Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
Kanalga Telegram’da o‘tish
Ko'proq ko'rsatish
1 063
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
-77 kunlar
+230 kunlar
Postlar arxiv
🇪🇹የሰንደቅ ዓላማ ቀን🇪🇹
18ኛው የሰንደቅ ዓላማ ቀን “ሰንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ” በሚል መሪ ሃሳብ ዛሬ ይከበራል።
በኢፌዲሪ ሕገ መንግስት መሰረት የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ቀለማት እና በሰንደቅ ዓላው መሀል ላይ የሚገኘው ዓርማ ትርጉም ምንድን ነው?
👉አረንጓዴው
• ሥራ፣ የልምላሜና የዕድገት ምልክት ነው፡፡
👉ቢጫው
• የተስፋ፣ የፍትሕና የእኩልነት ምልክት ነው፡፡
👉ቀዩ
• ለነፃነትና ለእኩልነት መስፈን የሚደረግ የመስዋዕትነትና የጀግንነት ምልክት ነው፡፡
እንዲሁም በሰንደቅ ዓላማው መሀል ላይ የሚገኘው ዓርማ ትርጉም :-
👉ክብ የሆነው፡- ሰማያዊ መደብ ሰላምን ያመለክታል፡፡
👉ቀጥታና እኩል የሆኑት መስመሮች፡- የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች እንዲሁም የሐይማኖቶችን እኩልነት ያመለክታሉ፡፡
👉ቀጥታና እኩል ከሆኑት መስመሮች የተዋቀረው ኮከብ፡- የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በመፈቃቀድ የመሠረቱትን አንድነት ያመላክታል፡፡
👉ቢጫ ጨረሩ ደግሞ ፡- በመፈቃቀድ አንድነት ለመሰረቱት ብሔር፣ ብሔረሰቦች የፈነጠቀውን ብሩህ ተስፋ ይጠቁማል፡፡
ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጲያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጲያ ሕዳሴ!
+4
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሦስተኛ ዙር ብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ አምስተኛ ዙር የአቻ ለአቻ ውይይት ተካሄደ።
#ዜና /"የቴክኒክ እና ሙያ ኮሌጆች ለወጣቶች አዳዲስ እና በገበያው ላይ ተፈላጊ የሆኑ የሙያ ዘርፎችን በማሰልጠን ወጣቶችን የሙያ ባለቤት እያረጉ ይገኛሉ"- የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር
#DGC ጥቅምት 1/2018
የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠኑአቸውን 1042 ሰልጣኞችን በድምቀት እያስመረቁ ይገኛል።
በምርቃት ፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ለተመራቂ ሰልጣኞች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክታቸውን በማስተላለፍ፤ ሀገራችን ኢትዮጵያ ወደ ብልፅግና ለምታደርገው ጉዞ በሙያዊ ክህሎትና ሥነ-ምግባር የታነፀ፣ ለሥራ ፍቅርና ተነሳሽነት ያለው እንዲሁም ከአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሠራሮች ጋር ተዋህዶ መሥራት የሚችል የሰው ኃይል በብዛት እና በጥራት በማሰልጠን ረገድ ቴክኒክ እና ሙያ ኮሌጆች ጉል ሚና እንዳላቸው ተናግረዋል።
በድሬዳዋ አስተዳደር የሚገኙ የቴክኒክ እና ሙያ ኮሌጆች ለወጣቶች አዳዲስ እና በገበያው ላይ ተፈላጊ የሆኑ የሙያ ዘርፎችን በማሰልጠን ወጣቶችን የሙያ ባለቤት እያረጉ እንደሚገኙም ክቡር ከንቲባ ከድር ጁሀር ገልፀዋል።
ከንቲባ ከድር አያይዘውም ለቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ዘርፍ ትኩረት ሰጥተው የሰሩ ሀገሮች ዛሬ ላይ የደረሱብት የኢኮኖሚያዊ እመርታ እና የቴክኖሎጂ የበላይነትን ላይ እንዲደርሱ እንዳስቻላቸው ጠቁመው፤ በሀገራችንም ዋነኛ ተግዳሮት የሆነውን ስራ አጥነትን ለማስወገድና ለሀገራችን ዘላቂ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ የድሬዳዋ ቴክኒክ እና ሙያ ኮሌጆች በቴክኖሎጂ ታግዘው እየሰሩ እንደሚገኙ ገልፀዋል።
በመጨረሻም ከንቲባ ከድር ተመራቂ ሰልጣኞች በስልጠናው ወቅት ያሳዩትን የሙያ ፍቅር እና ዲሲፒሊን በስራው ዓለምም በማስቀጠል በተለይም በድሬዳዋ ነፃ የንግድ ቀጠና እና በሌሎችም በተፈጠሩት የኢንደስትሪ ማዕከላት በመሰማራት ድሬዳዋን ብሎም ሀገርን የሚጠቅም ስራ እንዲሰሩ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
©️ DGC
#አሁን
#Happening_Now
የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች የ2017 ዓ.ም የቴክኒክና ሙያ ሰልጣኞች ምረቃ ስነ-ስርዓት
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+6
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ EASTRIP ፕሮጀክት የGRM ኮሚቴ የ2018 የመጀመሪያ ሩብ አመት መደበኛ ስብሰባውን አከናወነ፡፡
በኮሌጁ እየተገነባ ያለው የልህቀት ማእከል ግንባታው ምንም ችግር ሳይፈጠር እና ማህበረሰቡ ላይ ተጽእኖ ሳይኖረው በአግባቡ ተገንብቶ ለሚፈለገው አላማ እንዲውል እንዲሁም ችግር ቢከሰት በተገቢው መንገድ እንዲፈታ እያደረገ ላለው አስተዋጽኦ የGRM ኮሚቴ ምስጋና ያቀረቡት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ አያይዘውም ባለፉት አመታት በኮሌጁ፣ በኮሚቴው እንዲሁም በፕሮጀክቱ በኩል የተሰሩ ስራዎች አመርቂ መሆናቸውን የተናገሩ ሲሆን ባለፉት አመታት የተገኘውን ልምድ በመጠቀም በቀጣይም የሚሰሩ ስራዎች በሙሉ የማህበረሰቡን፣ የኮሌጁ እንዲሁም የመንግስትን ፍላጎት በተከተለ መልኩ ሊሰራና ችግሮችም በተገቢው መንገድ እንዲፈቱ አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
መስከረም 29/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
ለወቅታዊ ትኩስ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መረጃ
You tube: Dire Dawa Polytechnic College(DDPTC)
Facebook: https://web.facebook.com/Dire Dawa Polytechnic College Regional Flagship TVET Institute
Telegram: t.me/Dire Dawa Polytechnic College
TikTok: tiktok.com/@diredawapolytechnicollege
#ዜና | በስራ እድል ፈጠራና በስራ ፈጠራ አገልግሎት ዙሪያ ስልጠና መስጠት ተጀመረ
#DGC መስከረም 29/2018
የድሬዳዋ የቆላማ አካባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጄክት ምዕራፍ ሁለት በገጠር ጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት የአመራር በቡድን ክህሎት፣በስራ እድል ፈጠራና በስራ ፈጠራ አገልግሎት ዙሪያ የተዘጋጀ ስልጠና መሰጠት ተጀመረ፡፡ስልጠናው ከፌደራል ፕሮጀክት ዩኒት እና ከድሬዳዋ ስራና ክህሎት ቢሮ ለተውጣጡ ባለሞያዎች የሚሰጥ ነው።
በስልጠናው መክፈቻ ንግግር ያደረጉት አቶ ኢሳም ሁሴን የቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻል ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ በአጭር ጊዜ ውስጥ የመጠጥ ውሃ፣የመንገድ ግንባታ ፣የገጠር ቁጠባ እና ብድር ማህበራት ማደራጀት ፣በስራ እድል ፈጠራ እና በግብርና ዘርፍ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል ብለዋል። ፕሮጀክቱ የመንግስት የልማት አቅጣጫ ከመደገፍ አንፃር በሌማት ቱሩፋት እና አረንጓዴ አሻራ ላይ ሰፊ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ተናግዋል
ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግር ፈቺና ፋይዳቸው ላቅ ያሉ ስራዎን እየሰራ መሆኑን አስታውሰዋል፡፡
የዛሬው ስልጠና በመሰረታዊነት በዚህ የገንዘብ ድጋፍ የሚደረግላቸው በአዲስ የሚመሰረቱ 40 ያህል ማህበራት የወረዳ አመራሮች ባለድርሻ አካላት ወደ ስራ ከመግባታቸው አስቀድሞ ስለአፈፃፀም ሂደቱ በቂ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ይህ ስልጠና መዘጋጀቱን አውስተዋል።
ዛሬ ስለ ስራ ፈጠራ አገልግሎት፣ የንግድ ስራ ዕቅድ ዝግጅት እና ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የተዘጋጀ መመሪያን በተመለከተ ግንዛቤ ተሰጥቷል። በግብርና እንዲሁም በሌሎች ከግብርና ዘርፍ ውጪ ባሉ የስራ ዕድሎች ላይ ተሰማርተው የሚደረግላቸውን ድጋፍ ለተገቢ ዓላማው በማዋል ኑሯቸውን የሚያሻሽሉበት ሁኔታ ይፈጠራል ተብሎ ይጠበቃል፡፡LLRP2 የአርብቶ እና አርሶ አደር ማህበረሰብ የኑሮ ሁኔታን ማሻሻልና የምርትና ምርታማነት ማሳደግ ሂደቱን መደገፍ ትኩረት አድርጎ እየሰራ ይገኛል፡፡
በገጠር ጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት የአመራር፣ በቡድን ክህሎት፣በስራ እድል ፈጠራና በስራ ፈጠራ አገልግሎት ዙሪያ በተዘጋጀው ስልጠና የስራ ክህሎት ቢሮ ባለሞያዎች ፣የወረዳ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሰራተኞች የወረዳ አስተባባሪዎ እና ባለሞያዎች በስልጠናው ላይ ተሳታፊ ሆነዋል ሲል ዘገባውን ያደረሰን የግብርና ውሀ መአድን እና ኢነርጂ ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ነው።
ለፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን የተዘጋጀ በተግባር የተደገፈ ተከታታይ የአቅም ግንባታ ስልጠና ማስጀመሪያ መርሃግብር ተካሄደ፡፡
ይህ የአቅም ግንባታ መድረክ የኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን ሙያዊ ብቃታቸውን ከማሳደግ ባሻገር በየሙያ መስኩ በየኢንዱስትሪው ተግባራዊ ዕውቀትና ክህሎት የሚያገኙበት ሆኖ መሰናዳቱና የተሻለ ልምድና ተሞክሮዎችን ከአቻዎቻቸው የሚቀስሙበትን ዕድል የሚፈጥር መድረክ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ተናግረዋል፡፡
የቢሮው ም/ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በበኩላቸው ሰልጣኞች ስልጠናውን በንቃት እንዲሳተፉ እና ስልጠናውን አጠናቀው ሲጨርሱ በማሰልጠን የስልጠና ጥራትን ለማሻሻልና የሥራ ገበያውን ፍላጎት ለመመለስ በሚደረገው ሁሉን አቀፍ ርብርብ ውስጥ የበኩላቸውን አስተዋፅዖ ለማበርከት ከወዲሁ እንዲዘጋጁ አሳስበዋል፡፡
በዚህ የአቅም ግንባታ ስልጠና የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እና የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን ተሳታፊ ሲሆኑ ገበያው የሚፈልገውን ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያ ለማፍራት የአሰልጣኞችን ብቃት ተከታታይነት ባለው መልኩ ማሳደግ ወሳኝ በመሆኑ በቀጣይም ትኩረት እንደሚሰጠውም በቢሮው የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ ገልጸዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መስከረም 27/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ እንዲሁም የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ እና የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሰራተኞች በዛሬው እለት “ከጂኦስትራቴጂ ኩስመና ወደ ታደሰ ቁመና እና ወደ ተሻለ ሀገር” በሚል መሪ ሀሳብ የመንግስት ያለፉት ዓመታት ጉዞና የቀጣይ ዓመታት የትኩረት መስኮች ላይ የሚመክር የውይይት መድረክ አካሄደዋል፡፡
በመድረኩ ላይ የተገኙት ሰራተኞች በሀገራዊ ቀጣይ የእድገት ጉዞ ላይ የጠራ ግንዛቤን እንዲጨብጡና ለሀገራዊ ለውጡ በሁሉም መስክ የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ አቅም የሚፈጥርላቸው ይሆናል።
መድረኩም የድሬዳዋን እድገትና ተምሳሌትነት እንዲሁም የኢትዮጵያን የከፍታ ጉዞ ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል በቀጣይም የመንግስትን አሻጋሪ ዕሳቤዎች በቁርጠኝነት ለመፈፀምና ለማስፈፀም ተግባቦት የፈጠረ መሆኑን ተሳታፊዎች ተናግረዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መስከረም 27/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
