Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
Kanalga Telegram’da o‘tish
Ko'proq ko'rsatish
1 112
Obunachilar
+224 soatlar
+107 kunlar
+3730 kunlar
Postlar arxiv
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+3
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለአራተኛ ዙር ያሰለጠናቸውን መካኒክ አሽከርካሪዎችን በዛሬው አስመረቀ፡፡
በሀገራችን እንዲሁም በድሬዳዋ አስተዳድር መካኒክ አሽከርካሪዎችን በማፈራት የትራፊክ አደጋን መቀነስ እና አለም አቀፍ ተወዳዳሪ አሽከርካሪዎችን ማፍራት ላይ ትኩረቱን ያደረገ የአራተኛ ዙር ስልጠና ያጠናቀቁ አሽከርካሪዎችን በዛሬው የተመረቁ ሲሆን፡፡
በምርቃቱ መርሃ ግብር ላይ በመገኘት መልእክት ያስተላለፉት የኮሌጁ አውቶሞቲቭ ትምህርት ክፍል ተጠሪ አ/መር አሸናፊ ዘገየ እንዳሉት ይህ ስልጠና ብቃት ያለው መካኒክ አሽከርካሪዎችን በማፈራት የትራፊክ አደጋን መቀነስ ላይ ትኩረቱን አድርጎ በኮሌጁ የተሰጠውን ስልጠና ወስዳችሁ ላጠናቀቃችሁ ባለሙያዎች በቅድሚያ እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እወዳለሁ ያሉ ሲሆን አያይዘውም የስልጠናውን ውጤት በተግባር በመፈጸም በየእለቱ ልትተገብሩት ይገባል ብለዋል፡፡
መካኒክ አሽከርካሪዎች ስልጠና ይህ የአራተኛ ዙር ሲሆን በዚህም ስልጠና ከ27 በላይ አሽከርካሪዎች የተሳተፉበት እንደሆነና ቀጣይ ዙር ስልጠናም በጥቂት ጊዜያት ውስጥ እንደሚጀመር በእለቱ ተገልጿል ፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ሰኔ 9/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+4
በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የEASTRIP 4ኛ ሩብ ዓመት የቅሬታ አፈታት ኮሚቴ (GRC) መደበኛ ስብሰባ ባለድርሻ አካላትና የኮሌጁ ቅሬራ ሰሚ ኮሚቴ በተገኙበት በዛሬው እለት ተከናወነ፡፡
በዛሬው እለት የተከናወነው የኮሚቴው ስብሰባ በዋናነትበኮሌጁ በሚገኙ ሁለቱ ግዙፍ ፕጀክቶች ማለትም በEASTRIP እና SIFA ፕሮጀክቶች የአካባቢና ማህበራዊ ጥበቃ ተግባራት አፈፃፀምን ለመገምገም፣ የቅሬታ አስተዳደር ሁኔታን ለማየት እና ከፕሮጀክት መስፈርቶች ጋር ያለውን ተገዢነት ማረጋገጥ ላይ ትኩረቱን አድርጓል።
በዚህም ሁለቱ ግዙፍ ፕጀክቶች የተከናወኑ የቅሬታ አስተዳደርና የአካባቢና ማህበራዊ ጥበቃ ተግባራት አፈፃፀምን ላይ የተገኙ ለውጦች፣ ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እና የማሻሻያ እርምጃዎች ላይ በስብሰባው ላይ የተገኙ አካላት በጋራ ተወያይተዋል።
በተጨማሪም በባለድርሻ አካላት መካከል ያለውን ቅንጅት ለማጠናከር፣ የቅሬታ አፈታት ሥርዓቱን የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ እና የአካባቢና ማህበራዊ ጥበቃ ተግባራትን ለማሻሻል የሚያግዙ ምክረ ሃሳቦችና የተግባር እቅዶች የተለዩ ሲሆን በስብሰባው የተሰጡ አቅጣጫዎች ወደፊት የፕሮጀክቶቹን አፈፃፀም ለማሻሻል፣ የቅሬታ አያያዝን ለማጠናከር እና የፕሮጀክት ዓላማዎችን በተሳካ ሁኔታ ለማሳካት አስፈላጊ መሠረት ይሆናሉ።
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ሰኔ 9/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
#ዜና | በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከ140 ሚሊዮን ብር በላይ የፈሰሰበት የዲጂታል መሠረተ ልማት ተመረቀ
#DireTvአማርኛ | ሰኔ 8 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ
በድሬዳዋ አስተዳደር በሚገኘው የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ @ቴክኒክ ኮሌጅ፣ በ"ትምህርት እና ክህሎት ለሥራ ዕድል ፈጠራ ፕሮጀክት" (EASE) አማካኝነት ከ140 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነቡ ዘመናዊ የዲጂታል መሠረተ ልማቶች በዛሬው ዕለት ተመርቀዋል።
የኮሌጁን ተቋማዊ አሠራር ለማዘመንና የመማር-ማስተማር ሂደቱን ለማቀላጠፍ የተገነቡት እነዚህ መሠረተ ልማቶች ዘመናዊ ዳታ ሴንተር እና የውስጥ የኔትወርክ መሠረተ ልማት ግንባታ፣ የኢ-ለርኒንግ (e-Learning) ላብራቶሪ፣ ተቋሙን መረጃዎች ተደራሽ የሚያደርግ ዳይናሚክ ዌብሳይት ይዟል።
በምርቃት ሥነ ሥርዓቱ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው፣ የፌደራል ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት ምክትል ዳይሬክተርና የEASE ፕሮጀክት አስተባባሪ ዶክተር ሀብቶም ገብረእግዚአብሔር፣ እንዲሁም የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
አቶ ሮቤል ጌታው እንዳሉት
"መንግሥት የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆችን @topfans ለማደራጀት በሚያደርገው ጥረት ውስጥ ይህ የዲጂታል መሠረተ ልማት ለኮሌጁ ማኅበረሰብ ፈጣንና አስተማማኝ የመረጃ ተደራሽነትን በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል።"
የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ
"ኢትዮጵያ በ2030 ዓ.ም የተቋማትን አገልግሎት ሙሉ በሙሉ በዲጂታል ሥርዓት ለማስተሳሰር የያዘችውን ብሔራዊ ዕቅድ ከግብ ለማድረስ ይህ ፕሮጀክት ትልቅ እርምጃ ነው። በሥራ ሂደት ውስጥ የሚታዩ ክፍተቶችን በመቅረፍም በቴክኖሎጂ የሰለጠነና በሙያ የጎለበተ የሰው ኃይል ለማፍራት ያስችላል።" ብለዋል።
አዲሱ የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት የኮሌጁን የመማር ማስተማር ሂደት ከማቀላጠፉም በላይ፣ ለተማሪዎችና መምህራን ሰፊ የመረጃ ነፃነትና ቀልጣፋ አገልግሎት የሚፈጥር በመሆኑ የላቀ ተስፋ ተጥሎበታል።
ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት አማራጮች ያግኙ፡-
በፌስቡክ -https://www.facebook.com/share/19wDiZAD7x/?mibextid=wwXIfr
በቴሌግራም -https://t.me/EIPC2001
በቲክቶክ -https://www.tiktok.com/@ethioitaly2001?_t=ZM-90MxIrBN8qe&_r=1
በዌብሳይት - https://ethioitalypolytechniccollege.com/
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
ታላቅ የምስራች ለፋሽን አልባሳት 👗 አድናቂዎች በሙሉ
ልዩ የፋሽን አልባሳት ትርኢት በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሰኞ 8/2018 ዓ.ም ⌚️ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
ኮሌጁ ወጣቶችን በእውቀት፣በክህሎት እና በአመለካከት የታነጹ እንዲሆኑ እየሰራ ያለው ስራ የሚበረታታ ነው ተባለ፡፡
በድሬዳዋ አስተዳደር ወረዳ 08 እና የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በመተባበር የ2018 ዓ.ም የወጣቶች የሥራ ክህሎት እና የሙያ ስልጠና ማጠቃለያ መርሃ ግብር ተከናወነ፡፡
በመርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የአስተዳደሩ ኮንስትራክሽን ቢሮ ም/ኃላፊ የሆኑት ክቡር አቶ ኢማጅ አብደላ ሲሆኑ በንግግራቸውም ወጣቶችን በክህሎትና በእውቀት ከማብቃት ባሻገር በአመለካከት የዳበሩ ሃገር ገንቢ እንዲሆኑ በርካታ ስራዎች ሊሰሩ ይገባል፡፡ይህ ስራ ደግሞ በአንድ ወገን ብቻ የሚሰራ ሳይሆን ሁሉም ባለድርሻ አካላት በጋራ ሊሰሩ ይገባል ያሉ ሲሆን አያይዘውም የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ወጣቶችን በእውቀት፣በክህሎት እና በአመለካከት የታነጹ እንዲሆኑ እየሰራ ያለው ስራ ለሌሎችም እንደ ተሞክሮ ሊወሰድ የሚገባው ነው ብለዋል፡፡
የወረዳው ዋና ስራ አስፈጻሚ አብዱልአዚዝ አሜ በበኩላቸው የአካባቢው ወጣቶች ሙያና ክህሎት እንዲኖራቸው እንዲሁም አመለካከታቸው የተቀየረና ከራስ አልፈው ለሀገር የሚተርፉ ወጣቶች እንዲሆኑ ወረዳው በየቀኑ የሚሰራው ዋናው ስራው ነው ይህም ስራችን የተሳካ እንዲሆን የድሬዳዋ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ እንዲሁም የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አብረውን እየሰሩ ይገኛል ለዚህም ምስጋናችን ከፍ ያለ ነው ብለዋል፡፡
ኮሌጁን በመወከል ንግግር ያደረጉት የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ም/ዲን አቶ ቢቂላ ታደሰ ሲሆኑ የአካባቢው ማህበረሰብ በተለይ ወጣቶች አምራች ዜጋ እንደመሆናቸው መጠን በስልጠናና በክህሎት የዳበሩ እንዲሆኑ መስራት ያስፈልጋል ለዚህ ደግሞ ኮሌጃችን በረጃጅምና በአጫጭር ስልጠናዎች ወጣቶችን የማብቃት ስራ በሰፊው እየሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡
በዛሬው እለት ከወረዳ 08 የተውጣጡ ከ50 በላይ ወጣቶች በኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታና በኮንስትራክሽን ፊኒሺንግ ስራ የተመረቁ ሲሆን ሰልጣኞችም በስልጠናው ወቅት ያገኙት እውቀትና ክህሎት ተጠቅመው እራሳቸውን ሊለውጡ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ሰኔ 6/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር ስራ ክህሎት ቢሮ የስራ እድል ፈጠራ ምክር ቤት የ2018 በጀት ዓመት መደበኛ ጉባኤውን አካሂዷል።
ምክር ቤቱ በመደበኛ ጉባኤም የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በስራ እድል ፈጠራ በበጀት አመቱ የተሰሩ የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ ጥልቅ ግምገማውን አካሂዷል።
+3
100 ሺህ ወጣቶችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚ የሚያደርግ ፕሮግራም ይፋ ሆነ
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር “ብቃት” የተሰኘ 100 ሺህ ወጣቶችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚ የሚያደርግ ፕሮግራም ይፋ አድርጓል።
ሚኒስቴሩ የወጣቶችን የሥራ አጥነት ችግር ለመፍታት ከዓለም ባንክ ጋር በመተባበር “ብቃት'” የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራምን በ11 ከተሞች ሲተገብር ቆይቷል፡፡
አሁን ላይም ይህንን የሥራ ዕድል ወደ 27 ከተሞች በማስፋት 100 ሺህ ተጨማሪ ወጣቶችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ፕሮግራም ነው ይፋ ያደረገው፡፡
ፕሮግራሙ በዓለም ባንክ 52 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ በሚቀጥሉት 2 ዓመታት የሚተገበር ሲሆን÷ ከ18 እስከ 29 የዕድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ወጣቶችን ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡
በማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ ላይ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴዔታ ሰለሞን ሶካን ጨምሮ የክልሎች የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
©️ኤፍ ኤም ሲ
በድሬዳዋ ባለፉት አመታት ለነዋሪዎች የስራ ዕድል ለመፍጠር የተሰሩ ተግባራት ውጤታማ ናቸው - ኢዜአ አማርኛ https://share.google/2jfdzOukM3qR6esJp
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+9
በአፍሪካ ደረጃ ለሚደረገው የካይዘን ውድድር የተመረጠው አንጋፋው የምስራቅ አፍሪካ የቴክኒክና ሙያ የልህቀት ማእከል የሆነው የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በካይዘን ፅንሰ-ሃሳብ እያከናወናቸው የሚገኙ ዘርፈ ብዙ ተግባራትና ወቅታዊ አፈፃፀም ላይ በዚህ አመት ባሳየው ምርጥ ተሞክሮ በኢትዮጵያ ከሚገኙ 13 አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ውስጥ አንዱ በመሆን ለአፍሪካ የካይዘን ውድድር ተመርጧል፡፡
ከዚህ በፊት የሀገር አቀፍ የካይዘን ውድድር አካል በሆነውና ከፌደራል በመጡ ባለሙያዎች በተካሄደው ምዘና በኮሌጁ የስራ ቦታን ምቹ ከማድረግ ፤ ብክነትን ከመቀነስ፤ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትና ፍጥነትን ከማሻሻል አኳያ በተቀመጡ መመዘኛዎች የተከናወኑ ተግባራትን ለገምጋሚው ቡድን በበቂ ሁኔታ ያስረዳ በመሆኑና የሚሰራቸው ስራዎች ከራስ አልፎ ለሌሎችም ተቋማት ጭምር የሚተርፍ በመሆኑ ለዚህ በአፍሪካ ደረጃ እንዲወዳደሩ ከተመረጡ 13 አገልግሎት ሰጪ ተቋማት መካከል አንዱ በመሆን በትናንትናው እለት ለአወዳዳሪው አካል የኮሌጁን አፈጻጸም በበይነ መረብ አቅርቧል፡፡
በዚህም መሰረት በኮሌጁ የካይዘን ትግበራ አጠቃላይ የአፈፃፀም እንዲሁም ከ8ቱ የውጤት አመላካች አኳያ የተገኙ ውጤቶችን በገለጻው ወቅት ለገምጋሚ ቡድኑ በበይነ መረብ ማስረዳት ተችሏል::
በዚህ አንጋፋ ኮሌጁ ያለው በትምህርትና ስልጠና፣በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅ ለኢንተርፕራይዞች እና ኢንዱስትሪዎች የማሻገር ተሞክሮዎች ከራስ አልፎ ለሌሎችም የሚተርፍ እንደመሆኑ መጠን በኮሌጁ ያለውን እምቅ አቅም በጋራ እንጠቀም ሃገራችንንም ወደተሸለ ልማት እንውሰድ፡፡
"ዛሬን እናሻሽል፤ ብክነትን እንቀንስ፤ ጥራትና ፍጥነትን እንጨምር፤ ነገን እንገንባ"!!
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ሰኔ 5/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
በአስተዳደሩ በገጠር ስራ እድል ፈጠራ በተከናወነው የተቀናጀ ርብርብ አመርቂ ውጤት ተመዝግቧል..የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ እድል ፈጠራ ምክር ቤት የ2018 በጀት ዓመት መደበኛ ጉባኤውን በዛሬው እለት አካሂዷል።
በጉባኤውም ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያካሄዱት የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር እንደገለጹት በአስተዳደሩ የስራ ዕድል በመፍጠር የዜጎች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በማሳደግ በሀገር ኢኮኖሚ ውስጥ ዘላቂ ለውጥ ለማምጣት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
የስራ ዕድል ፈጠራ የዜጎች የኑሮ ደረጃ በማሻሻል ድህነትን ለመቀነስ ፍትሀዊ እድገት ለማረጋገጥ ሚናው ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም በአስተዳደሩ በባለፉት ዓመታት በስራ እድል ፈጠራ የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ስራዎች መሰራታቸውን ፣በተለይም በበጀት ዓመቱ በገጠር ስራ እድል ፈጠራ በተደረገው የተቀናጀ ርብርብ አመርቂ ውጤት መመዝገቡን አስረድተዋል።
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸውም በበኩላቸው ዘላቂና አስተማማኝ የስራ ዕድል በመፍጠር የዜጎች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በማሳደግ በሀገር ኢኮኖሚ ውስጥ ለውጥ ለማምጣት ቢሮው በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
በበጀት ዓመቱም በግብርና፣ በኢንድስትሪ እና በአገልግሎት ዘርፍ የተሰሩ ስራዎች አበረታች መሆኑን አስታውቀዋል።
በጉባኤውም የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ ጥልቅ ውይይት ተደርጎበታል።
በመድረኩ ማጠቃለያም ክቡር ከንቲባ ከድር ጁሀር ተሳታፊዎች ላነሷቸው ሀሳብ አስተያየት ምላሽ እና ማብራሪያ እንዲሁም የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን ሰጥተው የእለቱን ጉባኤውን አጠናቋል።
©️DGC ሰኔ 5/2018
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ እድል ፈጠራ ምክር ቤት የ2018 መደበኛ ጉባኤ ማካሄድ ጀምሯል
#DGC ሰኔ 5/2018
ምክር ቤቱ በመደበኛ ጉባኤም የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በስራ እድል ፈጠራ በበጀት አመቱ የተሰሩ የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ ግምገማ ያደርጋል።
በመድረኩም የየድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር፣ የካቢኔ አባላት፣ የምክር ቤቱ አባላት፣የዘርፉ አመራሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኘተዋል።
***********
Yaa'iin Idilee Mana Marii Carraa Hojii Uumuu Biiroo
Hojiifi Ogummaa Bulchinsa Dirree Dhawaa Gaggeeffamaati Jira.
Waltajjii Kanarratti Kabajamoo Kantibaa Bulchinsa Dirree Dhawaa Obbo Kadiir Juhaar, dabalatee Miseensonni Kaabinee Bulchinsaa, Hoggantoonni Olaanoo Bulchinsaa, Gaggeessitoonni Aanaalee Bulchinsaafi daayreektoerrtonnifi ogeeyyiin Biiroo Carraa Hojiifi Ogmmaa,fi Dhaabbilee Leenjiifi Ogummaa Bulchinsa Dirree Dhawaarraa Argamaniiti jiran.
Biiroon Dhimmoota Komunikeeshinii Bulchinsa Dirree Dhawaa Odeeffannoowwan jiran hordofuun kan isin biraan gahu ta'a.
***********
#Warka Waxaa hada socda oo bilabamay kalfadhiga caadiga ah ee golaha shaqo abuurka ee 2018,oo soo aggasimay xafiska Shaqada iyo xirfadaha ee is Maamulka Diridhaba.
Golaha ayaa dib u eegi doona warbixinta hirgalinta qorshayaasha la hirgaliyay sanad miisaaniyeedka ee loogu talagalay abuurista shaqada si loo hubiyo faa'iidada wadajirka ah ee muwaadiniinta.
Duqa Magaalada Diridhaba , mudane Kkadir Juhar, xubnaha golaha kabineedka, hoggaaminta dagmooyinka qaybaha iyo marti sharaaf kale ayaa goob joog ka ahaa madashaa kalfadhigii
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ በአስተዳደሩ ከተማና ገጠር የትምህርትና ስልጠና ተደራሽነትና ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ስራዎች ትኩረት እንደተሰጣቸው ተገለጸ።
በአስተዳደሩ አራቱም የገጠር ወረዳዎች የቴክኒክና ሙያ (TVET) ተንቀሳቃሽ ስልጠና በአምስት ሙያዎች ማለትም በከብት፣ በበግ፣ በፍየል፣ በዶሮ እና በንብ እርባታ ማሰልጠኛ ሞጁሎችን በኦሮምኛ ቋንቋ የተተረጎሙትን በመከለስ ወደፊት ሞጁሎቹን በፓይለት ፕሮግራም በመፈተሸ ማስተካከያ በማድረግ ለስልጠና እንዲውሉ የሚመቻች ይሆናል፡፡
በዚህም በአስተዳደሩ ገጠር ተደራሽ ያልሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች፣ ሥራ ፈላጊ ወጣቶች እና የአርብቶ አደር ማህበረሰቦች በተደራሽነት ረገድ የሚስተዋሉ ውስንነቶችን በመቅረፍ በተለይም የገጠር ወጣቶች በቀላሉ እንዲጠቀሙ ተጨማሪ የስልጠና ማዕከላት፣ የሞባይል ስልጠና ፕሮግራሞች እና የቅርንጫፍ ስልጠና ማዕከላት እተመቻቹ ይገኛሉ ።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሰኔ 5/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ