1 067
订阅者
+424 小时
-27 天
+230 天
帖子存档
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የ2017 በጀት አመት የስራ አፈጻጸም በአስተዳደሩ ድጋፋዊ ሱፐርቪዥን ቡድን ተገመገመ።
በዚህም ቡድኑ በምልከታውም ቢሮው በበጀት አመቱ የተከናወኑ በርካታ ሥራዎች መመልከት የቻለ ሲሆን የተሰሩ ስራዎችን መረጃ በአግባቡ በማደራጀት እረገድም ጥሩና ከዚህ በበለጠ እያጠናከሩ መሄድ እንደሚገባ ያስገነዘቡ ሲሆን የድጋፋዊ ክትትሉም አላማ ቢሮው በበጀት አመቱ ያከናወናቸውን ተግባራት አፈፃፀም በመገምገም ግብረ መልስ ለመስጠት ያለመ መሆኑ በመድረኩ ተገልጿል፡፡
በበጀት አመቱ ቢሮው የተሻለ አፈጻጸም ያስመዘገበ መሆኑን በመግለጽ በቀጣይም ያሉ ጠንካራ አፈጻጸሞችን አጠናክሮ በማስቀጠል ቀልጣፋ አገልግሎትን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ማድረግ እንደሚገባ በማሳሰብ በከተማ እና በገጠር ለሚገኙ ስራ አጥ ወጣቶች ቋሚ የስራ ዕድል ለመፍጠር እንዲያስችል የግሉን ዘርፍ፣ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጋር ያለውን ቅንጅታዊ ስራ ማጠናከር እንዲሁም ኮሌጆችን በዞኒንግና ዲፈረንሼሽን ወደ ትግበራ በማስገባት ውጤታማነትን ማሳደግ እንደሚገባ ቡድኑ አመላክቷል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሰኔ 30/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በአስተዳደሩ ለ19ሺ ዜጎች የስራ እድል መፈጠሩ ተገለጸ
በድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የበጀት፣ ኢኮኖሚ ንግድና ኢንድስትሪ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮን የ2017 በጀት አመት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ እና የመውጫ ውይይት አካሂዷል።
በሪፖርቱም በበጀት አመቱ በከተማ እና በገጠር የስራ እድል ፈጠራ በግብርና በማህበራዊ እና በአገልግሎት ዘርፍ በተሰሩ ስራዎች አበረታች ለውጥ መመዝገቡ ተገልጿል።
በበጀት አመቱ ለ19 ሺ ዜጎች የስራ እድል መፈጠሩ የተገለጸ ሲሆን 85 በመቶ ለወጣቶች ፣ ለሴቶች እንዲሁም አካል ጉዳተኞችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉ ተገልጿል።
ቋሚ ኮሚቴው ለቢሮው የተሰጡ ግብረመልሶችን፣ በገጠር እና ከተማ የውክልና አወጣጥ መድረኮች ላይ የተነሱ የህዝብ ጥያቄዎች፣ የበጀት አመቱ መደበኛና የካፒታል ፕሮጀክቶች አፈፃፀም፣ ከክህሎት ልማትና ስራ ዕድል ፈጠራ ጋር ተያያዝነት ያላቸውን ተግባራት አፈፃፀም ያሉበትን ደረጃ፤ በዘርፉ ያሉ ተግዳሮቶች ላይ በቼክ ሊስቱ መሰረት ሰፋ ያለ ውይይት በማድረግ በአፈፃጸም ሂደት የታዩ ጠንካራ ጎኖች ተጠናክረው እንዲቀጥሉና በውስንነት የተለዩ ጉዳዮች መታረም እንዳለባቸው የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ ግብረ መልስ ሰጥቷል።
ቢሮው በተለያዩ የስራ ዘርፎች የስራ እድል መፍጠሩን፣ የኮሌጆች እና ኢንድስትሪዎች ግንኙነትን ማጠናከር እንዲሁም የክህሎት መር አጫጭር ስልጠናዎች ጨምሮ በአመቱ የታቀዱ ተግባራት የተሻለ አፈፃፀም ማስመዝገቡንና በዘርፉ በውስንነት የተለዩትን እንዲታረሙ ለማድረግ የቀጣይ በጀት አመት እቅድ ውስጥ እንዲካተቱ እና ከሁሉም የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ጋር የተጀመረውን ቅንጅታዊ አሰራር አጠናክሮ በማስቀጠል በስፋትና በጥራት የክህሎት መርና የከተማና የገጠር ስራ ዕድል ፈጠራ ላይ ትኩረት ሰጥተው መስራት እንዳለባቸው የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ አይናለም ተዘራ አቅጣጫ በመስጠት የ2017 በጀት አመት የማጠቃለያ ምዕራፍ የመስክ ምልከታውን አጠናቀዋል ።
©️ DGC ሰኔ 30/2017
በስራና ክህሎት ዘርፍ ተቋማዊ አቅምን በማጎልበት ማህበረሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ስራዎችን ለማከናወን እንደሚሰራ ተገለፀ
የድሬዳዋ አስተዳደረር ሥራና ክህሎት ቢሮ የ2017 በጀት አመት ዕቅድ አፈፃፀም እና 2018 በጀት አመት ረቂቅ እቅድ ላይ ለቢሮው ባለድርሻ አካላት የተዘጋጀ የውይይትና የግምገማ መድረክ ተካሂዷል።
በመድረኩ የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በአዲስ ወደ ስራ ከገባ ወዲህ የሚያከናውናቸውን ስራዎች ግምገማ በማድረግ በጥንካሬና በድክመት የተስተዋሉ ጉዳዮች ለቀጣይ አመት ግብአቶችን እንደሚሰበስብ ገልፀዋል።
በዘርፉ በተልይ አራት ዋና ዋና ጉዳዮች ማለትም ከተቋም ግንባታ በአደረጃጀትና አሰራር፣ ከስራ እድል ፈጠራ አንፃር ድሬዳዋ ላይ ያለ የስራ እድል አሟጦ ከመጠቀም አንፃር፣ ከቴክኒክና ሙያ ስልጠና ጋር ከመደበኛ ቅበላ ከአጫጭር ስልጠናና ከምዘና ስርአት እንዲሁም ከአሰሪና ሰራተኛ ዘርፍ ሰራተኛ ላይ ትኩረት አድርጎ እንደሚሰራ ተናግረዋል።
የቢሮው የመካከለኛ ዘመን ማለትም የ3 አመት እቅድ የቀረበ ሲሆን፣ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ዘርፍ፣ ከኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን፣ ከሙያ ብቃት ምዘና፣ ከስራ አድል ፈጠራና ኢንተር ፕራይዞች ልማት፣ ኢንዱስትሪ ሰላምና የሙያ ደህንነት ጋር በ2018 ዓ.ም እንደ እቅድ የተያዙ ዋና ዋና ጉዳዮች ተመላክተዋል።
ከቀረበው ሪፖርትና እቅድ ሰነድ ባሻገር በተደረገው ሰፊ ውይይት በርካታ ሃሳቦች ተመላክተዋል። ከገጠር የስራ እድል ፈጠራ ጋር አዲስ እንደመሆኑ ዘርፉን ለማጠናከር የሚያስችሉ በርካታ ስራዎችን ማከናወን እንደሚጠይቅ ፣ ከመልካም አስተዳደር ጥናትና አፈታት እረገድ ፣ማህበራዊ አገልግሎት በቴክኒክና ሙያ የተማሪዎች ቅበላ ፣የተቋሙን ሰራተኞች አቅም ግንባታ ማጎልበት ትኩረት ማድረግ ይገባል የሚሉት ዋና ዋናዎቹ ናቸው።
በ2017 ዓ.ም በአጠቃላይ በአንፃራዊነት የተሻለ አፈፃፀም መኖሩን ነገር ግን በቀጣይ የተስተዋሉ ችግሮችን በመቅረፍ የተሻለ አፈፃፀም እንዲመዘገብ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ የቢሮ ኃላፊው አቶ ሮቤል ጌታቸው አመላክተዋል።
©️ DGC ሰኔ 28/2017
በስራና ክህሎት ዘርፍ ተቋማዊ አቅምን በማጎልበት ማህበረሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ስራዎችን ለማከናወን እንደሚሰራ ተገለፀ
የድሬዳዋ አስተዳደረር ሥራና ክህሎት ቢሮ የ2017 በጀት አመት ዕቅድ አፈፃፀም እና 2018 በጀት አመት ረቂቅ እቅድ ላይ ለቢሮው ባለድርሻ አካላት የተዘጋጀ የውይይትና የግምገማ መድረክ ተካሂዷል።
በመድረኩ የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቢል ጌታቸው በአዲስ ወደ ስራ ከገባ ወዲህ የሚያከናውናቸውን ስራዎች ግምገማ በማድረግ በጥንካሬና በድክመት የተስተዋሉ ጉዳዮች ለቀጣይ አመት ግብአቶችን እንደሚሰበስብ ገልፀዋል።
በዘርፉ በተልይ አራት ዋና ዋና ጉዳዮች ማለትም ከተቋም ግንባታ በአደረጃጀትና አሰራር፣ ከስራ እድል ፈጠራ አንፃር ድሬዳዋ ላይ ያለ የስራ እድል አሟጦ ከመጠቀም አንፃር፣ ከቴክኒክና ሙያ ስልጠና ጋር ከመደበኛ ቅበላ ከአጫጭር ስልጠናና ከምዘና ስርአት እንዲሁም ከአሰሪና ሰራተኛ ዘርፍ ሰራተኛ ላይ ትኩረት አድርጎ እንደሚሰራ ተናግረዋል።
የቢሮው የመካከለኛ ዘመን ማለትም የ3 አመት እቅድ የቀረበ ሲሆን ፣የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ዘርፍ፣ከኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን፣ ከሙያ ብቃት ምዘና፣
ከስራ አድል ፈጠራና ኢንተር ፕራይዞች ልማት፣ኢንዱስትሪ ሰላምና የሙያ ደህንነት ጋር በ2018 ዓ.ም እንደ እቅድ የተያዙ ዋና ዋና ጉዳዮች ተመላክተዋል።
ከቀረበው ሪፖርትና እቅድ ሰነድ ባሻገር በተደረገው ሰፊ ውይይት በርካታ ሃሳቦች ተመላክተዋል። ከገጠር የስራ እድል ፈጠራ ጋር አዲስ እንደመሆኑ ዘርፉን ለማጠናከር የሚያስችሉ በርካታ ስራዎችን ማከናወን እንደሚጠይቅ ፣ ከመልካም አስተዳደር ጥናትና አፈታት እረገድ ፣ማህበራዊ አገልግሎት በቴክኒክና ሙያ የተማሪዎች ቅበላ ፣የተቋሙን ሰራተኞች አቅም ግንባታ ማጎልበት ትኩረት ማድረግ ይገባል የሚሉት ዋና ዋናዎቹ ናቸው።
በ2017 ዓ.ም በአጠቃላይ በአንፃራዊነት የተሻለ አፈፃፀም መኖሩን ነገር ግን በቀጣይ የተስተዋሉ ችግሮችን በመቅረፍ የተሻለ አፈፃፀም እንዲመዘገብ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ የቢሮ ኃላፊው አቶ ሮቤል ጌታቸው አመላክተዋል።
©️ DGC ሰኔ 28/2017
አንድ ተቋም በሚሰጠው አገልግሎት ያለዉን ጠንካራ እና ደካማ የስራ አፈፃፀም እርስ በእርስ በመወያየት ጥንካሬን ማስቀጠል እና ደካማ አሰራርን ማሻሻል እንደሚያስፈልግ ተገለፀ።
የአስተዳደሩ የሥራና ክህሎት ቢሮ የ2017 በጀት አመት የዕቅድ አፈፃፀም እና የ 2018 በጀት አመት ረቂቅ እቅድ ላይ ከተቋሙ ባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት እና የግምገማ መድረክ አካሂደዋል።
ይህን የግምገማ እና የውይይት መድረክ ያስጀመሩት የቢሮው ሀላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ቢሮው በአጭር ጊዜ ውስጥ በርካታ ሰዉ ተኮር ስራዎችን መከወኑን ገልፀዋል።
ኃላፊው አያይዘውም አንድ ተቋም በሚሰጠው አገልግሎት ያለዉን ጠንካራ እና ደካማ የስራ አፈፃፀም እርስ በእርስ በመወያየት ጥንካሬን ማስቀጠል እና ደካማ አሰራርን ማሻሻል ያስፈልጋል ብለዋል ።
የቢሮው የ 2017 እቅድ አፈፃፀም እና የ 2018 ረቂቅ እቅድ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል :: ሪፖርቱ እና እቅዱ በተቋም ግንባታ ፤ ከስራ እድል ፈጠራ ፤ ከስልጠና እና ከአሰሪና ሰራተኛ በነዚህ በአራቱ ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ።
በዚህም የተቋሙ ባለሞያዎች መሻሻል ባሉባቸው ጉዳዮች ላይ ሀሳብ እና አስተያየታቸውን ሰጥተውበታል።
ከመድረኩ የተነሱ ለቀጣይ የስራ አፈፃፀም የሚጠቅሙ ግብዓቶችንም በመውስድ እና የስራ አቅጣጫ በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል ።
©️ Dire Tv-አማርኛ
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎትቢሮ የመንግስት ሰራተኞች ብልፅግና ህብረት የ2017 ዓ.ም በጀት አመት ኮንፈረንስ በደማቅ ሁኔታ ተካሄደ።
በተካሄደው ኮንፈረንስ ፕሮግራም ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የህብረቱ ሰብሳቢ አቶ ሮቤል ጌታቸው እንዳሉት ህብረቱ ባለፉት 12 ወራት በርካታ የፖለቲካ ስራዎች መከናወናቸውን ገልፀው በተለይ ደግሞ ከመንግስት ስራ አፈፃፀም ጋር በተያያዘ የተገኘው ውጤታማ አፈጻጸም በጥምረት መቅረቡ ፖለቲካው ህብረተሰቡን የሚጠቅም ተጨባጭ ስራ ለመስራት ወሳኝ ሚና እንዲጫወት አድርጎታል ብለዋል።
በኮንፈረንሱ ፕሮግራም ላይ የህብረቱ የ2017 በጀት አመት የዕቅድ ክንውን ሪፖርት፣ የቀጣይ 2018 በጀት አመት ዕቅድ፣ የኢንስፔክሽንና ስነ ምግባር ሪፖርት ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጎበት በአባላቱ በሙሉ ድምፅ የፀደቀ ሲሆን በመጨረሻም በቀጣይ የህብረቱን እና የቤተሰብ አደረጃጀትን የሚመሩ አመራሮች ምርጫን በዴሞክራሲያዊ መንገድ በማከናወን ፕሮግራሙ ተጠናቋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሰኔ 27/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬደዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የ2017 የሥራና ክህሎት ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ተካሄደ።
የድሬዳዋ አስተዳደር ካቢኔ የሥራና ክህሎት ምክር ቤትን ለማቋቋም ባወጣው መመሪያ ቁጥር 32/2014 መሠረት የተለያዩ የመንግስት አስፈጻሚ ተቋማት አባል የሆኑበትና በክቡር ከንቲባ ከድር ጁሃር የሚመራ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ምክር ቤት ተመስርቶ ወደ ስራ መግባቱ ይታወቃል፤ 54 አባላት ያሉት ይህ ምክር ቤት የአስተዳደሩን አስፈጻሚና ባለድርሻ አካላት በማቀናጀት ለዜጎች ሊፈጠሩ የሚችሉ የስራ እድሎችን አሟጦ ከመጠቀም እንፃር የተሰሩ ስራዎችን የሚገመግም ሲሆን በ2017 በጀት አመት የተከናወኑ ስራዎችን በጥልቅ በመፈተሽ ገምግሟል።
በዚህም የምክርቤት ጉባኤ ላይ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የብልጽግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ክቡር አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ እንደገለጹት አስተዳደሩ ትኩረት ከሰጣቸው ጉዳዮች መካከል 'የስራ ዕድል ፈጠራ' ዋነኛው መሆኑንና ይህ ዘርፍ ትርጉም ያለው ተጨባጭ ውጤት እንዲያስገኝ ለማስቻል፤ ምክር ቤቱ የዘርፉን ተግባራዊ ክንውኖች በመከታተል፣ አፈፃፀሙን በመገምገምና ድጋፍ በማድረግ፤ ለስኬታችን ጉልህ አስተዋፅኦ እንዲያበረክት አጠናክሮ መቀጠል ይገባል ብለዋል፡፡
በድሬዳዋ አስተዳደር ደረጃ የስራ ዕድል ፈጠራና የቴክኒክና ሙያ የሰው ሃይል ልማት ስራን የአስፈጻሚና ባለድርሻ አካላትን ተሳትፎና ቅንጅት ባረጋገጠ መልኩ እንዲመራ ለማድረግ አዲስ የአደረጃጀትና የአሰራር ስርዓት መከተል አስፈላጊ በመሆኑ ምክር ቤቱ መመስረቱን አስታውሰው የስራ ዕድል ፈጠራ ስራዎችን ጊዜና ሀብትን በሚቆጥብ አግባብ በአንድ መዋቅር ለመምራትና ለማስፈጸም የአስፈጻሚ አካላትን እና በፈጻሚ አካላት መካከል ቅንጅታዊና ቀልጣፋና ውጤታማ የመረጃ ልውውጥ እንዲኖር ያስቻለ መሆኑን የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ተናግረዋል።
በተቋማት መካከል ቅንጅታዊ አሰራር፣ የማምረቻና የመሸጫ ቦታ፣ የፋይናንስ አቅርቦት፣ የቤተሰብ ንግድ ፅንሰ ሃሳብ አለማደግ፣ የሚፈጠሩ የስራ እድል ፈጠራዎች ክህሎት መር መሆናቸውን ከማረጋገጥ አንጻር፣ የስራ ባህል ደካማ መሆን በዘርፉ እንደ ችግር የተነሱ ጉዳዮች ሲሆኑ፣ የመረጃ ቅብብሎሽን ማዘመን፣ ቅንጅታዊ አሰራርን ማጠናከር፣ የሚሰጡ ድጋፎቸን ማጠናከር፣ ማምረቻና የመሸጫ ቦታን ጉዳይ ልዩ ትኩረት በመስጠት በዘርፉ የሚዳሰስ ለውጥ ለማምጣት መስራት እንደሚገባ አቅጣጫ ተቀምጧል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሰኔ 27/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 42ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ካነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች...
👉ግብርና የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ዋልታ ነው በርካታ የኢትዮጵያ ህዝብ የሚሳተፍበት ሴክተር ነው፤ በአንድ ዘርፍ ላይ ጥገኛ የሆነ ኢኮኖሚ ስለማያዋጣ ብዝኃ ዘርፍ እና ብዝኃ ተዋናይ በማድረግ ብዙ ጥቅም ለማግኘት ነው በግልፅ መንገድ ሪፎርም የጀመርነው፡፡
👉ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ አለባት፤ አምርታ መብላት የማትችል ሀገር ብሔራዊ ጥቋሟን ለማስጠበቅ ትቸገራለች፡፡
👉ባለፉት ጥቂት ዓመታት በኢትዮጵያ 27 ሚሊየን ገደማ ሰዎች በሴፍቲኔት የታቀፉ ተረጂዎች ነበሩ፤ ኢትዮጵያ መለመን የለባትም ልጆቿ ተግተው፤ ሰርተው ከልመና ራሳቸውን መገላገል አለባቸው የሚለው ዕምነት ፍሬ አፍርቷል፡፡
👉ዘንድሮ 23 ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ከሴፍቲኔት ተረጂነት መውጣት ችለዋል፤ ኢትዮጵያ ሙሉ በመሉ ከሴፍቲኔት እና ከተረጂነት የተላቀቀች ሀገር እንድትሆን ከሁላችንም ብዙ ስራዎች ይጠበቃሉ፡፡
👉23 ሚሊየን የሴፍትኔት ተረጂዎችን ማላቀቅ ተችሏል፣ ቀሪ 4 ሚሊየን በላይ ተረጂዎችን ከእርዳታ ለማላቀቅ እና ወደ አምራችነት ለማሸጋገር በትኩረት ይሰራል፡፡
👉ባለፈው ዓመት 26 ሚሊየን ሄክታር መሬት ታርሶ ነበር፤ በዚህኛው ዓመት ደግሞ 31 ነጥብ 8 ሚሊየን ሄክታር መሬት ማረስ ተችሏል፤ ኢትዮጵያ ባፈው ዓመት በሁሉም ዓይነት የሰብል ምርቶች 1 ነጥብ 2 ቢሊየን ኩንታል ምርት ነው የሰበሰበችው፣ ዘንድሮ 1 ነጥብ 5 ቢሊየን ኩንታል መሰብሰብ ተችሏል፡፡
👉በዚህ ዓመት እስከ መስከረም ባለው ጊዜ ውስጥ ስድስት ከፍተኛ ግድቦች ይመረቃሉ፡፡
👉በዓመት ሁለት እና ሶስት ጊዜ የማምረት ልምምዳችን የጨመረ ሲሆን፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ብለን የጀመርነው ሥራ በርካት ለውጦችን ማምጣት ችሏል፡፡
👉የሌማት ትሩፋት ብለን በጀመርነው ሥራ የወተት እና የእንቁላል ምርቶችን ማሳደግ ችለናል፡፡
👉ምርታማነት እያደገ ሲሆን ከውጭ የምናስገባቸውን ምርቶች መተካት ችለናል ይህንን አጠናክረን ከቀጠለን በብዙ ዘርፍ ውጤታም ልንሆን እንችላለን፡፡
👉የግብርናው ዘርፍ ትልቅ ትኩረት ያገኘ እና ትልቅ ውጤት ያመጣ ነው፤ ለአጠቃላይ ዕድገታችን ከፍተኛ ድርሻ አለው፡፡
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያነሷቸው ጥያቄዎች፡-
🔘ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያላትን አሁናዊ ግንኙነት እና ትብብር እንዴት ይገልጹታል፣ በተለይም ከኤርትራ ጋር ባለው አሁናዊ ሁኔታ ላይ ማብራሪያ ቢሰጡ፤
🔘 የኢትዮጵያን የባሕር በር ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በሰላማዊ፣ በሕጋዊና ዲፕሎማሲያዊ መንግድ የተጀመረው ጥረት ምን ደረጃ ላይ ይገኛል? ጎረቤት ሀገራት፣ ወዳጅ ሀገራት፣ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እና ዲፕሎማቶች የጥያቄውን ፍትሃዊነት ተረድተው ድጋፍ እንዲያደርጉ የተከናወኑ ጥረቶች ላይ ማብራሪያ ቢሰጥ፤
🔘 በሰው ሰራሽ እና በተፈጥሮ ችግሮች ሳቢያ ከትምህር ገበታ ውጪ የሆኑ ተማሪዎችን ትምህርት ለማስጀመር ምን እየተሰራ ነው?
🔘 የትምህርት ጥራት ስብራትን በዘላቂነት ለመጠገን ለመምህራን ልማት ሥራ ትኩረት መደረጉ ይታወቃል፤ አሁን ላይ በጉዳዩ ላይ እየተሰሩ የሚገኙ ሥራዎችን በተመለከተ ማብራሪያ ቢሰጥ።
🔘 በታችኛው የመንግስት መዋቅር ሙስናና ብልሹ አሰራር ሕዝቡን እያማረረ እንደሚገኝ በተደጋጋሚ ቅሬታዎች ይቀርባሉ፤ ሙስና የልማት ጠንቅ ወደ ማይሆንበት ደረጃ ለማድረስ እየተሰሩ ያሉ ሥራዎች፣ የተገኙ ውጤቶችና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ማብራሪያ ቢሰጥ፤
🔘 ሀገራዊ የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም ስኬታማ እንዲሆን እና የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ እንዲሻሻል እየተከናወኑ የሚገኙ ሥራዎች እና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ገለጻ ቢያደርጉ፤
🔘 የኮሪደር ልማትን ሥራ አፈጻጸም ያለበት ደረጃ፣ በአፈጻጸሙ ተገቢ ያልሆነ ጥፋት እንዳይፈጸም እንዲሁም ሥራውን የሚያጠለሹ እና ዘመቻ የከፈቱ አካላትን አስመልክተው ማብራሪያ ቢሰጡ፤
🔘 ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ግብር በተገቢ ሁኔታ ለመሰብሰበ እና በሒደቱ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል ምን እየተሰራ ነው።
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
