Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
Kanalga Telegram’da o‘tish
Ko'proq ko'rsatish
1 076
Obunachilar
+224 soatlar
+37 kunlar
+230 kunlar
Postlar arxiv
በአስተዳደሩ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና ኢንተርፕራይዝ ልማትን የሚደግፉ ፕሮጀክቶች ከቢሮውና ብድር ከሚያቀርቡ ባንኮች ጋር ያላቸው ቅንጅታዊ አጠቃላይ የስራ አፈጻጸም ግምገማ እና የመስክ ምልከታ ተደረገ፡፡
በዚህም አቶ ተፈሪ ታደሰ የኢኔብሊንግ ኢትዮጵያ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ፣ አቶ ንጉሱ ጥላሁን የኢኔብሊነግ ኢትዮጵያ ሲንየር አማካሪ፣ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊ እንዲሁም የቢሮው ባለሙያዎች በተገኙበት የፕሮጀክቶቹ አፈጻጸም ቀርቦ በመስክ ምልከታ የታዩ ጉዳዮችን ጨምሮ ውይይት ተካሂዶባቸዋል፡፡
በመስክ ምልከታ አፈጻጸማቸው ከታየ ፕሮጀክቶች ጥላ ፕሮጀክት አንዱ ሲሆን ገቢያቸው አነስተኛ ለሆኑ የገጠር ወጣት ሴቶች ቀጣይነት ያለው የኑሮ መሻሻል እንዲፈጠር መነሻ ካፒታል የሚሆን የሶስት አመት ከዋስትና ነጻ የብድር አቅርቦት በማመቻቸት ስልጠናዎችን እንዲያገኙ እና ቢዝነሶቹን በቅርበት ውጤታማነታቸውን በመከታተል መደገፍ ላይ ያለበት ደረጃ ታይቷል።
ሌላኛው አፈጻጸሙ የታየው ሳፊ ፕሮግራም ሲሆን ፋይናንሻል ቴክኖሎጂ ላይ የሚሰራና መደበኛ እና ኢ-መደበኛ ብድሮችን በማቅረብ በተለይ ለኢ-መደበኛ ተበዳሪዎች በመታወቂያ ብቻ ብድሮችን ከእጅ ንክኪ ነጻ የሆነ በAI ታግዘው ብድሮችን ያመቻቻሉ፤ በዚህም በዋናነት 80% ሴቶች፣ 10% ለአካል ጉዳተኞች እና 10% ለተፈናቃዮች ትኩረት አድርጎ የሰራቸው ስራዎች በተጨባጭ ምን ላይ እንደሚገኙ ምልከታ ተደርጎባቸዋል፡፡
በተጨማሪም መስመር ፕሮግራም የብድር አገልገሎት ሴቶችና ወጣት ሥራ ፈጣሪዎችን ለማበረታታትና ሥራቸውን ለማስፋፋት የሚሰጠውን የብድር አገልገሎት በአስተዳደሩ የሚገኙ በተለይም በወጣት ሴቶች የሚመሩ የጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን በመጠነኛ ዋስትናና በአነስተኛ የወለድ መጠን እንዲሁም የሸሪአ መርህን የተከተለ ከወለድ ነጻ የብድር አገልገሎት ተጠቃሚ የማድረግ ስራ ተጠቃሚዎችን በአካል በማነጋገር ያሉበትን ሁኔታ መመልከት ተችሏል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 14/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በአስተዳደሩ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና ኢንተርፕራይዝ ልማት ስራዎችን የሚደግፉ ፕሮጀክቶች ያላቸው አጠቃላይ የስራ አፈጻጸም ተገመገመ፡፡
በዚህም አቶ ተፈሪ ተደሰ የኢኔብሊንግ ኢትዮጵያ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ፣ አቶ ንጉሱ ጥላሁን የኢኔብሊነግ ኢትዮጵያ ሲንየር አማካሪ፣ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊ እንዲሁም የቢሮው ባለሙያዎች በተገኙበት የፕሮጀክቶቹ አፈጻጸም ቀርቦ በመስክ ምልከታ የታዩ ጉዳዮችን ጨምሮ ውይይት ተካሂዶባቸዋል፡፡
በመስክ ምልከታ አፈጻጸማቸው ከታየ ፕሮጀክቶች ጥላ ፕሮጀክት አንዱ ሲሆን (unpaid rural women) ገቢያቸው አነስተኛ ለሆኑ የገጠር ወጣት ሴቶች ቀጣይነት ያለው የኑሮ መሻሻል እንዲኖራቸው መነሻ ካፒታል የሚሆን የሶስት አመት ከዋስትና ነጻ የብድር አቅርቦት በማመቻቸት ስልጠናዎችን እንዲያገኙ እና ቢዝነሶቹን በቅርበት ውጤታማነታቸውን በመከታተል የሚደግፍ መሆኑ ታይቷል።
ሌላኛው አፈጻጸሙ የታየው ሳፊ ፕሮግራም ሲሆን ፋይናንሻል ቴክኖሎጂ ላይ የሚሰራና መደበኛ እና ኢ-መደበኛ ብድሮችን በማቅረብ በተለይ ለኢ-መደበኛ ተበዳሪዎች በመታወቂያ ብቻ ብድሮችን ከእጅ ንክኪ ነጻ የሆነ በAI ታግዘው ብድሮችን ያመቻቻሉ፤ በዚህም በዋናነት 80% ሴቶች፣ 10% ለአካል ጉዳተኞች እና 10% ለተፈናቃዮች ትኩረት አድርጎ የሰራቸው ስራዎች በተጨባጭ ምን ላይ እንደሚገኙ ምልከታ ተደርጎባቸዋል፡፡
በተጨማሪም መስመር ፕሮግራም የብድር አገልገሎት ሴቶችና ወጣት ሥራ ፈጣሪዎችን ለማበረታታትና ሥራቸውን ለማስፋፋት የሚሰጠውን የብድር አገልገሎት በአስተዳደሩ የሚገኙ በተለይም በወጣት ሴቶች የሚመሩ የጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን በመጠነኛ ዋስትናና በአነስተኛ የወለድ መጠን እንዲሁም የሸሪአ መርህን የተከተለ ከወለድ ነጻ የብድር አገልገሎት ተጠቃሚ የማድረግ ስራ ተጠቃሚዎችን በአካል በማነጋገር ያሉበትን ሁኔታ መመልከት ተችሏል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 14/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ወደ ሥራ ያስገባውን የሀሳብና ክህሎት ባንክ / Idea and Skill Bank/ የፈጠራ ሀሳብ እና ክህሎት ያላቸው ዜጎች ሀሳብና ክህሎታቸውን የሚያካፍሉበት፣ ለገበያ የሚያቀርቡበት እንዲሁም ሀሳብና ክህሎታቸውን አቅናጅተው ሥራ የሚፈጥሩበትን ትስስር ከተለያዩ አካላት ጋር መፍጠር የሚያስችላቸው ነው፡፡ የሚከተለውን የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት ማስፈንጠሪያን በመጠቀም አሁኑኑ ይቀላቀሉ https://www.lmis.gov.et
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
‹‹ወጣቶችን የሳይንስና ቴክኖሎጂ ክህሎቶችን በማስገንዘብ የፈጠራ ሃሳባቸውን በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ውስጥ እንዲያዳብሩ በማድረግ ለሃገር የሚጠቅሙ ዜጎችን መፍጠር ያስፈልጋል››
የኮሌጁ ዲን
አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ
********************************************************
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከተለያዩ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ የሳይንስ ትምህርቶች ላይ ዝንባሌ ላላቸውና የፈጠራ ሃሳብ ላላቸው ወጣቶች በSTEM Power ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በዛሬው እለት አከናወነ፡፡
በመድረኩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ እንደተናገሩት በቅድሚያ ወደ ምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል እና ሁለተኛ ቤታችሁ ወደሆነው ድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በደህና መጣችሁ ያሉ ሲሆን አያይዘውም ኮሌጁ ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ በርካታ ወጣቶችን በእውቀት በክህሎት በአመለካከት ከማሰልጠን ውጪ የፈጠራ ሃሳብ ያላቸውን ወጣቶች በመቀበል እንዲሁም ሊሰሩት ያሰቡትን ቴክኖሎጂ ወደ መሬት አውርደው ለራሳቸው ብሎም ለሃገራቸው የሚተርፍ ቴክኖሎጂዎችን እንዲፈጥሩና ሃሳባቸውን ወደ ቢዝነስ እንዲቀይሩ የተለያዩ ድጋፎችን ሲያደርግ ቆይቷል ያሉ ሲሆን
የፈጠራ ሃሳብ ያላቸውን ወጣቶች የሳይንስና ቴክኖሎጂ ክህሎቶችን በማስገንዘብ የፈጠራ ሃሳባቸውን በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ውስጥ እንዲያዳብሩ በማድረግ ለሃገር የሚጠቅሙ ዜጎችን መፍጠር ያስፈልጋል ለዚህ ደግሞ ኮሌጁ ቀን ከሌት እየሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡
በመቀጠል ንግግር ያደረጉት ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ዲን የሆኑት ወ/ሮ ትግስት በዙ ሲሆኑ በንግግራቸውም አሁንም በዚህ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ላይ የተሳተፋችሁ እንዲሁም በትምህርት ቤት ውስጥ ያሉ የፈጠራ ሃሳብ ላላቸው የከተማችን ወጣቶች የፈጠራ ሃሳባቸውን ይዘው መጥተው ከፈጠራ ስራቸው ተጠቃሚ እንዲሆኑ በራካታ ስራዎችን በጋራ በመስራት ለራሳቸው ብሎም ለሃገር እንዲጠቅሙ የምንሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡
በተጨማሪም ም/ዲኗ እንደገለጹት ኮሌጃችን በአሁኑ ሰአት በባቡር ቴክነሎጂ እንዲሁም በICT የትምህርት ዘርፎች የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል ነው ስለዚህ የከተማችን ወጣቶች ይህንን እድል በአግባቡ ተጠቅመው እራሳቸውንም ሃገራቸውንም እንዲጠቅሙ በዚሁ አጋጣሚ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ ብለዋል፡፡
በመድረኩ ላይ በኮሌጁ ውስጥ ተማሪዎች ቢመጡ በምን አይነት መንገድ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ክህሎቶቻቸውን ማደበር እንደሚችሉ ግንዛቤ የተፈጠረ ሲሆን በመቀጠልም በተለያዩ ትምህርት ክፍሎች ጉብኝት በማድረግ የመድረኩ ፍጻሜ ሆኗል፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ታህሳስ 12/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ከኔዘርላንድ የልማት ድርጅት (SNV) ጋር በመተባበር 35 በወጣት ሴቶች ለሚመሩ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በበግና ፍየል ማድለብ ለተሰማሩ በአጠቃላይ 156 አባላትን (149 ሴት እና 7 ወንድ) ለእያንዳንዱ ኢንተርፕራይዝ 60,000 ብር የሚገመት ስራ ማስጀመሪያ ድጋፍ ተደረገ፤
የድጋፍ ርክክብ ስነ ስርዓቱ የቢሮው ተወካይ እና የልማት ድርጅቱ ተወካይ እንዲሁም የእንስሳት ጤና እና ሀብት ልማት ተወካይ በተገኙበት የተደረገ ሲሆን የተደራጁት ሴት ወጣቶች የሥራ እድል ለራሳቸውና ለሌሎች እንደሚፈጥሩ እንዲሁም ለሌሎች ምሳሌ በመሆን በበግና ፍየል ማድለብ ላይ በአነስተኛ አቅምና እውቀት አሁን በመጀመር በቀጣይ አስፍተውና አጠናክረው እንዲቀጥሉ ከባለሙያዎች ጋር ገለጻ ተደርጎላቸዋል፤
የልማት ድርጅቱ ከቢሮው ጋር በመተባበር ሥራ የሌላቸው ሴቶችና ወጣቶችን በገጠርና በከተማ በማደራጀት በተለያዩ ርዕስ ጉዳዮዎች በተለይ በኢንተርፕሩነርሺፕና በህይወት ክህሎት ስልጠናዎችን በመስጠት እና ተደራጅተው በሚሰማሩበት ሥራ ዘርፍ ላይ አሰፈላጊው ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱንና የዛሬውን ድጋፍ ጨምሮ በአጠቃላይ በከተማና በገጠር ለተደራጁ ወጣቶች በተመሳሳይ ኢንተርፕራይዞቹን በቅርበት በመከታተል ድጋፍ የተደረገ መሆኑንም ታውቋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 11/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
"ከወጣቶች ጋር በመተባበር ሙስናን መከላከል የነገን ስብዕና ለመቅረጽ"
21ኛው ዓለምአቀፍ የፀረሙስና ቀን!"
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ "ከወጣቶች ጋር በመተባበር ሙስናን መከላከል የነገን ስብዕና ለመቅረጽ" በሚል በአገር አቀፍ ደረጃ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀን ምክንያት በማድረግ ከቢሮው ማህበረሰብ ጋር ተወያይቷል።
የአስተዳደሩ የስነ-ምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ፌኑስ አብዱልጀባር በውይይቱ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር የሙስና ምክንያት የሆነውን የስነ-ምግባር ዝቅጠትንና ስግብግብነትን ለማረም እና አይቶ እንዳላየ ማለፍን ለማስቆም የቢሮው ሰራተኞችና አመራሮች በተለይም ወጣቱ ሚናው ላቅ ያለ መሆኑን አስረድተዋል።
የፀረ-ሙስና ትግሉ በቢሮው የአገልግሎት አሰጣጥ ዘንድ እንዲቀጣጠልና በዋናነት የስነ ምግባር ግንባታው የድርሻውን እንዲወጣ ወጣቱ ሙስናን የሚጠየፍ ብሎም በመከላከሉ ሂደት የድሻውን ተወጥቶ የሚታመንና የሚተማመን ሰራተኛና አመራር መፍጠር እንደሚገባ ተመላክቷል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 10/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማት እና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ለአዲስ አበባ ቢዝነስና ሜዲካል ኮሌጅ የስልጠና ጥራት ኦዲት በማከናወን የፈቃድ እድሳት እንዳደረገ ገለጸ፤
የፈቃድ እድሳቱን ለማድረግ አስፈላጊ የሆኑ ሰነዶች ማለትም የኮሌጁን የሶስት አመት የስራ አፈጻጸም፤ የሰው ሃይል የስራ ፍላጎት የገበያ ጥናት ሰነድ፣ የአሰልጣኞች ፕሮፋይል፣:የህንጻ ውል፣ የንግድ ፈቃድ እድሳት እና የመሳሰሉት ሰነዶች የማረጋገጥ ስራ ተሰርቷል በዚህም ዝቅተኛ የጥራት ስታንዳርድ ስለሟሟላቱ በተለይ በጤናው ዘርፍ ከጤና ቢሮ በተመደቡ ባለሙያዎች በፋርማሲ እና በነርሲንግ በኢትዮጵያ በቴ/ሙ/ት/ስ የስልጠና ዘርፍ በካሪኩለም መሠረት የስልጠና ግብአቶች ስለመሟላታቸው የማረጋገጥ ስራ ተሰርቷል፡፡
በዚህም በአምስት የስልጠና ፕሮግራሞች በአካውንቲንግ፣ በሰው ሃብት አስተዳደር፣ በማርኬቲንግ አስተዳደር፣ በነርሲንግ እና በፋርማሲ በግብአት፣ በአደረጃጀትና በአሰራር ብቁ ስለመሆኑ በባለሙያዎች ቡድን ተረጋግጦ ለቀጣይ ሶስት አመታት ስልጠናውን እንዲያካሂድ የፍቃድ እድሳት ሰርተፍኬት እንዲሰጠው ውሳኔ ላይ መደረሱን የአሰልጣኝ ልማት እና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ ተናግረዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 10/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ ምሩቅ ስራ ፈላጊዎች በድሬዳዋ ሰርቶ መለወጥ እንደሚቻል ለማሳየት ፍላጎትና ተነሳሽነታቸውን ከፍ የሚያደርግ ለዩኒቨርስቲ እና ኮሌጅ ምሩቃን ስራ ፈላጊዎች የማይንድ ሴት ስልጠና ተሠጠ።
ይህም ስልጠና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የስራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት በአስተዳደሩ ስር ከሚገኙ ቀበሌዎች የተወጣጡ ስራ ፈላጊዎች ተቀጥሮ መስራት ላይ ብቻ ሳይሆን በግልም ሆነ ተደራጅተው ስራ ፈጣሪ ለማድረግ አቅማቸውን ለመገንባት ታስቦ በተከታታይ በመሰጠት ላይ ይገኛል።
ቢሮው በአስተዳደሩ ትኩረት የተሰጠውን የስራ አጥ ቁጥርን ለመቀነስ የተጀመሩ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን እና ከኢንዱስትሪዎች ጋር በተፈጠረው መልካም ግንኙነት ተመራቂዎች ተደራጅተው ወደ ስራ እንዲሰማሩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ በመስራቱ ብዙዎች ተጠቃሚ እየሆኑ እንደሚገኙ የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ ተናግረዋል።
ዳይሬክቶሬቱ አክለው ተሳታፊ ምሩቃን ሥራ ፈላጊዎችም ከዚህ በፊት ተቀጥሮ ለመስራት ብቻ ይጠብቁ የነበሩበትን አመለካከት ከስልጠናው ባገኙት ግንዛቤ በግልም ሆነ ተደራጅቶ ለመስራት መነሳሳት እንደሚፈጥርባቸውና ይህን መሰል ስልጠናዎችንም ለወጣቶች ማዘጋጀት በአስተዳደሩ የተፈጠሩ የሥራ እድሎችን ለመጠቀም ያለው ሚና ከፍ ያለ መሆኑን ገልጸዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 9/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ኤጀንሲ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ለተከታታይ ቀናት የሚቆይ ስልጠና ለመንግስትና ለግል ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን መስጠት ጀመረ፡፡
በዚህም በሞዴል ኢንተርፕራይዞች ላይ የካይዘን ትግበራ የሚደረግ ሲሆን ለኢንተርፕራይዞች ሠራተኞች የጥራትና ምርታማነት ማሻሻያ (ካይዘን) ትግበራ ስልጠና/ድጋፍ በመስጠት ማብቃት እና የመስሪያ/ ማምረቻ ወርክሾፖችን በካይዘን እንዲደራጁ በማድረግ ኮሌጆች ከኢንተርፕራይዞች ጋር የሚኖራቸዉን የስራ ትስስር ለማጠናከርና የኢንተርፕራይዞችን ሠራተኞች መሰረታዊ የካይዘን እዉቀትና ክህሎትን በኢንተርፕራይዙ ማምረቻ/የስራ ቦታ በመተግበር ደረጃዉን የጠበቀ ማምረቻ ቦታ ለመፍጠር እና በአጠቃላይ የካይዘን ፍልስፍናን በመተግበር የአሰልጣኝ መምህራኑን አቅም በመገንባት የኢንተርፕራይዞችን አላስፈላጊ ብክነቶችን በማስወገድ ምርትና ምርታማነትን ለማሻሻል አቅም የሚፈጥር ስልጠና ይሆናል፡፡
ኤጀንሲው ከኮሌጆች ጋር በመሆን የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ድጋፍ በመስጠት በአስተዳደሩ ጉልህ ስራዎችን እየሰራ ሲሆን በተለይም በ4ቱ የድጋፍ ማእቀፎች የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን የምርትና ምራታማነት በማሻሻልና ብቁ የሆነ የሰዉ ሃይል በማፍራትና የሥራ እድል እንዲፈጥሩ ለማድረግ ድጋፍ እየሰጠ ይገኛል፤ በዚህም በአስተዳደሩ ዘጠኙም ወረዳዎች ለሚገኙ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ድጋፍ ለሚደረግላቸው ኢንተርፕራይዞች የድርጊት መርሀ ግብር በማዘጋጀት ከተለመደው 5ቱ ማዎች በተሻሻለው አድቫንስድ ካይዘን ትግበራ እንደሚደረግ የቢሮው ም/ኃላፊና የኤጀንሲው ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ገልጸዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 9/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች ስለ ቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ያላቸው ግንዛቤ ከሚፈለገው እኳያ ዝቅተኛ መሆኑ ተገለፀ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት በአስተዳደሩ ለሚገኙ የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ርዕሰ መምህራንና የተማሪ ተወካዮችን የግንዛቤ መስጫ መድረክ አካሂዷል::
ፕሮጀክቱ በቀጣይ በሚኖረው የ5 አመት ትግበራ በኮሌጅ የሚሰጡ የሞያ ስልጠናዎች በእስተዳደሩ የሚገኙትን የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች የሚገኙ ተማሪዎችን ማእከል ያደረገ እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን ለዚህም ለአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ርዕሰ መምህራንና የተማሪ ተወካዮች ስለ ዘርፉ በቂ ግንዛቤ መፍጠር ተቀዳሚው ተግባር በመሆኑ ይህ መድረክ መዘጋጀቱም ተገልፇል::
በመድረኩ ለተሳታፊዎች መልዕክት ያስተላለፉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በንግግራቸው የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች ላይ ስለ ቴክኒክና ሙያ በቂ ግንዛቤ ባለመፈጠሩ ምክንያት ወጣቶቹ በዘርፉ የሚኖራቸውን ተጠቃሚነት ባለመገንዘብ ህይወታቸውን በማይለውጡ የትምህርት መስኮች ላይ እድሜያቸውን እያባከኑ እንደሚገኙ ገልፀው በስተመጨረሻም የተማሩትን ዲግሪ አስቀምጠው ሌሎች ስልጠናዎችን ለመውሰድ ወደ ኮሌጁ እንደሚመጡም አስታውሰዋል::
የኮሌጁ ዲን አክለውም በአስተዳደሩ የሚገኙ የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ከኮሌጁ ጋር በመቀናጀት ተማሪዎቹ ላይ ተገቢውን የግንዛቤ የመፍጠር ስራ በመስራትና ተማሪዎቻቸው የ12 ክፍል መልቀቂ ፈተና ከመውስዳቸው አስቀድሞ ተማሪዎቹን በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ እሳቤ መቅረፅ የሁላችንም ድርሻ መሆን እንደሚግባውም አፅዕኖት ሰተው ተናግረዋል::
በኢንዱስትሪው ዘርፍ ሰፊ የክህሎት ክፍተት እንዳለ የተጠቀሰ ሲሆን በየፋብሪካዎች ተቀጥረው የሚሰሩ ወጣቶችም ዝቅተኛ ክህሎቶች(Low skills) ላይ አየሰሩ ያሉ መሆናቸውም ተመላክቷል::
በመድረኩ የSTEM(Science,Technology, Engineering,Mathematics)ፅንሰ ሃሳብና ምንነት ዙሪያ በኮሌጁ ምክትል ዲን እና የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽና ቴክኖሎጂ ሽግግር ስራ ሂደት ሃላፊ አቶ ተሾመ ሸዋዬ በኩል ለመድረኩ ተሳታፊዎች ቀርቧል::
የመድረኩ ተሳታፊዎች
በበኩላቸው በዘርፉ በሚፈለገው ልክ ውጤት እንዳይመጣ ተግዳሮት ሆነዋል ያሏቸውን ምክንያቶች በዝርዝር ያስቀመጡ ሲሆን በቀጣይም ከኮሌጁ ጋር በቅንጅትና በባለቤትነት ለመስራት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ እንደሆኑና የሚታዩ ክፍተቶችንም በዘላቂነት መፈታት እንደሚሹ ሀሳብ አስተያየታቸውን ሰተዋል::
ኮሌጁ በቀጣይ በአስተዳደሩ ከሚገኙ የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ጋር የጋራ መግባብያ ሰነድ በመፈራረም ወደ ትግበራ እንደሚገባም በመድረኩ ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
ታህሳስ 9/2017 ዓ.ም
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
