለይም ነበር።" ሉቃ 2:37 ሰናይ ሌሊት! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ኅዳር 14 እና 15 ቀን 2017 ዓ.ም የዓመቱን የመጀመሪያ ጠቅላላ ጉባኤና የ3ኛ ዙር ሀገረ ስብከት አቀፍ የሰንበት የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ
+9
የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ኅዳር 14 እና 15 ቀን 2017 ዓ.ም የዓመቱን የመጀመሪያ ጠቅላላ ጉባኤና የ3ኛ ዙር ሀገረ ስብከት አቀፍ የሰንበት የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መንፈሳዊ ተማሪዎች የምረቃ ሥነ ሥርዓት የጠቅላይ ቤተክህነት የሰንበት ት/ቤቶች ማ/መምሪያ እና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በተገኙበት በታላቅ ሥነ ሥርዓት ተከብሯል። መረጃው የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የአ/አ/ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ከልማት ጋር ተያይዞ የመኖሪያ አካባቢ ለቀዉ ወደ ሌላ አካባቢዎች የተዘዎወሩ እና የሚዘዋወሩ  አባላትን  መንፈሳዊ ትምህርታቸው እና አገልግሎታቸው  ለማስቀጠል ውይይት ተደረገ። (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) ኅዳር 16/03/ 2017 ዓ/ም የአ/አ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ኅዳር 15/2017 ዓ.ም ባደረገው ውይይት በኮሪደር ልማት ምክንያት ከየአጥቢያው የተነሱ ምእመናን እና የሰንበት ት/ቤት አባላቶቻቸው ወደ ሌሎች አካባቢዎች በመዘዋወራቸው በአጥቢያ ቤተክርስቲያኑ ብሎም በሰንበት ት/ቤቱ  አባላቶቻቸው ቁጥር ማነስ እና በአገልግሎት ላይ የሚያሳድረውን እና እያመጣ ያለውን ተግዳሮት አሳሳቢ መሆኑን በውይይቱ ላይ  በሰንበት ት/ቤቶቹ ተነስቷል። በዚህም ሰንበት ት/ቤቶቹ ከአባላት ከአካባቢው መነሳት ጋር ተያይዞ ከአምስት ፐርሰንት እስከ ሰማንያ ፐርሰንት አባላቶቻቸው መቀነሳቸው እና በሥርዓተ ትምህርት እየተማሩ ከነበሩ ተማሪዎች ከአንድ አጥቢያ ከ500 በላይ ተማሪ የነበረበት ወደ 30 የመቀነስ ሁኔታዎች እንደገጠሙ በውይይቱ ተነስቷል ከዛም ባለፈ ከሳምንታዊ ጉባኤያት ወደ ወርሐዊ ጉባኤ ለመዘዋወር የተገደዱ እንዳሉ እና በቀጣይም ሙሉ በሙሉ የሕፃናት ጉባኤያት በአዲስ ሌላ ተማሪ  እስኪመጣ ሊቋርጥ የሚችልበት ስጋት መኖሩን ገልጸዋል። በልማት አገልጋዮቻቸው  እና አባላቶቻቸው የተነሱባችው ሰንበት ት/ቤቶችም አሁን ያለውን  የአገልግሎት  ችግር ለመቅረፍ እና አባላቶቻቸው በሄዱበት አካባቢ በሚገኝ አጥቢያ  አገልግሎታቸውን ለማሰቀጠል እና ከቤተክርስትያን እንዳይርቁ የሚያደርጉበትን ዋና ዋና ምክረ ሐሳቦችን ተወያይተዋል። ይህ ሁኔታ ቀጣይ ከመሆኑ አንጻር ሌሎችም ወደፊት ይህ ተግዳሮት ሲመጣ እንዴት ይለፉት ለሚለው ጥናቶች በችግሮቹ እና መፍትሔዎቻቸው ዙሪያ እንዲጠኑ ከባለድርሻ አካላት እና ከቤተክርስትያን የመዋቅር አመራር አባቶች ጋር ውይይት መደረግ እንዳለበት በጉባኤው ሐሳብ ተነስቷል አንድነቱም ከክ/ከተማ ከሰንበት ትቤቶች አንድነት አመራሮች እና ከተነሺ  እና ተቀባይ አጥቢያ  ሰንበት ት/ቤት አመራሮች ጋር በመወያየት እና በማስተባበር አባላቱ ባሉበት መንፈሳዊ ትምህርታቸውን እና አገልግሎታቸውን ለማስቀጠል እንደሚሰራ እና የግንዛቤ መፍጠሪያ  ውይይቶችን በቀጣይም እንደሚደረግ ተገልጿል። በማጠቃለያውም ሁሉም በጋራ በመተባበር በአጭር ጊዜ በመካከለኛ እና በረጅም ጊዜ መሠራት ያለባቸውን ጉዳዮች ጥናት ላይ ተሞርኩዞ ተግዳሮቶቹን ለመቀነስ የሚፈጠሩ እድሎችን ለማስፋት ሁሉም የበኩሉን ድርሻ ለነገ ሳይል ከዛሬ ጀምሮ በጸሎት እና በተግባር ሥራ ርብርብ እንዲያደርግ  ጥሪ ቀርቧል። ዘገባው የአ/አ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት ቤቶች አንድነት ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ሰንበት ትምህርት ቤትን ከመጣንበት መንገድ ይልቅ በተሻለ መንገድ ልናደራጀውና ልንጠቀምበት ይገባል በማለት መመሪያ አስተላለፉ። (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) ኅዳር 15 /03/ 2017 ዓ/ም ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የሰሜን ወሎ መንበረ ጵጵስና ሀገረ ስብከት ቤተክህነት ሊቀ ጳጳስ ሰንበት ትምህርት ቤትን በተሻለ መንገድ ማደራጀትና መጠቀም እንደሚገባ አባታዊ መመሪያ አስተላልፈዋል። ብፁዕነታቸው ይኽን መመሪያ ያስተላለፉት የወልድያ መንበረ ንግሥት ደብረ ገሊላ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ የ2016 በጀት ዓመት የእቅድ አፈጻጸም እና የ2017 በጀት ዓመት የትግበራ እቅድ ባቀረበበት መርሐግብር ላይ ተገኝተው ቃለምእዳን ባስተላለፉበት ወቅት ነው። ከዚኽ በፊት የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት የሚማሩበት ሥርዓተ ትምህርት ያልነበረ መኾኑን የጠቀሱት ብፁዕነታቸው፥ በአኹኑ ጊዜ ግን ሀገራችን ላይ "አሉ" የተባሉ ምሁራን የተሳተፉበት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ተዘጋጅቶ አገልግሎት ላይ የዋለ ምርሆኑንና እስከ 4ኛ ክፍል ድረስ የሚያገለግሉ የመማሪያ መጻሕፍት ታትመው መጥተዋል ብለዋል። የሰንበት ትምህርት ቤት ልጆቻችንን ማን ያስተምር እና ምን ላይ ይማሩ የሚለውን ሰበካ ጉባኤው ከእናንተ ከምእመናን ጋር በመመካከር ያመቻቻል ያሉት ብፁዕነታቸው፥ በዋናነት ግን ወላጆች ልጆቻችሁን ተቸግራችሁ ወደ ዘመናዊ ትምህርት እንደምታስገቧቸው ኹሉ ወደ ቤተክርስቲያን መጥተው እንዲማሩ ክርስቲያናዊ ግዴታችሁን ተወጡ በማለት የአደራ መልእክት አስተላልፈዋል። ለውጥ የሚመጣው ሰንበት ትምህርት ቤት ላይ በቊርጠኝነት ስንሠራ ነው ያሉት ብፁዕነታቸው፥ እንደ ሀገረ ስብከትም ሥርዐተ ትምህርቱ በሚገባ እንዲተገበር 5 መምህራንን ለሥልጠና ልከን በአኹኑ ሰዓት በ14ቱም ወረዳ አብያተክህነት እየተዘዋወሩ እንዲያሠለጥኑ እያደረግን ነው በማለት ገልጸዋል። ብፁዕነታቸው፥ ሰንበት ትምህርት ቤትን በመደገፍ ልጆቻችን ለሰማይ ቤታቸው ዋስትና እንዲኖራቸው በዓላማ ወደ ሰንበት ትምህርት ቤት መላክ ይገባችኋል ሲሉም ጥሪ አስተላልፈዋል። ሰንበት ትምህርት ቤቱ ከ2012 ዓ/ም ጀምሮ ሥርዐተ ትምህርቱ በሚያዘው መሠረት መምህራንን በመመደብ የማስተማሪያ ማኑዋል እያዘጋጀ ያስተምር እንደነበርና በ2017 ዓ/ም ደግሞ ከ1ኛ-4ኛ ክፍል የማስተማሪያ መጻሕፍት ተረክቦ ሙሉ ለሙሉ ውጤታማ ሊያደርግ በሚችል መንገድ እያስተማረ እንደሚገኝ ሰበካ ጉባኤው በሪፖርቱ አመላክቷል። ዘገባው የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ሥር የሚገኙ የቅዱስ ማቴዎስ ምድብ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ፣ የቅዱስ ሉቃስ ምድብ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ፣ የቅዱስ ዮ
+5
የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ሥር የሚገኙ የቅዱስ ማቴዎስ ምድብ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ፣ የቅዱስ ሉቃስ ምድብ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ፣ የቅዱስ ዮሃንስ ምድብ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ አካሄዱ። (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) ኅዳር 1 /03/ 2017 ዓ/ም በጠቅላላ ጉባኤው ባለፋት ሦስት ዓመት በምድብ አንድነት አመራር የተከናወኑ ስራዎች ሪፓርት ቀርበው ውይይት በማድረግ በጠቅላላ ጉባኤው እንዲጸድቅ ተደርጎል። በተለይ በሥርዓተ ትምህርት ትግበራ ዙሪያ ሰፊ ውይይት በማድረግ ሥርዓተ ትምህርቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አቅጣጫ ተቀምጧል። የምድብ አንድነት ምርጫ ተወካይ የላኩ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ምርጫ እንዲደርግ እና ተወካይ ያላኩ ሰንበት ትምህርት ቤቶች በአጭር ጊዜ አንድ አንድ ተወካይ በመላክ እንዲዋዋቀር ተወስኖል። የማቴዎስ ምድብ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ከሁለት ይከፈልልን የሚል እና ከቦታ እርቀት የተነሳ ለአገልግሎት ተቸግረና በሚል ለቀረበው የውሳኔ ሐሳብ መሰረት ዘንዘልማ ላይ የቅዱስ ማርቆስ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት እንዲቋቋም እና ከሁለት እንዲከፈል ተወስኖል። ጉባኤው ቅዱስ ማቴዎስ ምድብ አንድነት የሚመሩ ስራ አስፈጻሚዎች ምርጫ በመምረጥ ተጠናቋል። ዘገባው የባሕረዳር ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

"ጾምን ቀድሱ!" ኢዩ 1፡14 እንኳን ለጾመ ነቢያት በሰላም አደረሳችሁ! ጾሙ የዲያብሎስ ድል መንሻ የመንግሥተ ሰማያት መውረሻ ያድርግልን። መልካም ዕለተ ሰንበት! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበ
"ጾምን ቀድሱ!" ኢዩ 1፡14 እንኳን ለጾመ ነቢያት በሰላም አደረሳችሁ! ጾሙ የዲያብሎስ ድል መንሻ የመንግሥተ ሰማያት መውረሻ ያድርግልን። መልካም ዕለተ ሰንበት! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

አዲሱ ሥርዓተ ትምህርትን የማስተዋወቅ ግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ ተካሄደ። (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) ኅዳር 13 /03/ 2017 ዓ/ም ኤክቱስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት በሰንበት ት/ቤት ማደራጃ መምሪያ ለሰንበት ት/ቤት ተማሪዎች የተዘጋጀውን ሥርዓተ ትምህርት ብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል በተገኙበት ለወረዳ ቤተክህነት ሠራተኞች ፣ ለአድባራት አስተዳዳሪዎች ፣ ለሰበካ ጉባኤ ም/ሊቃነ መናብርት ፣ ለሰንበት ት/ቤት ተወካዮችና የስብከተ ወንጌል ክፍል ሐላፊዎች የግንዛቤ መፍጠሪያ ሥልጠና ተካሂዷል። መርሐ ግብሩን ብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል በጸሎት አስጀምረዋል። በሥርዓተ ትምህርትና የሰንበት ት /ቤት መዋቅራዊ ሒደትን በተመለከተ የተዘጋጀውን ሰነድ ያቀረቡት የሀገረ ስብከቱ የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ ክፍል እና የሰንበት ት/ቤት ማደራጃ ክፍል ሐላፊ መልአከ ብርሃን ቀሲስ ዳንኤል ነቢዩ ናቸው። በገለጻቸው የሥርዓተ ትምህርት ምንነት እና የሰንበት ት/ቤት አደረጃጀት ተቋማዊ መዋቅርን በተመለከተ ሥልጠናውን ሰጥተዋል። በመጨረሻም በብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ ቃለ ምዕዳንና ጸሎተ ቡራኬ ተሰጥቶ የሥልጠናው መርሐ ግብር ተፈጽሟል። የሰንበት ት/ቤት ሥርዓተ ትምህርት ለየአድባራቱ መጽሐፍቱን የማሰራጨት ሂደትም ተከናውኗል ። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

"እርሱም፦ ከእኛ ጋር ያሉት ከእነርሱ ጋር ካሉት ይበልጣሉና አትፍራ አለው።" 2ኛ ነገ 6፡16 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! (የሰንበት ትም
"እርሱም፦ ከእኛ ጋር ያሉት ከእነርሱ ጋር ካሉት ይበልጣሉና አትፍራ አለው።" 2ኛ ነገ 6፡16 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የወልድያ ከተማ አስተዳደር ቤተክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት አተገባበር ላይ ኹለተኛ ዙር የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሐግብር አከናወነ። (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) ኅዳር 13 /03/ 2017 ዓ/ም የወልድያ ከተማ አስተዳደር ቤተክህነት ጽ/ቤት የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዐተ ትምህርት አተገባበርን አስመልክቶ ለኹለተኛ ጊዜ የግንዛቤ ማስጨበጫ እና የምክክር መርሐግብር አካሂዷል። በግንዛቤ ማስጨበጫ መርሐግብሩ 12 የአድባራት አስተዳዳሪዎች፣ 7 የሰንበት ትምህርት ቤት አንድነት ተወካዮች፣ 7 የየሰንበት ትምህርት ቤት አመራሮች፣ 1 የማኅበረ ቅዱሳን ተወካይ፣ 8 የአድባራት የስብከተ ወንጌል ኀላፊዎች፣ 2 የወረዳው የክፍል ኀላፊዎች በአጠቃላይ 37 የሚመለከታቸው አካላት የተሳተፉ ሲኾን ሥርዓተ ትምህርቱ ውጤታማ ኾኖ ከሚሔድበት (ከሚተገበርበት) ከበጀት፣ ከሰው ኀይል፣ ከጊዜ፣ ከመዋቅር አደረጃጀትና ከመሳሰሉት አንጻር አጠቃላይ ኹኔታዎችን ትኩረት አድርጎ መሥራት እንደሚገባ በምክክር መርሐ ግብሩ የጋራ አቋም ተይዟል። በመርሐ ግብሩ ተገኝተው የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናውን የሰጡት የሰሜን ወሎ መንበረ ጵጵስና ሀገረ ስብከት ቤተክህነት የስብከተ ወንጌልና የሰንበት ትምህርት ቤቶች ዋና ክፍል ኀላፊ መ/ር ኤርምያስ አዳነ ሲኾኑ ምክክርን የመሩት ደግሞ የከተማ አስተዳደሩ ቤተክህነት ሥራ አስኪያጅ የኾኑት መጋቤ ጥበባት አክሊለብርሃን ተመስገን ናቸው። የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ መልአከ ብርሃን ፍሥሓ ጌታነህም የማጠቃለያ መልእክት አስተላልፈዋል። የነገዋ ቤተክርስቲያንና የነገዋ ሀገር ተረካቢ ከኾኑት መካከል የሰንበት ትምህርት ቤት ልጆች ዋነኞቹ ናቸው ያሉት ሥራ አስኪያጁ፥ ሰው ላይ መሥራት አማራጭ የሌለው መንገድ ነው በማለት የገለጹ ሲኾን በቀጣይም መመሪያ ከማስተላለፍ በላይ ሀገረ ስብከቱ የሚጠበቅበትን ድጋፍና ክትትል ኹሉ ያደርጋል ብለዋል። መረጃው የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok