uz
Feedback
ኢት-መጽሐፍት | ETHIO-BOOKS

ኢት-መጽሐፍት | ETHIO-BOOKS

Kanalga Telegram’da o‘tish

👉 "የምታነበው መጽሐፍ ለአንተ የሚያስብልህ ሳይሆን አንተ እንድታስብ የሚያደርግ ነው።" ሃርፐር ሊ Fiction (ልቦለድ), History (ታሪክ), Politics (ፖለቲካ), Psychology (ስነልቦና), Biography (ግለ-ታሪክ), Self-help(ራስ አገዝ),& Philosophy(ፍልስፍና) የሀገር ውስጥ & የውጪ ሀገር መጽሐፎችን ያገኛሉ!አስተያየትዎን እዚህ @Desutech_bot ያድርሱን

Ko'proq ko'rsatish
1 989
Obunachilar
-324 soatlar
-67 kunlar
-5630 kunlar
Postlar arxiv
የሌሊት ድምፆች እና ሌሎችም ወጎች ድርሰት - ጋሽ መስፍን ሀብተማርያም ይዘት - ወግ የመጀመሪያ ዕትም - 1992 ዓ.ም የገፅ ብዛት - 130 Join us; 👉 @et_books1 👉 @et_books1

የኢትዮ ኤርትራ ጦርነትና የፆረና ግንባር ተጋድሎ ድርሰት - ም/መቶ አለቃ የኋላወርቅ ተገኝ ይዘት - ታሪክ የመጀመሪያ ዕትም - 2004 ዓ.ም የገፅ ብዛት -300 Join us; 👉 @et_books1 👉 @et_books1

ንጉሱ ግጥም አነበበና እንዴት ነኝ¿ ብሎ ነስሩዲንን ጠየቀዉ "ምንም አትችልም። ልክ እንደ ህፃን ነህ።" ንጉሱ ተናደደና 3 ቀን አሳሰረው። በአራተኛው ቀን አሶጣውና አነበበለት...ከዛም እ አሁንስ እንዴት ነኝ? አለው። ነስሩዲን ዝም ብሎ ሄደ። ንጉሱ ተናዶ ወዴት እየሄድክ ነው? ሲለው ነስሩዲን፦ "ወደ እስር ቤት.."🚶‍♂️ Join us; 👉 @et_books1 👉 @et_books1

ፍልስፍና -1 ደራሲ - ብሩህ አለምነህ ፓለቲካዊ ፍልስፍና ዲበ- አካላዊ ፍልስፍና ማህበራዊ ፍልስፍና የስነ-ፍቅር እና የስነ-ውበት ፍልስፍናዊ ሀሳቦች በጥልቀት ይዳሰሳሉ !! Join us; 👉 @et_books1 👉 @et_books1

+3
ርዕስ:-ፍቅር እስከ መቃብር ደራሲ ፦ ሀዲስ አለማየሁ format ፦#pdf 👉 @et_books1 👉 @et_books1

ሰውን ሰው ሲቸግረው… ━━━━✦✗✦━━━━ —ዓለማየሁ ገላጋይ አንዳንዴ… …. ሰውን እንቸገራለን፤ ለህይወት አስፈላጊ እንደሆነ ቁስ ሁሉ በሰው መደህየታችን ህይወታችንን አደጋ ላይ ጥሎት እናገኛለን፡፡ እንደ ገንዘብ ዕጦት ሁሉ ሰውን “መመንዘር” ግዳችን ሆኖ ሳንችል እንቀራለን፡፡ ሰው እንራቆታለን፤ እንደ አልባሳት መጎናጸፍ እያስፈለገን በብቸኝነት መለመላነት ላይ እንወድቃለን፡፡ ማርክስ ይሄን ያለው ይሄን ተመልክቶ ሳይሆን ይቀራል? “Mans most precious treasure, his greatest wealth, is man himself” “የሰው ጌጡ እራሱ ሰው ፤ ኃብቱም” ብለን ብንተረጉመው ይበቃዋል፡፡ አንድ የጉራጌ አዛውንት ሲያጫውቱኝ ይሄን እንዳሉኝ አስታውሳለሁ፡፡ “ሰውየው ተጠየቀ አሉ፡፡ ‘ግንድ ቢወድቅብህ ይሻላል፣ ወይስ ህዝብ?’ መለሰ ሰውየው፡- ‘ግንድ ይውደቅብኝ’ ‘ለምን?’ ‘ግንድ ቢወድቅብኝ ህዝብ ያነሳልኛል፡፡ ህዝብ ቢወድቅብኝ ማን ያነሳልኛል?” ልክ ነው፤ ‘ግንድ’ ወድቆባቸው በህዝብ የተነሳላቸው ብዙ ሰዎች እናውቃለን፡፡ ህዝብ ወድቆባቸው የሚያነሳላቸው አጥተው…. …. ይቺን፤ ሰው በሰው የመሸነፉን ድክመት የተረዱ ነገስታቱ፤ ሁሉም የሚፈራው ቅጣት ከውስጡ አዋልደዋል - ግዞት፡፡ የግዞት ቅጣት ውስጥ አካባቢያዊና ማህበረሰባዊ ባዕድነት ተቀጪው ላይ ይሆናል፡፡ ህዝቡ እንዲወድቅበት “አንተ ያከበርከው ንጉስህ ላይ አምጿልና በቸልታና በማግለል ቅጣው” የሚል ትዕዛዝ ውስጥ ለውስጥ ይስለከላካል፡፡ ግዞተኛው በስሙና በማዕረጉ አይጠራም፡፡ “ውለታቢሱ” ይባላል፡፡ “ከውለታቢሱ ቤት ወዴት?” ከአንድ ወዳጄ የሰማሁት የግዞት ትርክት ባስታወስኩት ቁጥር ሀዘን የሚለቅብኝ ነው። ደጃዝማች ዓለማየሁ ይባላሉ፡፡ “ህዝብ እንዲወድቅባቸው” ተፈርዶባቸው ባይተዋርነቱ ይቆጠቁጣቸዋል፡፡ እሳቸውን ማናገር የንጉስ ትዕዛዝ እንደመናቅ ይቆጠራልና ሰው ሁሉ እርቋል፡፡ “ደጃዝማች” ቀርቶ በሌጣው “ዓለማየሁ” እንኳ የሚላቸው የለም፡፡ “ውለታቢሱ” ነው ከተጠሩም። እና ደጃዝማቹ የአካባቢውን ህፃናት ሰብስበው የልጅ ወሬ ሲያስተናግዱ ይውላሉ፡፡ ቀስ በቀስ ዋነኛ ተሳታፊ እየሆኑ፣ በልጅ ወሬ ከልጅ ጋር ሲነታረኩ ይውሉ ጀመር፡፡ እንዲሁም ብይ እየተጫወቱ፣ ብስክሊት በተራ እያሽከረከሩ፡፡ የግዞት ቁልቁለት እስከዚህ ድረስ ወርዶ ያወርዳል፡፡ የሰው ማጣት ንጣት እንዲህ ያገረጣል፡፡ …ሀዘን!! ሰውን ከሰው መነጠል እድሜ ጠገብ ቅጣት መሆኑን የሚነግረን ብዙ ነባር ታሪክ አለ፡፡ የቆሮንቶሱ ንጉስ ፔሪያንደር በልጁ (ሊከፍሮን) ላይ ይህንን አሰቃቂ ከሰው የመነጠል ፍርድ አፅንቶበት እንደነበር ታላቁ የታሪክ ሰው ሔሮዶቱስ ይነግረናል፡፡ ንጉስ ፔሪያንደር የልጆቹን እናት ይገድላል፡፡ ሁለት ልጆቹ አያቶቻቸው ጋ ለጥየቃ ሲሄዱ ይህንን የአባታቸውን ግፍ ይሰማሉ፡፡ ታላቅየው ጉዳዩን ከቁብ ሳይቆጥረው ቢቀርም ታናሹ ግን ክፉኛ አመረረ፡፡ አባቱን ማናገር ሆነ በአንድ ክፍል ውስጥ አብሮ መገኘት ሳይፈልግ ቀረ፡፡ በዚህም ንጉሱ መጀመሪያ ከቤተመንግስቱ ልጁን አባረረ፤ ቀጥሎ ማንም ሰው እንዳያስጠጋው ከለከለ፡፡ የንጉስ ልጅ በየታዛው ስር እና በየሜዳው ይተኛ ጀመር፡፡ የልጁን አለመበገር ያየው ንጉስ ቅጣቱን አጠበቀ፤ “ከልጁ ጋር ሲያወራ የተገኘ ማንኛውም ሰው ከፍተኛ የገንዘብ ቅጣት ለአፖሎ የሚከፍል ይሆናል” አለ፡፡ በአጭር ጊዜ ውስጥ ልጁ ጠወለገ፡፡ ሊሞት ደረሰ፡፡ በአራተኛው ቀን ግድም አባት ልጁን አገኘው፡፡ በአየው ነገር እጅግ አድርጎ አዘነ፡፡ “ልጄ ሆይ የትኛው ይሻላል? አሁን ያለህበት የጉስቁልና ሁናቴ ወይስ ለእኔ ለአባትህ በመታዘዝ ብቻ እኔ የምደሰትበትን ሀብትና ሥልጣን የመውረስ ተስፋ ይሻልሃል?” ሲል ጠየቀው። ልጁ አንዲት መልስ ብቻ ሰጠው፡፡ “ከእኔ ጋር በመነጋገርህ ለአፖሎ የሚከፈል መቀጫ እንዳለብህ እንዳትዘነጋ” “ንጉስ ፔሪያንደር፣ የልጁ ስቃይ የሚያስፈራና መድሃኒት የሌለው መሆኑን ተገንዝቦ፣ ከፊቱ እንዲለይለት ብቻ በመርከብ ጭኖ የግዛቱ ክፍል ወደ ሆነው ወደ ኮርሲራ ሰደደው” ይለናል ሔሮዶቱስ፡፡ ያልታደለ ልጅ፤ በአባቱ ግዛቶች ሁሉ ተፈፃሚ የሚሆነው የአባቱ አዋጅ ሰለባው ላያደርገው ይተወዋል? በአራት ቀን እንዲያ የተጎሳቆለ አርባ ቀን ሲሞላው ምን ያደርገው ይሆን? እዚህ ላይ የካርል ማርክስን አባባል ደግመን እንጥቀስና እንለፍ…`Man’s most precious treasure, his-greatest Wealth, is man himself”(“የሰው ጌጡ እራሱ ሰው ነው፤ እንዲሁም ሀብቱ!”) አፄ ቴዎድሮስ ማንም ያልመለሰው አንድ ጥያቄ ለሊቃውንቱ አቀረቡ አሉ፡፡ “ከሁሉ በላይ የሚያስደስት ጥቀሱ” ተዘረዘረ፡፡ ከልባቸው አልደረሰም፡፡ በኋላ እራሳቸው መለሱ፡፡ “የማያውቁት ሀገር ሄደው የሚያውቁት ሰው ማግኘት” ግሩም ነው፤ ይሄን ስንቅ አድርገን እንቀጥል፡፡ ታላቁ ፈላስፋ ባሩች ስፒኖዛ (1632-1677) የሞተው የሰው ዕጦት አንገላቶት ነው፡፡ በዘመኑ ከመገለልና ከመወገዝ የከፋ ስቃይ አልነበረምና፣ ጀርመናዊው ፈላስፋ ፍሬዴሪክ ኒች የስፒኖዛን ህይወት በመስቀል መሰለው። “በመስቀል ላይ የሞተው የመጨረሻው ክርስቲያን” ሲል ጠራው፡፡ በእርግጥ ቃላቸውን አንድ አድርገው በአደሙ ሰዎች መካከል መኖር የመስቀል ላይ ሞት ነው፡፡ ስፒኖዛ በገዛ ዘመዶቹ በአይሁድ ሲወገዝና ሲታደምበት ገና የ24 ዓመት ለግላጋ ነበር። በ1656 ዓ.ም የስፒኖዛ ጓደኞች ወደ አይሁድ ቤተመቅደስ አስተዳዳሪ አንድ ወሬ ይዘው ቀረቡ፡፡ ወሬው አስደንጋጭ ነበር፡፡ ስፒኖዛ በአይሁድ አምላክ ላይ ከአስተምህሮ ውጭ ተናግሯል የሚል ነው፡፡ አስጠሩት። አስተዳዳሪው የገመቱት የወጣቶቹ የሀሳብ ንትርክ እንደሆነ አድርገው ነበር፡፡ ስፒኖዛን ያውቁታል፡፡ ለአይሁድ ማኅበረሰብ መጠናከር ተስፋ የተጣለበት ነው፡፡ እናም ጠየቁት፡- “ቁስ የእግዚአብሄር አካል ሳይሆን አይቀርም ትላለህ አሉ፡፡ መላዕክታትን የቁም ቅዥት የወለዳቸው ናቸው፤ ነፍስ ከዘፈቀደ ህይወት የማታልፍ ነገር ነች ብለሃል አሉ፤ ብሉይ ኪዳንም ስለዘላለማዊለነት ያወሳበት ስፍራ የለም ትላለህ አሉ…” ስፒኖዛ አልካደም… …ጉዳዩ ስር እየሰደደ ተካረረ፡፡ የቤተመቅደሱ የበላይ ኃላፊዎች ተሰብስበው ስፒኖዛ ወደ ቀደም የይሁድ አስተሳሰብ ለመመለስ ተጣጣሩ። አልሆነም፤ ደለሉ፣ አልሆነም። ስለዚህ በዚያው አመት ላይ ስፒኖዛን አውግዘው፣ የአይሁድ ማኅበረሰብ ከዚህ ሰው ጋር ትብብር እንዳይኖረው አወጁ፡፡ ባለ ስድስት ነጥብ የማግለል ብይን ተላለፈ፡፡ ማንም አይሁድ ከስፒኖዛ ጋር እንዳይነጋገር፣ የጻፈውን እንዳያነብ፣ የሚናገረውን እንዳያዳምጥ፣ ከተወሰነ እርቀት በላይ እንዳይቀርብ፣ አንድ ጣሪያ ሥር እንዳይገኝ፣ ማንኛውም አገልግሎት እንዳይሰጥ… የስፒኖዛ ህይወት ከበደች፤ የገዛ አባቱ እንዳያናግራቸው በጣታቸው የአጥሩን ውጭ አሳዩት፡፡ እህቱ፣ አብሮ አደግ ጓደኞቹ ሁሉም አደመ፡፡ አድማው ህይወቱ አመሰቃቀለው፡፡ ይሁን እንጂ ከቅጣቱ አልራቀም፤ አላፈገፈገም። ከሀይድልበርግ ዩኒቨርስቲ የቀረበለትን የፍልስፍና መምህርነት ጥያቄ ሳይቀበል ቀረ፡፡ የተለያዩ ግለሰቦች አመታዊ ድርጎ ሊቆርጡለት ቢጥሩም አልፈልግም ሲል ውድቅ አድርጓል። እስከ ህይወቱ ፍፃሜ በብቸኝነትና ልጅ ሆኖ ከአይሁድ ማህበረሰብ በተማረው በመነጽር ስራ ተዳድሯል፡፡ ስፒኖዛ ሕዝብ ከሚወድቅበት ግንድ ቢጫንበት አልተሻለም ነበር ትላላችሁ? በስንት ጣዕሙ?! 👉 @et_books1 👉 @et_books1

የ20ኛው ክፍለ ዘመን ኢትዮጲያ 👉 @et_books1 👉 @et_books1
የ20ኛው ክፍለ ዘመን ኢትዮጲያ 👉 @et_books1 👉 @et_books1

ህይዎቴና የኢትዮጵያ ርምጃ ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ part-5 👉 @et_books1 👉 @et_books1

ህይዎቴና የኢትዮጵያ ርምጃ ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ part-4 👉 @et_books1 👉 @et_books1

ህይዎቴና የኢትዮጵያ ርምጃ ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ part-3 👉 @et_books1 👉 @et_books1

ህይዎቴና የኢትዮጵያ ርምጃ ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ part-2 👉 @et_books1 👉 @et_books1

ህይዎቴና የኢትዮጵያ ርምጃ ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ part-1 👉 @et_books1 👉 @et_books1

ኢት-መጽሐፍት | ETHIO-BOOKS - Telegram kanali @ethiobooks_21 statistikasi va tahlili