uz
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Kanalga Telegram’da o‘tish

Ko'proq ko'rsatish
1 069
Obunachilar
+224 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kunlar
+230 kunlar
Postlar arxiv
መጪውን ዘመን የዋጀ አመራር ማፍራት ወሳኝ መሆኑ ተመላከተ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ያዘጋጀው የ2017 ዓመታዊ የእቅድ አፈጻጸም እና የ2018 የእቅድ ውይይት መድረክ ላይ የአመራሩ የማስፈጸም አቅም የሚያጎለብቱ የተለያዩ ስልጠናዎች እየተሰጠ ይገኛል፡፡ ዘርፉ ለሀገር ኢኮኖሚ እድገት ያለውን ፋይዳ ታሳቢ ያደረገ፣ መጪውን ዘመን የዋጀ አመራር ማፍራት ላይ ያተኮረ ስልጠና በዘርፉ የካበተ ልምድ ባላቸው አሰልጣኞች እየተሰጠ ይገኛል፡፡ በመድረኩ ወቅቱ የሚፈልገውንና መጪውን ዘመን የዋጀ አመራር ማፍራት ወሳኝ መሆኑ ተመላክቷል፡፡ በዘርፉ የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት በትላንት እና በዛሬ ያልተወሰነ፣ መጪውን ጊዜ ገምቶ፣ ዓለም አቀፍ ነባራዊ ሁኔታ ተገንዝቦና ስትራቴጂ ነድፎ መጪውን ጊዜ አስቦ የሚሰራ አመራር ለማፍራት በትኩረት መሰራት እንዳለበት በመድረኩ ላይ ተመላክቷል፡፡ በስልጠናው የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚልን ጨምሮ ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የተጠሪ ቋማት የሥራ ኃላፊዎች፣ የክልልና የከተማ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊዎችና ምክትል ኃላፊዎች፣ የሙያ ብቃት ማዕከላት ኃላፊዎች፣ የፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲኖች እና የባለድርሻና አጋር አካላት ተወካዮች እየተሳተፉ ይገኛል፡፡ ስልጠናውን ተከትሎ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ፣ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድና የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ ይካሄዳል፡፡ ©️ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር - ኢትዮጵያ

በኮሌጁ ባለፉት ሳምንታት በትምህርትና ስልጠና ክፍሎች ላይ ሲካሄድ የቆየው ምልከታ ተጠናቀቀ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ማኔጅመንት በኮሌጁ የሚገኙ የትምህርትና ስልጠና ክፍሎች ላይ የአፈፃፀም ትግበራን በተመለከተ ሲያካሂድ የቆየውን የግምገማ መድረክ በዛሬው እለት አጠናቋል:: በምልከታ መርሃ-ግብሩ መሰረት የተቀሩ ዲፓርትመንቶችን (ማኑፋክቸሪንግ ፣ኮንስትራክሽን፣ድራፍቲንግና ሰርቬይ እንዲሁም የሆቴልና ቱሪዝም) ዲፓርትመንቶችን የአፈፃፀም ሪፖርት የተመለከተ ሲሆን በዚህም የትምህርትና ስልጠና ክፍሎቹ በ2017 ዓ.ም የትምህርትና ስልጠና ዘመን ከተቀመጠው ግብ አንፃር ያከናወኗቸውን ዝርዝር ተግባራት መመልከትም ተችሏል:: የኮሌጁ ማኔጅመንት ከትምህርትና ስልጠና ክፍሎች በተጨማሪም የኮሌጁን የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ስራ ሂደትን አመታዊ ሪፖርት ተገኝቶ የተመለከተ ሲሆን በዚህም በበጀት አመቱ የተሰሩ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎች እንዲሁም በኢንተርፕራይዞችና ኢንዱስትሪዎች ላይ የተከናወኑ ውጤታማ ተግባራትን በዋናነት ተመልክተዋል:: ምልከታ በተካሄደባቸው ክፍሎች የቀረቡት የአፈፃፀም ሪፖርቶችን መነሻ በማድረግም በማኔጅመንት አባላት ግብረ መልሶች የተሰጡ ሲሆን በተጨማሪም በኮሌጁ ዲን የቀጣይ የስራ አቅጣጫ ለትምህርትና ስልጠና ክፍሎቹ በመስጠት የምልከታ መድረኩ ተጠናቋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሐምሌ 4/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የ2017 በጀት አመት የስራ አፈጻጸም በአስተዳደሩ ድጋፋዊ ሱፐርቪዥን ቡድን ተገመገመ። በዚህም ቡድኑ በምልከታውም ቢሮው በበጀት አመቱ የተከናወኑ በርካታ ሥራዎች መመልከት የቻለ ሲሆን የተሰሩ ስራዎችን መረጃ በአግባቡ በማደራጀት እረገድም  ጥሩና ከዚህ በበለጠ እያጠናከሩ መሄድ እንደሚገባ ያስገነዘቡ ሲሆን የድጋፋዊ ክትትሉም አላማ ቢሮው በበጀት አመቱ ያከናወናቸውን ተግባራት አፈፃፀም በመገምገም ግብረ መልስ ለመስጠት ያለመ መሆኑ በመድረኩ ተገልጿል፡፡ በበጀት አመቱ ቢሮው  የተሻለ አፈጻጸም ያስመዘገበ መሆኑን በመግለጽ በቀጣይም ያሉ ጠንካራ አፈጻጸሞችን አጠናክሮ በማስቀጠል ቀልጣፋ አገልግሎትን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ማድረግ እንደሚገባ በማሳሰብ በከተማ እና በገጠር ለሚገኙ ስራ አጥ ወጣቶች ቋሚ የስራ ዕድል ለመፍጠር እንዲያስችል የግሉን ዘርፍ፣ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጋር ያለውን ቅንጅታዊ ስራ ማጠናከር እንዲሁም ኮሌጆችን በዞኒንግና ዲፈረንሼሽን ወደ ትግበራ በማስገባት ውጤታማነትን ማሳደግ እንደሚገባ ቡድኑ  አመላክቷል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሰኔ 30/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

በአስተዳደሩ ለ19ሺ ዜጎች የስራ እድል መፈጠሩ ተገለጸ በድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የበጀት፣ ኢኮኖሚ ንግድና ኢንድስትሪ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮን የ2017 በጀት አመት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ እና የመውጫ ውይይት አካሂዷል። በሪፖርቱም በበጀት አመቱ በከተማ እና በገጠር የስራ እድል ፈጠራ በግብርና በማህበራዊ እና በአገልግሎት ዘርፍ በተሰሩ ስራዎች አበረታች ለውጥ መመዝገቡ ተገልጿል። በበጀት አመቱ ለ19 ሺ ዜጎች የስራ እድል መፈጠሩ የተገለጸ ሲሆን 85 በመቶ ለወጣቶች ፣ ለሴቶች እንዲሁም አካል ጉዳተኞችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉ ተገልጿል። ቋሚ ኮሚቴው ለቢሮው የተሰጡ ግብረመልሶችን፣ በገጠር እና ከተማ የውክልና አወጣጥ መድረኮች ላይ የተነሱ የህዝብ ጥያቄዎች፣ የበጀት አመቱ መደበኛና የካፒታል ፕሮጀክቶች አፈፃፀም፣ ከክህሎት ልማትና ስራ ዕድል ፈጠራ ጋር ተያያዝነት ያላቸውን ተግባራት አፈፃፀም ያሉበትን ደረጃ፤ በዘርፉ ያሉ ተግዳሮቶች ላይ በቼክ ሊስቱ መሰረት ሰፋ ያለ ውይይት በማድረግ በአፈፃጸም ሂደት የታዩ ጠንካራ ጎኖች ተጠናክረው እንዲቀጥሉና በውስንነት የተለዩ ጉዳዮች መታረም እንዳለባቸው የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ ግብረ መልስ ሰጥቷል። ቢሮው በተለያዩ የስራ ዘርፎች የስራ እድል መፍጠሩን፣ የኮሌጆች እና ኢንድስትሪዎች ግንኙነትን ማጠናከር እንዲሁም የክህሎት መር አጫጭር ስልጠናዎች ጨምሮ በአመቱ የታቀዱ ተግባራት የተሻለ አፈፃፀም ማስመዝገቡንና በዘርፉ በውስንነት የተለዩትን እንዲታረሙ ለማድረግ የቀጣይ በጀት አመት እቅድ ውስጥ እንዲካተቱ እና ከሁሉም የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ጋር የተጀመረውን ቅንጅታዊ አሰራር አጠናክሮ በማስቀጠል በስፋትና በጥራት የክህሎት መርና የከተማና የገጠር ስራ ዕድል ፈጠራ ላይ ትኩረት ሰጥተው መስራት እንዳለባቸው የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ አይናለም ተዘራ አቅጣጫ በመስጠት የ2017 በጀት አመት የማጠቃለያ ምዕራፍ የመስክ ምልከታውን አጠናቀዋል ። ©️ DGC ሰኔ 30/2017

በስራና ክህሎት ዘርፍ ተቋማዊ አቅምን በማጎልበት ማህበረሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ስራዎችን ለማከናወን እንደሚሰራ ተገለፀ የድሬዳዋ አስተዳደረር ሥራና ክህሎት ቢሮ የ2017 በጀት አመት ዕቅድ አፈፃፀም እና 2018 በጀት አመት ረቂቅ እቅድ ላይ ለቢሮው ባለድርሻ አካላት የተዘጋጀ የውይይትና የግምገማ መድረክ ተካሂዷል። በመድረኩ የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በአዲስ ወደ ስራ ከገባ ወዲህ የሚያከናውናቸውን ስራዎች ግምገማ በማድረግ  በጥንካሬና በድክመት የተስተዋሉ ጉዳዮች ለቀጣይ አመት ግብአቶችን እንደሚሰበስብ ገልፀዋል። በዘርፉ በተልይ አራት ዋና ዋና ጉዳዮች ማለትም ከተቋም ግንባታ በአደረጃጀትና አሰራር፣ ከስራ እድል ፈጠራ አንፃር ድሬዳዋ ላይ ያለ የስራ እድል አሟጦ ከመጠቀም አንፃር፣ ከቴክኒክና ሙያ ስልጠና ጋር ከመደበኛ ቅበላ ከአጫጭር ስልጠናና ከምዘና ስርአት እንዲሁም ከአሰሪና ሰራተኛ ዘርፍ ሰራተኛ ላይ ትኩረት አድርጎ እንደሚሰራ ተናግረዋል። የቢሮው የመካከለኛ ዘመን ማለትም የ3 አመት እቅድ የቀረበ ሲሆን፣ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ዘርፍ፣ ከኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን፣ ከሙያ ብቃት ምዘና፣ ከስራ አድል ፈጠራና ኢንተር ፕራይዞች ልማት፣ ኢንዱስትሪ ሰላምና የሙያ ደህንነት ጋር በ2018 ዓ.ም እንደ እቅድ የተያዙ ዋና ዋና ጉዳዮች ተመላክተዋል። ከቀረበው ሪፖርትና እቅድ ሰነድ ባሻገር በተደረገው ሰፊ ውይይት በርካታ ሃሳቦች ተመላክተዋል። ከገጠር የስራ እድል ፈጠራ ጋር አዲስ እንደመሆኑ ዘርፉን ለማጠናከር የሚያስችሉ በርካታ ስራዎችን ማከናወን እንደሚጠይቅ ፣ ከመልካም አስተዳደር ጥናትና አፈታት እረገድ ፣ማህበራዊ አገልግሎት በቴክኒክና ሙያ የተማሪዎች ቅበላ ፣የተቋሙን ሰራተኞች አቅም ግንባታ ማጎልበት ትኩረት ማድረግ ይገባል የሚሉት ዋና ዋናዎቹ ናቸው። በ2017 ዓ.ም በአጠቃላይ  በአንፃራዊነት የተሻለ አፈፃፀም መኖሩን ነገር ግን በቀጣይ የተስተዋሉ ችግሮችን በመቅረፍ የተሻለ አፈፃፀም እንዲመዘገብ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ የቢሮ ኃላፊው አቶ ሮቤል ጌታቸው አመላክተዋል። ©️ DGC ሰኔ 28/2017

በስራና ክህሎት ዘርፍ ተቋማዊ አቅምን በማጎልበት ማህበረሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ስራዎችን ለማከናወን እንደሚሰራ ተገለፀ የድሬዳዋ አስተዳደረር ሥራና ክህሎት ቢሮ የ2017 በጀት አመት ዕቅድ አፈፃፀም እና 2018 በጀት አመት ረቂቅ እቅድ ላይ ለቢሮው ባለድርሻ አካላት የተዘጋጀ የውይይትና የግምገማ መድረክ ተካሂዷል። በመድረኩ የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቢል ጌታቸው በአዲስ ወደ ስራ ከገባ ወዲህ የሚያከናውናቸውን ስራዎች ግምገማ በማድረግ በጥንካሬና በድክመት የተስተዋሉ ጉዳዮች ለቀጣይ አመት ግብአቶችን እንደሚሰበስብ ገልፀዋል። በዘርፉ በተልይ አራት ዋና ዋና ጉዳዮች ማለትም ከተቋም ግንባታ በአደረጃጀትና አሰራር፣ ከስራ እድል ፈጠራ አንፃር ድሬዳዋ ላይ ያለ የስራ እድል አሟጦ ከመጠቀም አንፃር፣ ከቴክኒክና ሙያ ስልጠና ጋር ከመደበኛ ቅበላ ከአጫጭር ስልጠናና ከምዘና ስርአት እንዲሁም ከአሰሪና ሰራተኛ ዘርፍ ሰራተኛ ላይ ትኩረት አድርጎ እንደሚሰራ ተናግረዋል። የቢሮው የመካከለኛ ዘመን ማለትም የ3 አመት እቅድ የቀረበ ሲሆን ፣የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ዘርፍ፣ከኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን፣ ከሙያ ብቃት ምዘና፣ ከስራ አድል ፈጠራና ኢንተር ፕራይዞች ልማት፣ኢንዱስትሪ ሰላምና የሙያ ደህንነት ጋር በ2018 ዓ.ም እንደ እቅድ የተያዙ ዋና ዋና ጉዳዮች ተመላክተዋል። ከቀረበው ሪፖርትና እቅድ ሰነድ ባሻገር በተደረገው ሰፊ ውይይት በርካታ ሃሳቦች ተመላክተዋል። ከገጠር የስራ እድል ፈጠራ ጋር አዲስ እንደመሆኑ ዘርፉን ለማጠናከር የሚያስችሉ በርካታ ስራዎችን ማከናወን እንደሚጠይቅ ፣ ከመልካም አስተዳደር ጥናትና አፈታት እረገድ ፣ማህበራዊ አገልግሎት በቴክኒክና ሙያ የተማሪዎች ቅበላ ፣የተቋሙን ሰራተኞች አቅም ግንባታ ማጎልበት ትኩረት ማድረግ ይገባል የሚሉት ዋና ዋናዎቹ ናቸው። በ2017 ዓ.ም በአጠቃላይ በአንፃራዊነት የተሻለ አፈፃፀም መኖሩን ነገር ግን በቀጣይ የተስተዋሉ ችግሮችን በመቅረፍ የተሻለ አፈፃፀም እንዲመዘገብ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ የቢሮ ኃላፊው አቶ ሮቤል ጌታቸው አመላክተዋል። ©️ DGC ሰኔ 28/2017

አንድ ተቋም በሚሰጠው አገልግሎት ያለዉን ጠንካራ እና ደካማ የስራ አፈፃፀም እርስ በእርስ በመወያየት ጥንካሬን ማስቀጠል እና ደካማ አሰራርን ማሻሻል እንደሚያስፈልግ ተገለፀ። የአስተዳደሩ የሥራና ክህሎት ቢሮ የ2017 በጀት አመት የዕቅድ አፈፃፀም እና የ 2018 በጀት አመት ረቂቅ እቅድ ላይ ከተቋሙ ባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት እና የግምገማ መድረክ አካሂደዋል። ይህን የግምገማ እና የውይይት መድረክ ያስጀመሩት የቢሮው ሀላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ቢሮው በአጭር ጊዜ ውስጥ በርካታ ሰዉ ተኮር ስራዎችን መከወኑን ገልፀዋል። ኃላፊው አያይዘውም አንድ ተቋም በሚሰጠው አገልግሎት ያለዉን ጠንካራ እና ደካማ የስራ አፈፃፀም እርስ በእርስ በመወያየት ጥንካሬን ማስቀጠል እና ደካማ አሰራርን ማሻሻል ያስፈልጋል ብለዋል ። የቢሮው የ 2017 እቅድ አፈፃፀም እና የ 2018 ረቂቅ እቅድ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል :: ሪፖርቱ እና እቅዱ በተቋም ግንባታ ፤ ከስራ እድል ፈጠራ ፤ ከስልጠና እና ከአሰሪና ሰራተኛ በነዚህ በአራቱ ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ። በዚህም የተቋሙ ባለሞያዎች መሻሻል ባሉባቸው ጉዳዮች ላይ ሀሳብ እና አስተያየታቸውን ሰጥተውበታል። ከመድረኩ የተነሱ ለቀጣይ የስራ አፈፃፀም የሚጠቅሙ ግብዓቶችንም በመውስድ እና የስራ አቅጣጫ በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል ። ©️ Dire Tv-አማርኛ

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎትቢሮ የመንግስት ሰራተኞች ብልፅግና ህብረት የ2017 ዓ.ም በጀት አመት ኮንፈረንስ በደማቅ ሁኔታ ተካሄደ። በተካሄደው ኮንፈረንስ ፕሮግራም ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የህብረቱ ሰብሳቢ አቶ ሮቤል ጌታቸው እንዳሉት ህብረቱ ባለፉት 12 ወራት በርካታ የፖለቲካ ስራዎች መከናወናቸውን ገልፀው  በተለይ ደግሞ ከመንግስት ስራ አፈፃፀም ጋር በተያያዘ የተገኘው ውጤታማ አፈጻጸም በጥምረት መቅረቡ ፖለቲካው ህብረተሰቡን የሚጠቅም ተጨባጭ ስራ ለመስራት  ወሳኝ ሚና እንዲጫወት አድርጎታል ብለዋል። በኮንፈረንሱ ፕሮግራም ላይ የህብረቱ የ2017 በጀት አመት የዕቅድ ክንውን ሪፖርት፣ የቀጣይ 2018 በጀት አመት ዕቅድ፣ የኢንስፔክሽንና ስነ ምግባር ሪፖርት ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጎበት በአባላቱ በሙሉ ድምፅ የፀደቀ ሲሆን በመጨረሻም በቀጣይ የህብረቱን እና የቤተሰብ አደረጃጀትን የሚመሩ አመራሮች ምርጫን በዴሞክራሲያዊ መንገድ  በማከናወን  ፕሮግራሙ ተጠናቋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሰኔ 27/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ