uz
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Kanalga Telegram’da o‘tish

Ko'proq ko'rsatish
1 076
Obunachilar
+224 soatlar
+37 kunlar
+230 kunlar
Postlar arxiv
#ዜና የወጣቶችን ችግር ለመፍታት ሁሉም ተቋማት በጋራ ሊሰሩ ይገባል ተባለ፡፡ በድሬዳዋ አስተዳደር የወጣቶችና ስፖርት ኮምሽን ኮምሽነር ክቡር አቶ ካሊድ መሀመድ የተመራ ልኡክ ቡድን በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የመስክ የስራ ጉብኝት አደረጉ፡፡ በመስክ ጉብኝቱ ላይ በመገኘት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲና አቶ ሰልሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ በንግግራቸውም እንኳን ወደ ምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል ወደ ሆነው የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በደህና መጣችሁ ኮሌጁ ወጣቶችን የሞያ ባለቤት ከማድረግ በዘለለ ስራ ፈጣሪ እንዲሆኑና ከራስ አልፎ ለማህበረሰቡ የሚተርፉ ባለሙያዎች ለማድረግ የሚሰራ አንጋፋ ተቋም ነው፡፡ ከዚህ ረገድ ኮሌጁ የሚጠበቅበትን እየተወጣ ያለ ኮሌጅ ነው ያሉ ሲሆን አያይዘውም የወጣቶችን ችግር ለመፍታት ሁሉም በለድርሻ አካላት በጋራ በመሆን ሊሰሩ ይገባል ብለዋል፡፡ ኮሌጁ በአስተዳደራችን ብሎም በሃገራችን ወጣቶችን ለሃገር እንዲተርፉ እያደረገ ያለ አንጋፋና ግንባር ቀደም ተቋም ነው፡፡ ያሉት ደግሞ የወጣቶችና ስፖርት ኮምሽን ኮምሽነር ክቡር አቶ ካሊድ መሀመድ ሲሆኑ ሁለቱም ተቋማት ወጣቶች ላይ እንደ መስራታችን በከተማችን ብሎም በአካባቢው የሚገኙ ወጣቶችን ጤናው የተጠበቀና ክህሎት ያለው ወጣቶችን ማፍራት ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡አያይዘውም ከድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በጋራ በመስራታችን በጣም ደስተኞች ነን ኮምሽኑና በየወረዳው የሚገኙ ተጠሪ ተቋማት በየወረዳው ያሉ ወጣቶችን በማሰባሰብ በኮሌጁ ያለውን እምቅ አቅም መጠቀም ይኖርብናል ብለዋል፡፡ በመጨረሻም ልኡክ ቡድኑ በኮሌጁየሚገኙ የተለያዩ ትምህርት ክፍሎችን ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን ኮሌጁ ያለበት ደረጃ እንዲሁም በቀጣይ ሊሰራቸው ያሰባቸውን ጉዳዮች በአቶ መሐመድአወል ጠሃ በቂ ገለጻ የተደረገላቸው ሲሆን በመስክ ምልከታው ላይ የወጣቶችና ስፖርት ኮምሽን ኮምሽነር ክቡር አቶ ካሊድ መሀመድ፣የወጣቶችና የበጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ዳይሬክተር አቶ ባህር አብደላ እና የኮምሽኑ የማኔጅመንት አባላትና የወረዳ ተጠሪ ተቋማት እንዲሁም የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ እና የኮሌጁ ም/ዲን አቶ አብዱልፈታህ ኢብራሂም ተገኝተዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ታህሳስ 18/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

በስራ ቦታ የኤች አይ ቪ/ኤድስ ስርጭትን ለመግታት የአመራሩን ግንዛቤ በማሳደግ ቅንጅታዊ አሰራርን ማጎልበት እንደሚገባ ተገለፀ፤ በስራ ቦታ ላይ የኤች አይ ቪ/ኤድስ መከላከል ማንዋልን በተመለከተ ለሥራና ክህሎት ቢሮ ማኔጅመንት አባላት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሂዷል። በመድረኩም ላይ ተገኝተው መልእክታቸውን ያስተላለፉት የቢሮው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በስራ ቦታ ላይ  የኤች አይ ቪ.ኤድስ ስርጭትን ለመግታት የአመራሩን ግንዛቤ በማሳደግ ቅንጅታዊ አሰራርን ማጎልበት እንደሚገባ ሲጠቁሙ፤ የኤች.አይ.ቪ ኤድስ ስርጭት አሁናዊ ሁኔታ አሳሳቢ በመሆኑ ከመዘናጋት ወጥተን ኤች አይ ቪ ኤድስን ለመከላከልና ከኤች አይ ቪ ኤድስ ነፃ የሆነ ትውልድን ለመፍጠር የቢሮው ማኔጅመንት ሚናቸው የላቀ በመሆኑ ከቢሮው የሴቶች ወጣቶችና ኤች አይቪ ኤድስ ባለሙያ ጋር በመቀናጀትና በመናበብ ሰፊ ስራዎችን በመስራት የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት በሚደረገው ጥረት ሰፊ ድርሻ እንዳላቸው አመላክተዋል። በመድረኩ ላይ የተሳተፉት የማኔጅመንት አባላትም እንደገለፁት ከስልጠናው ጥሩ ግንዛቤ እንዳገኙና በተለይ ለዘርፉ ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰራባቸው የሚገቡ ቁልፍ ቦታዎችንም በመጠቆም ተጋላጭነትን በሚቀንሱ ስራዎች ላይ ትኩረት በማድረግና ግንዛቤ በማስጨበጥ ረገድ በቀጣይ ትኩረት ሰጥተው በሀላፊነት ስሜት እንደሚንቀሳቀሱ ገልፀው መድረኩን አጠናቀዋል ። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ታህሳስ 17/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የአሰሪና ሰራተኛ ዳይሬክቶሬት ኢንዱስትሪ ፓርክ ለሚገኙ ከተለያዩ ኢንዱስትሪዎች  ለተወጣጡ  ሰራተኞችና የሴፍቲ የኮሚቴ አባላት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በማዘጋጀትበስራ ሁኔታ እና በሙያ ደህንነትና ጤንነት ላይ ስልጠና መስጠቱ ተገለጸ። በቢሮው የአሸሪና ሰራተኛ ዳይሬክቶሬት በዋናነት የኢንደስትሪውን ሰራተኛ የስራ ሁኔታ ደህንነትና ጤና የማስጠበቅ ሥራዎች ትኩረት የተሰጣቸው ሲሆኑ ይህም የኢንዱስትሪውን ምርታማነት በማሳደግ የኢንዱስትሪውን ሰላም በማረጋገጥ ረገድ የሚጫወተው ሚና ቀላል የሚባል አይደለም። በመሆኑም በአስተዳደሩ በሚገኙ ኢንደስትሪዎች የሙያ ደህንነትና ጤንነት ኮሚቴ አንዲደራጅና እንዲቋቋም ድጋፍ በማድረግ ለተመሰረቱት ኮሚቴዎችም በቀጣይ በሚያከናውኗቸው ሥራዎች በማስገንዘብ  በተለይ የሙያ ደህንነቱና ጤናው የተጠበቀ የሥራ አካባቢን በመፍጠር የኢንደስትሪውን ሰላም እና ደህንነት በማስጠበቁ በተጨባጭም ውጤት እንዲያመጣ እያገዘ ይገኛል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ታህሳስ 17/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ስር የሚገኘው ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ዘርፉ ወቅቱ የደረሰበትን የቴክኖሎጂ እድገት እና የኢንዱስትሪውን የሰው ሃይል ፍላጎት ለማሟላት የሚያስችል የክህሎት ማሻሻያ ስልጠናና ማሽን ጥገና ላይ ያተኮሩ ስራዎች መሠራታቸው ተገለጸ፤ ይህም ስራ በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የሚገኙ የአይሲቲ እና የቴክስታይል፣ ጋርመንትና ሌዘር ትምህርት ክፍሎች ለሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን  የተግባር አቅም ግንባታ ስልጠናዎችና የማሽን ጥገና ስራዎችን የኮሌጁን የውስጥ አቅም በመጠቀም የተሰራ መሆኑ ታውቋል። በዚህም ለ15 ቀናት በተሰጠው ስልጠናና በተደረገው ጥገና SNLS, Over Lock Machine, Ironing Machine, Post Bed Leather Sewing Machine and Cyliderical Bed Leather Sewing በቴክስታይል፣ ጋርመንት እና ሌዘር ዲፓርትመንት የተጠገኑ ሲሆን በአይሲቲ ዲፓርትመንትም ብልሽት የገጠማቸውን ኮምፒውተሮች በመጠገን ወደ ስራ ማስገባት ተችሏል። የክህሎት ማሻሻያ ስልጠና እና ማሽን ጥገናው ውጤታማ በሆነ መልኩ እንዲከናወን አሰልጣኝና ባለሙያ ከሌላ ቦታ ሳይመጣ በኮሌጁ ውስጥ በሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን አቅም በመጠቀም የተሰራ መሆኑንና አቅምን ከማሳደግ ጎን ለጎን ለጥገና የሚወጣውን ተጨማሪ ወጪ ማስቀረት መቻሉን የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ ገልፀዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ታህሳስ 16/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና  ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ኤጀንሲ ሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ያዘጋጀው የገበያ ተኮር አጫጭር ስልጠናን ፍትሃዊነት ለማረጋገጥ እና የስልጠና ጥራት ለማሻሻል ብሎም ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል ከከተማና ከገጠር ወረዳዎች ምክትል ስራ አስፈፃሚዎችና የአንድ ማእከል አስተባባሪች እንዲሁም ከሁለቱ የመንግስት ፖሊ ቴክኒክ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና  ምክትል ዲኖችና የስልጠና አስተባባሪዎች የተሳተፉበት የግንዛቤ ማስጨበጫና የውይይት መድረክ አካሄደ፡፡ በግንዛቤ ማስጨበጫና በውይይት መድረኩ ላይ የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ያተኮረ ሲሆን በዋነኛነት የ2017 ዓ.ም የገበያ ተኮር አጫጭር ስልጠና በእስካሁኑ ዕቅድ አፈፃፀም የተገኙ ውጤቶችና የታዩ ክፍተቶች የተለዩበት ሲሆን በቀጣይ የገበያ ተኮር አጫጭር ስልጠናን  በገጠር ወረዳዎች ተደራሽ ለማድረግ  የMobile  TVET ስርአትን ለመተግበር የሚያስችል ምቹ ሁኔታዎች ዙሪያ ከገጠር ወረዳ ምክትል ስራ አስፈፃሚዎችና አስተባባሪዎች ጋር መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡  የድሬዳዋ አስተዳደር  ሥራና  ክህሎት ቢሮ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ጀማል አደን እንደገለፁት  የገበያ ተኮር አጫጭር ስልጠናን ፍትሃዊነት ለማረጋገጥ እና የስልጠና ጥራት ለማሻሻል ብሎም ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር የተጀመረውን ቅንጅታዊ አሰራር አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ታህሳስ16/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና  ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ኤጀንሲ ሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ያዘጋጀው የገበያ ተኮር አጫጭር ስልጠናን ፍትሃዊነት ለማረጋገጥ እና የስልጠና ጥራት ለማሻሻል ብሎም ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል ከከተማና ከገጠር ወረዳዎች ምክትል ስራ አስፈፃሚዎችና የአንድ ማእከል አስተባባሪች እንዲሁም ከሁለቱ የመንግስት ፖሊ ቴክኒክ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና  ምክትል ዲኖችና የስልጠና አስተባባሪዎች የተሳተፉበት የግንዛቤ ማስጨበጫና የውይይት መድረክ አካሄደ፡፡ በግንዛቤ ማስጨበጫና በውይይት መድረኩ ላይ የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ያተኮረ ሲሆን በዋነኛነት የ2017 ዓ.ም የገበያ ተኮር አጫጭር ስልጠና በእስካሁኑ ዕቅድ አፈፃፀም የተገኙ ውጤቶችና የታዩ ክፍተቶች የተለዩበት ሲሆን በቀጣይ የገበያ ተኮር አጫጭር ስልጠናን  በገጠር ወረዳዎች ተደራሽ ለማድረግ  የMobile  TVET ስርአትን ለመተግበር የሚያስችል ምቹ ሁኔታዎች ዙሪያ ከገጠር ወረዳ ምክትል ስራ አስፈፃሚዎችና አስተባባሪዎች ጋር መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡  የድሬዳዋ አስተዳደር  ሥራና  ክህሎት ቢሮ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ጀማል አደን እንደገለፁት  የገበያ ተኮር አጫጭር ስልጠናን ፍትሃዊነት ለማረጋገጥ እና የስልጠና ጥራት ለማሻሻል ብሎም ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር የተጀመረውን ቅንጅታዊ አሰራር አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ታህሳስ16/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የTVT ሴክተሩ ከአመለካከት ጋር ተያይዞ ከፍተኛ የሆነ ችግር የሚታይበት ዘርፍ በመሆኑ ከሚድያ አካላት ጋር ተቀናጅቶ መስራት እንደሚገባ ተግለፀ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት በአስተዳደሩ ለሚገኙ የሚዲያ ባለሙያዎች ዘርፉን አስመልክቶ የግንዛቤ መስጫ መድረክ አካሄደ:: የግንዛቤ መስጫ መድረኩን በንግግር የከፈቱት የስራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ሀላፊና የኤጀንሲው ሀላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በንግግራቸው በአስተዳደሩ የሚገኙ የሚዲያ ተቋማት በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ያሉ እንቅስቃሴዎች ላይ የሚሰሯቸው ስራንዎችና ለዘርፉ የሚሰጡትን የአየር ሰዓት በማሻሻል ተገቢውን ትኩረት መስጠት እንደሚገባቸው ገልፀው በተጨማሪም የሚዲያ ባለሙያዎች ስለዘርፉ በጥልቀት ለመገንዘብ እንዲረዳ በቴክኒክና ሙያ ተቋማት ውስጥ አንድ የሙያ ክህሎት እንዲሰለጥኑ ምክረ ሀሳብ አቅርበዋል:: ማህበረሰቡ ስለ ቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ያለው አመለካከት በጣም ዝቅተኛ መሆኑን የገለፁት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ በዘርፉ ተገቢውን ግንዛቤ ለመፍጠር የሚዲያ አካላት በተለያየ አጋጣሚ በሚያደርጏቸው እንቅስቃሴዎች ውስጥ የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ በህብረተሰቡ ውስጥ ሰርፇ ዋና ኢላማውን እንዲመታ እንዲሁም የተሻለ የስራ እድል ተፈጥሮ የወጣቱን ብሎም የማህበረሰቡን ህይወት መቀየር እንዲቻል የሚታየውን የተዛባ አመለካከትን መቀያር አስፈላጊ በመሆኑ ለዚህም የሚዲያ አካላት የአንበሳውን ድርሻ እንደሚወስዱ አፅዕኖት ሰጥተው ተናግረዋል:: የኮሌጁ ዲን አክለውም ተቋሙ በቀጣይ በአስተዳደሩ ከሚገኙ የሚዲያ ተቋማት ጋር በርካታና ዘላቂነት ያላቸው ስራዎችን በቅንጅት ለመስራት በእቅድ መያዙን ገልፀው ለዚህም እንዲረዳ የሚዲያ አካላት ከተቋሙ ጋር በጋራ ሊሰሩባቸው የሚችሉ ሀሳቦችንም ይዘው ቢመጡ ኮሌጁ በየትኛውም መንገድ በቅንጅት ለመስራት ዝግጁ መሆኑን ገልፀዋል:: በእዲሱ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ፓሊሲ ዙሪያ ለተሳታፊዎች ግንዛቤ የሰጡት በስራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ት/ት ስልጠና የሰልጣኞች ልማት ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ምንልክያለው ወርቅነህ ሲሆን በዚህም ነባሩ ፖሊሲ ላይ የነበሩ ክፍተቶችን ጨምሮ በአዲሱ ፖሊሲ የተካተቱ የለውጥ ሀሳቦችን በዝርዝር ለተሳተፊዎች አቅርበዋል:: በመድረኩ ኮሌጁ በEASE ፕሮጀክት በቀጣይ 5አመት ትግበራ ምን ሊሰራ እንዳቀደ ለሚዲያ አካላት በዝርዝር የቀርበ ሲሆን ከመድረኩ በቀረቡ ሃሳቦች ላይ እንዲሁም በቀጣይ ስለሚኖረው የጋራ እንቅስቃሴ ዙሪያ ሰፊ ውይይትም ተካሂዷል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን ታህሳስ 16/2017 ዓ.ም

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የEASE ፕሮጀክት በተቋሙ አገልግሎት ዘርፍ ላይ ለሚሰሩ ሰራተኞች የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት ጀመረ:: ኮሌጁ በEASE(Education and Skills for Employ Ability) ፕሮጀክት አማካኝነት ያዘጋጀው ይህን የአቅም ግንባታ ስልጠና Work Ethics & Service Delivery ላይ መሰረት ያደረገ ስልጠና ሲሆን በአስተዳደር ከሚገኘው የስራ አመራር ኢኒስቲትዩት ጋር በመተባበር የተዘጋጀ መሆኑም ተገልፇል:: ስልጠናውን በንግግር ያስጀመሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ባስተላለፋት መልዕክት "ይህ ስልጠና ሲዘጋጅ በተቋሙ ጥናት ተደርጎበትና አስፈላጊነቱም በማኔጅመንቱ ታምኖበት የተዘጋጀ ስልጠና በመሆኑ ሰልጣኞች እዚህ በሚኖራችሁ የ5ቀን ቆይታ የሚሰጠውን ስልጠና በአግባቡና በሀላፊነት ሰልጥናችሁ ወደ ኮሌጁ ስትመለሱ በየምትሰሩበት የስራ ክፍል ላይ በተግባር የሚታይ ለውጥ ማሳየት ይጠበቅባችኃል ያሉ ሲሆን ይህም ስልጠና እንደ ማስጀመርያ መሆኑን እና ተቋሙ በቀጣይ ያቀዳቸውና በየክፍሉ በተለዩ የስልጠና ፍላጎቶች ላይ ተመርኩዞ ክፍተቶችን በስልጠናዎች የሚሞላ መሆኑንም ገልፀዋል:: የኮሌጁ ዲን አክለውም ተቋሙ በዚህ አመት በርካታ አሳይመንቶች እንዳሉበትና አንደኛውም የISO ጉዳይ መሆኑን አስታውሰው IOS በዋናነት ሚያተኩረው Costomer Focus ላይ ነው ያሉ ሲሆን አሁን ያለንበት የCostomer satisfaction survey ከኛ ብዙ እንደሚጠበቅ አመላካች በመሆኑና ይህንንም ለመፈፀም የስራ ስነ-ምግባር ወሳኝነት ያለው በመሆኑ ምክንያት ይህንን ስልጠና ማዘጋጀት አስፈላጊ ሆኖ አጊኝተነዋልም ብለዋል:: የአቅም ግንባታው ስልጠናው በኢንቲትዩቱ አሰልጣኞች የሚሰጥ ሲሆን ስልጠናው በሁለት ዙር ተከፍሎ ሲሰጥ ይህ የመጀመርያ ዙር ስልጠና ለቀጣዮቹ 5ቀናትም የሚቆይ ይሆናል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን ታህሳስ 15/2017 ዓ.ም

የአፋር ክልል ስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊዎችና የአፋር ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የማኔጅምንት አባላት በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የመስክ የስራ ጉብኝት እና የልምድ ልውውጥ አደረጉ፡፡ በመስክ ጉብኝቱ እና በልምድ ልውውጡ ላይ በመገኘት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ በንግግራቸውም እንኳን ወደ ምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል እና ሁለተኛ ቤታችሁ ወደ ሆነው የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በደህና መጣችሁ ፡፡ ኮሌጁ ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ ብዙ ሺህ ወጣቶች የሙያና የክህሎት ባለቤት ያደረገ ኮሌጅ ነው ኮሌጁ አሁን ለደረሰበት ስኬትም የከተማ አስተዳደሩ እንዲሁም የኮሌጁ ማህበረሰቦችና ባለድርሻ አካላቶች የማይተካ ሚና አላቸው ያሉ ሲሆን ኮሌጁ በቀጣይ የባቡር ምህንድስና የልህቀት ማእከል እንደመሆኑ መጠን ለድሬዳዋ መመስረት ምክንያት የሆነውን የባቡር ቴክኖሎጂ ለማዘመንና አሁን ያሉትን ባለሞያዎች የሚረከቡ ባለሞያዎችን እያፈራ የሚገኝ ተቋም ነው ፡፡ እንዲሁም በአስራ አንዱ የቴክኒክና ሙያ ዘረመሎች አንጻር ኮሌጁ በትኩረት እየሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡ የመስክ ምልከታውን እና የልምድ ልውውጡን መሰረት በማድረግም የልኡካን ቡድኑ የመሩት የአፋር ክልል ስራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክተር የሆኑት አቶ አብዱ ሀሰን እንዳሉት አጠቃላይ የኮሌጁ እንቅስቃሴ እጅግ በጣም ጥሩ የሚባልና በኮሌጁ ውስጥ እየተገነባ የሚገኘውም የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት መአከል ግንባታ በከፍተኛ ፍጥነት ተከናውኖ ለሚፈለገው አላማ መዋል እንዲችል የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር እየወሰደ ያለው ቁርጠኝነት ለሌሎች ከተሞች አርአያ መሆን የሚችል ነው ብለዋል፡፡ በኮሌጁ የሚገኙ የተለያዩ ትምህርት ክፍሎች ያላቸው አቅም ከሌሎች ኮሌጆች አንጻር ከድሬዳዋ አልፎ ለምስራቁ የሀገራችን ክፍሎች የሚበቃ ነው ያሉ ሲሆን ይህንን አቅም በተገቢው መንገድ በመጠቀም ከተማችሁን ብሎም የምስራቁ የሀገራችንን ክፍል ማልማት የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡ በመስክ ጉብኝቱ ወቅት የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የኮሌጁ እና በኮሌጁ የሚገኙ ፕሮጀክቶ አፈጸጸም እንዲሁም አጠቃላይ የኮሌጁን እንቅስቃሴ በአቶ መሳይ ጥላሁንና በአቶ ዘየደ ተክሌ የቀረበ ሲሆን በመቀጠልም ከአፋር ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለኮሌጁ ዲን የአፋር ባህላዊ አልባሳት ስጦታ ተበርክቷል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ታህሳስ 14/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ