ar
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

الذهاب إلى القناة على Telegram

إظهار المزيد
1 067
المشتركون
-224 ساعات
-67 أيام
+430 أيام
أرشيف المشاركات
ለንግድ ፈጠራ ሃሳብ ውድድር ተወዳዳሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ፤ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት በ2018 ዓ.ም ለሚደረገው ብሩህ የንግድ ፈጠራ ሃሳብ ውድድር መወዳደር የሚፈልጉ እንዲመዘገቡ በማስታወቂያ አሳውቆ መመዝገቡ ይታወሳል በዚህም ለውድድሩ የሚያስፈልጉ መመሪያዎችን እና አሰራሮችን በማዘጋጀት የተወዳዳሪዎችን ሰነድ በመመርመርና በመለየት ስልጠና ሰጥቷል፤ ውድድሩ የሀሳብ  ስለሆነ ተወዳዳሪዎች ከሀሳብ ደረጃ ወጥተው ዕውን የሚያደርጉበትን ብቃት እንዲያገኙ ድጋፍ የሚደረግላቸው ሲሆን ድጋፉም ማሰልጠን፣  መሸለምና  ማብቃት በሚል ሶስት ደረጃዎችን ያልፋል፤ በመሆኑም በዋናነት በየዘርፉ የሚታዩ ዋና ዋና ተግዳሮቶችን መቅረፍ ላይ ያተኮሩ አዳዲስ የንግድ ፈጠራ ሀሳቦችን ማመንጨት የሚችሉበትን እና የአካባቢያቸውን ጸጋዎች ለይተው በፈጠራ ሀሳብ በመደገፍ ጥቅም ላይ ማዋልን እንዲያዳብሩ ስልጠናው መዘጋጀቱን የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ ተናግረዋል፡፡ በዚህም ውድድሩ ተወዳዳሪዎች ከሀሳብ ደረጃ ወጥተው ዕውን የሚያደርጉበትን ብቃት እንዲያገኙ ድጋፍ የሚያገኙበትን ሁኔታ የሚያመቻች በመሆኑ አሸናፊ የሚሆኑ በቀጣይ በመሸለምና በማብቃት ሂደት ውስጥ የሚበረታቱ እንደሚሆን ገልጸዋል፤ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ግንቦት 14/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+8

የተደራጁ ኢንተርፕራይዞችን ከሥራ ጋር ማስተሳሰር የሥራ ዕድል መፍጠሩ ዋነኛ ተልዕኮ ማስፈጸሚያ አቅም መሆኑ ተገለጸ፤ የኢትዮ ቴሌኮም ሊሰራ ላሰበው የኮንስትራክሽን ግንባታ በዘርፉ የተደራጁ ኢንተርፕራይዞች ተለይተው እንዲላኩ በቀረበ ጥያቄ መሠረት የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ በስሩ የሚገኙ በህጋዊ መንገድ የተደራጁና መስፈርቱን የሚያሟሉ አስራ ሰባት ኢንተርፕራይዞች ሁሉም በተገኙበት ግልጽ የዕጣ ማውጣት መርሃግብር አካሄደ። በዕጣ ማውጣት መርሃግብሩ ላይ የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው የተገኙ ሲሆን የስራ ዕድል መፍጠር የቢሮው ዋነኛ ተልዕኮ መሆኑን ገልጸው ኢንተርፕራይዞችን ከገበያ ጋር ለማስተሳሰር ቢሮው ከግልና ከመንግስታዊ ድርጅቶች ጋር በቅንጅት እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ግንቦት 14/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+4

በዚህ መሠረት ማንኛውም የ"ከወንጀል ነጻ" ማረጋገጫ የሚፈልግ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አመልካች፦ ✅ወደ አዲስ አበባ ፌዴራል ፖሊስ ፎረንሲክ ማዕከል በአካል መገኘት አይጠበቅበትም ✅በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት (lmis.gov.et) ላይ በመመዝገብ፣ በአቅራቢያቸው በሚገኙ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎች አስፈላጊውን የባዮሜትሪክስ መረጃ መስጠት ይኖርባቸዋል፤ ✅የ"ከወንጀል ነጻ" ማረጋገጫ ሰርተፊኬቱን የሥራ ስምሪት ሂደቱን በሚያስፈጽመው ሕጋዊ ኤጀንሲ አማካኝነት በቀላሉ ማግኘት ይቻላል፣ ይህ አገልግሎት በራስ ጥረት የሚገኙ የሥራ ዕድሎችን ለጊዜው አያካትትም፤

የ"ከወንጀል ነጻ" ማረጋገጫ ሰርተፊኬት አገልግሎትን በዲጂታል አማራጭ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አገልግሎት አሰጣጡን በማዘመን ይበልጥ ቀልጣፋ፣ ተደራሽ እና ግልጽነት የተላበሰ ለማድረግ ሰፊ ርብርብ እያደረገ ይገኛል። ይህን ተግባር ይበልጥ በማጠናከር፣ የ"ከወንጀል ነጻ" ማረጋገጫ ሰርተፊኬት አሰጣጥ ስርዓቱን ከኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት (lmis.gov.et) ውስጥ እንዲካተት ማድረግ ተችሏል። በዚህም በውጭ ሀገር የሥራ ስምሪቱ ተጠቃሚ የሚሆኑ ዜጎች አገልግሎቱን ባሉበት ሆነው እንዲያገኙ ያስችላቸዋል። ቀደም ሲል አመልካቾች ሰርተፊኬቱን ለማግኘት አዲስ አበባ በሚገኘው የፌዴራል ፖሊስ ፎረንሲክ ማዕከል በአካል መገኘት ግዴታ የነበረባቸው ሲሆን፤ በአዲሱ የዲጂታል ስርዓት አማካኝነት ግን ዜጎች ሂደቱን ባሉበት ሆነው በቀላሉ ማጠናቀቅ ይችላሉ። በዚህ መሠረት ማንኛውም የ"ከወንጀል ነጻ" ማረጋገጫ የሚፈልግ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አመልካች፦ ✅ወደ አዲስ አበባ ፌዴራል ፖሊስ ፎረንሲክ ማዕከል በአካል መገኘት አይጠበቅበትም ✅በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት (lmis.gov.et) ላይ በመመዝገብ፣ በአቅራቢያቸው በሚገኙ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎች አስፈላጊውን የባዮሜትሪክስ መረጃ መስጠት ይኖርባቸዋል፤ ✅የ"ከወንጀል ነጻ" ማረጋገጫ ሰርተፊኬቱን የሥራ ስምሪት ሂደቱን በሚያስፈጽመው ሕጋዊ ኤጀንሲ አማካኝነት በቀላሉ ማግኘት ይቻላል፣ ይህ አገልግሎት በራስ ጥረት የሚገኙ የሥራ ዕድሎችን ለጊዜው አያካትትም፤ ይህ የተቀናጀ አሰራር በዜጎች ላይ ይደርስ የነበረውን አላስፈላጊ የጊዜ፣ የጉዞ ወጪ እና የአስተዳደራዊ ጫናን በከፍተኛ ሁኔታ የሚቀንስ ሲሆን፤ በመንግስት በተቋማት መካከል ያለውን ቅንጅት በእጅጉ የሚያሳድግ ነው። የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የዲጂታል አገልግሎት ስርዓቶቹን በማስፋፋት የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማላቅ ከሁሉም አስፈጻሚ አካላት ጋር በመቀናጀት የጀመረውን ሥራ አጠናክሮ ይቀጥላል። የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ግንቦት  7/2018 ዓ.ም፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር Official Website: mols.gov.et Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE Telegram: https://t.me/FDRE_MoLSofficial TikTok: tiktok.com/@mols_official Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYI

በድሬዳዋ ለገጠር አነስተኛና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች ሲሰጥ የነበረው የሙያ ክህሎት ስልጠና ተጠናቀቀ ​የድሬዳዋ አስተዳደር ግብርና፣ መዓድንና ኢነርጂ ቢሮ የቆላማ አካባቢ ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት ከአስተዳደሩ የስራና ክህሎት ቢሮ ጋር በመተባበር፣ ከተለያዩ የገጠር ክላስተሮች ለተውጣጡ አነስተኛና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች ሲሰጥ የነበረውን የሙያ ክህሎት ስልጠና አጠናቋል። በቴክኒክና ሙያ (TVET) ደረጃ በተሰናዳው በዚህ ስልጠና ላይ ከ60 በላይ ወጣቶች ተሳትፈዋል። ​በስልጠናው ማጠቃለያ መርሃ ግብር ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የግብርና፣ መዓድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ አቶ ኑረዲን አብደላ እንደገለጹት፤ ስልጠናው እንደ ሀገር የተያዘውን ድህነትን የመቀነስና የስራ አጥነት ቁጥርን የመቀነስ እቅድ ለማሳካት አይነተኛ አስተዋፅኦ አለው። ወጣቶችም የተሰጣቸውን የስልጠና ዕድል በአግባቡ በመጠቀም የራሳቸውንና የሌሎችን ህይወት ማሻሻል እንዳለባቸው አሳስበዋል። ​የቆላማ አካባቢ ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት በገጠር አካባቢዎች የስራ ዕድል ፈጠራ ላይ በስፋት እየሰራ እንደሚገኝ የገለጹት ደግሞ የፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ ኢሳም ሐሰን ናቸው። በተለይም ወጣቶች በማህበር ተደራጅተው ስልጠናውን እንዲወስዱ ከተደረገ በኋላ፣ ወደ ስራ መግቢያ የሚሆን ለእያንዳንዳቸው ከ1.4 ሚሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ድጋፍ እንደሚደረግላቸው አስታውቀዋል። ይህ ድጋፍ ፕሮጀክቱ ለማህበራቱ ለስራ ከሚያስፈልገው አጠቃላይ ወጪ 90 በመቶውን (90%) የሚሸፍን መሆኑንም አብራርተዋል። ​የስራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ ፈጡም ሙስጠፋ በበኩላቸው፤ እንዲህ ያሉ ክህሎትን መሰረት ያደረጉ ስልጠናዎች ወጣቶች ለስራ ፍለጋ ከገጠር ወደ ከተማ የሚያደርጉትን አላስፈላጊ ፍልሰት እንደሚያስቀሩ ገልጸዋል። ከዚህም ባሻገር ህብረተሰቡ የተለያዩ አገልግሎቶችን በቅርበት በአካባቢው እንዲያገኝ ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግ አስገንዝበዋል። ​በስልጠናው የተሳተፉ የማህበራት አባላት በሰጡት አስተያየት፤ የተሰጣቸው ስልጠና ወደፊት ለሚሰማሩበት የስራ መስክ ስኬት ትልቅ መነሳሳትና አቅም እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል። ​በመርሃ ግብሩ ማጠናቀቂያ ላይ ለሰልጣኞቹ የሙያ ማረጋገጫ ሰርተፍኬት የተበረከተላቸው ሲሆን፣ በቀጣይ ስራዎች ዙሪያም በግብርና፣ መዓድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ አማካኝነት የስራ መመሪያና አቅጣጫ ተሰጥቷል። ©️ DireTvአማርኛ | ግንቦት 12 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ

photo content
+9

ለኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን በInnovative Pedagogy ላይ ያተኮረ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል:: ለኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራን የተሰጠ የሚገኘው የInnovative Pedag
+9
ለኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን በInnovative Pedagogy ላይ ያተኮረ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል:: ለኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራን የተሰጠ የሚገኘው የInnovative Pedagogy ስልጠና በፌደራል ስራና ክህሎት ሚኒስቴር አዘጋጅነት ከፌደራል TVET ኢንስቲትዩት በመጡ የዘርፉ ባለሞያዎች እየተሰጠ የሚገኝ ሲሆን የስልጠናው ዋና ዓላማም የተለመደውን የማሰልጠኛ ስነ-ዘዴ ለማሻሻልና ጊዜው የደረሰበትን ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም ትምህርትና ስልጠናውን ለማዘመን ያለም ስልጠና እንደሆነም ተገልፇል:: ይህ በኮሌጁ ለ5 ቀናት የሚቆየው ስልጠናም ባለፉት 15 ቀናት አሰልጣኝ መምህራኑ በOnline ሲከታተሉት የነበረውን የ Innovative Pedagogy ስልጠና በተግባር የሚሰለጥኑበት እንደሆነው ተመላክቷል:: ስልጠናው በሀገሪቱ በሚገኙና የEASE ፕሮጀክት በሚተገበባቸው 24 ፖሊቴክኒኮች ላይ ለሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን አየተሰጠ እንደሚገኝም ታውቋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ግንቦት 11/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

ለኢንተርፕራይዞች የሚሰጠው የድጋፍ አገልግሎት በተቀናጀና በተጠናከረ መንገድ መስጠት ትኩረት ተሰጥቶት እንደሚተገበር ተገለጸ፤ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት በአስተዳደሩ ከሚገኙ የሥራ ማዕከላት ጋር ከፌደራል በመጣ የሱፐርቪዥን ቡድን የተሰጠ ግብረመልስ ላይ  አጠቃላይ ውይይት አካሄደ፡፡ በዚህም በአስተዳደሩ ወረዳዎች ጉብኝት ሲደረግ እንደ ሃገር ዘርፉ የሚመራባቸውን እሳቤ አጥርቶ በየደረጃው ለሚገኙ የሚመለከታቸው አካላት የተልዕኮ ግልፅነት ፈጥሮ ከመስራት አኳያ በተለይም በሥራ ዕድል ፈጠራና በኢንተርፕራይዞች ልማት ላይ መሠረት ያደረጉ ተግባራት ላይ ያተኮረ ሆኗል፤ በመሆኑም የሥራ ማዕከላቱ የክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራና የኢንተርፕራይዞች ልማት ተግባራዊ በማድረጉ ረገድ ተግባራትን ከአጠቃላይ የኢኮኖሚ ልማት ሥራዎች ጋር አስተሳስሮ የመፈፀም አቅጣጫ አፈፃፀም በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝና ኢንተርፕራይዞች በሚያመርቱበትና አገልግሎት በሚሰጡበት ቦታ በአካል በመገኘት ጉብኝት የተደረገ ሲሆን በጉብኝቱም ለታዩ ጉዳዮች በሃሳብና በቀጣይ ድጋፍ የሚደረግበትን አግባብ የተመላከተበት ከዚሁ ጋር በተያያዘ ቀጣይ የስራ እንቅስቃሴን የሚያበረታታና የሚያጠናክር ግብረመልስ ቀርቦ ተወያይተዋል፡፡ በመጨረሻም በአስተዳደሩ ከተማና ገጠር ወረዳዎች ስር የሚገኙ የሥራ ማዕከላት ስር የሚገኙና በቢሮው ኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት የተለያዩ ድጋፎች የሚደረግላቸው ኢንተርፕራይዞችን ወደ ሞዴል ኢንተርፕራይዝነት ለማሳደግ የሚያስችል የመስክ ምልከታና ልየታን በቀጣይ በማጠናቀቅ በዚህም የተለዩ ሞዴል ኢንተርፕራይዞች በበጀት አመቱ መጨረሻ በአስተዳደር ደረጃ ዕውቅና የሚሰጥበት አግባብ ላይ ውይይት ተደርጓል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ግንቦት 7/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+5

በድሬዳዋ አስተዳደር ከ32 በላይ ቀጣሪ ድርጅቶችንና ሥራ ፈላጊ ምሩቃንን ያገናኘ መድረክ ተካሄደ ​በድሬዳዋ አስተዳደር የሚታየውን የሥራ አጥነት ቁጥር ለመቀነስና ወጣቶች በቀላሉ አስተማማኝ የሥራ ዕድል እንዲያገኙ የሚያስችል፣ ሥራ ፈላጊ ምሩቃንን ከቀጣሪ ድርጅቶች ጋር በቀጥታ የሚያገናኝ የሥራ ገበያ መድረክ ተካሄደ። ​በዚሁ መድረክ ላይ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎችና ኮሌጆች የተመረቁ በርካታ ሥራ ፈላጊዎች እንዲሁም ከ32 በላይ የግልና የመንግሥት ቀጣሪ ድርጅቶች ተሳስረዋል። ​የመድረኩን መክፈቻ ያደረጉት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጁሀር እንደገለጹት፤ ምሩቃኑ ያላቸውን እምቅ አቅምና የንድፈ-ሐሳብ ዕውቀት ለቀጣሪ ድርጅቶች ያለምንም መደናገጥ ማሳየት ይገባቸዋል ብለዋል። አያይዘውም ወጣቶቹ በሚቀጠሩባቸው ተቋማት ውስጥ በሥነ-ምግባር የታነጹ፣ ውጤታማና ብርቱ ሠራተኞች መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል። ​የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው፣ መድረኩ ከቀጥታ የቅጥር ዕድል ባለፈ ትልቅ ትምህርታዊ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል። ወጣቶች የገበያውን ወቅታዊ ፍላጎት በመረዳት የራሳቸውን የሥራ ፈጠራ ለመጀመር የሚያስችል መነሳሳት እንደሚፈጥርላቸው ጠቁመው፣ የተዘጋጀውን ዕድል በአግባቡ እንዲጠቀሙበት ጥሪ አቅርበዋል። ​ቀጣሪ ድርጅቶች በበኩላቸው "የምንፈልገውን ብቁ ባለሙያ በአንድ ማዕከልና በቀላል መንገድ ለማግኘት አስችሎናል፤ ይህም ለድርጅታችን ዕድገት የሚበጁ ስልጡን ወጣቶችን ለመምረጥ አመቺ ሆኖልናል።" ተብለዋል ። ​ሥራ ፈላጊ ወጣቶችም "ቀጣሪ ፍለጋ የሚባክነውን ጊዜና ጉልበት በመቆጠብ፣ በአንድ ቦታ በርካታ የሥራ አማራጮችን ለማነጻጸርና ራሳችንን ለገበያው ለማዘጋጀት ትልቅ አስተዋጽዖ አድርጓል።"ነው ያሉት። ​ይህ የሥራ ትስስር መድረክ በሥራ ፈላጊዎችና በቀጣሪዎች መካከል የነበረውን የመረጃ ክፍተት በመሙላት ረገድ ለሁለቱም ወገኖች የጎላ ጠቀሜታ እንዳለው ተመላክቷል። ©️ DireTvአማርኛ | ግንቦት 05፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ 

photo content
+9

በድሬዳዋ የቆላማ አካባቢ የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት ለአነስተኛና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች የክህሎት ሥልጠና መስጠት ጀመረ ​በድሬዳዋ አስተዳደር የቆላማ አካባቢ የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት ከገጠር ክላስተር ለተውጣጡ የአነስተኛና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች የክህሎት ማሻሻያ ሥልጠና መስጠት ጀመረ። ፕሮጀክቱ ከአስተዳደሩ የሥራና ክህሎት ቢሮ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ይህ ሥልጠና፤ የወጣቶችንና የሴቶችን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻልና የሥራ አጥነትን ለመቀነስ ያለመ ሲሆን ለተከታታይ አሥር ቀናት የሚቆይ ነው። ​የግብርና፣ መዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ አቶ ኑረዲን አብደላ በሥልጠናው መክፈቻ ላይ እንደገለጹት፤ ፕሮጀክቱ መንግሥት የያዘውን የምግብ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥ ዕቅድ ለማሳካት ከፍተኛ አስተዋጽዖ እያበረከተ ይገኛል። ሰልጣኞችም ሥልጠናውን በአግባቡ ተከታትለው ወደ ተግባራዊ የሥራ ምዕራፍ ሊሸጋገሩ እንደሚገባ አሳስበዋል። ​የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው፤ በከተማና በገጠር እየጨመረ የመጣውን የሥራ አጥነት ችግር ለመቅረፍ ዘርፈ-ብዙ ሥራዎች እየተሠሩ መሆኑን ገልጸው፤ ይህ ሥልጠና የገጠር ወጣቶችን አቅም በመገንባት ረገድ ፋይዳው የጎላ መሆኑን አስገንዝበዋል። ​የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ኢሳም ሁሴን የሥልጠናው ዋና ዓላማ የሴቶችንና የወጣቶችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ መሆኑን ጠቁመው፤ ሰልጣኞቹ ወደ ሥራ ሲሰማሩ ፕሮጀክቱ አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረጉን እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። ​ይህ የአሥር ቀናት ሥልጠና በግንባታ፣ በወፍጮ ሥራ፣ በዳቦ መጋገርና በሳሙና ማቀነባበር ዘርፎች ለተሰማሩ ስድስት ኢንተርፕራይዞች እየተሰጠ ይገኛል። ፕሮጀክቱ ባለፈው የበጀት ዓመት ድጋፍ የሚያደርግላቸውን ማኅበራት ቁጥር ከ15 ወደ 55 ያሳደገ ሲሆን፤ ለዚሁ ተግባር ከ55 ሚሊዮን ብር በላይ የፋይናንስ ድጋፍ ማድረጉ ተገልጿል። ከእነዚህ ማኅበራት መካከል 35 በመቶ ያህሉ በሴቶች የተደራጁ ናቸው። ©️ DireTvአማርኛ | ግንቦት 05፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ 

photo content
+6

በአስተዳደሩ ድጋፍ ወደ ተባበሩት አረብ ኤምሬትስ በመሄድ ለመስራት የተመዘገቡ ከ3 መቶ በላይ ወጣቶች የቅድመ ስምሪት ኦሬንቴሽን ተሰጠ የድሬዳዋ አስተዳደር ከዓለም አቀፍ የሥራ አገናኝ ኤጀንሲ ሰርኮ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ይህ መርሃ-ግብር፣ በከተማዋ የሚስተዋለውን የሥራ አጥነት ቁጥር ለመቀነስና ዜጎች በሕጋዊ መንገድ የውጭ ሀገር የሥራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማስቻል ያለመ ነው። በመድረኩ ላይ የተገኙት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሀር፣ ወጣቶች ለውጭ አገር ሥራ አገራቸውን ከመልቀቃቸው በፊት በስደት በሚሄዱበት አገር ያለውን ተጨባጭ የሥራ ባህልና ሁኔታ አስቀድመው መገንዘብ እንደሚገባቸው አሳስበዋል። በአስተዳደሩ ድጋፍ ወደ ተባበሩት አረብ ኢምሬትስ የሚጓዙት ወጣቶችም የሥራው ባህሪ የምቾት ቀጠናን የሚፈቅድ እንዳልሆነ የገለጹት ከንቲባው፣ ስኬታማ ለመሆን ከፍተኛ ዝግጁነትና መበርታት እንደሚጠይቅ አስገንዝበዋል። በተለይም አሁን የሚሰጠውን ስልጠና በአግባቡና በትኩረት መከታተል ዋነኛ የሥነ-ምግባር መገለጫ መሆኑን በመጥቀስ ወጣቶቹ ለሚገጥማቸው አዲስ የስራ ባህል ራሳቸውን እንዲያዘጋጁ መክረዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው፣ መርሃ-ግብሩ በዋናነት ሥራ ፈላጊ ወጣቶችን ለመደገፍ የታለመ መሆኑን ገልጸው፣ ወጣቶች የሚያገኙትን የሥራ ዕድል በአግባቡ በመጠቀም ራሳቸውን፣ ቤተሰባቸውንና አገራቸውን ለመደገፍ እንዲተጉ ጥሪ አቅርበዋል። በመድረኩ የተሳተፉት 350 ወጣቶች የተሰጣቸውን የቅድመ ስምሪት ኦሬንቴሽን ተከትሎ በሚደረገው የሙያ ምዘና ብቁ ሆነው ከተገኙ በኋላ፣ ሙሉ በሙሉ በሕጋዊና ደህንነቱ በተጠበቀ መንገድ ወደ ተባበሩት አረብ ኤምሬትስ እንደሚጓዙ ተገልጿል። ይህ ዓይነቱ የተቀናጀ አሠራር ዜጎች መብታቸው ተከብሮ በውጭ አገር እንዲሠሩ ለማስቻል የተቀረጸው ሰፊ ብሔራዊ ዕቅድ አካል ነው። ©️ Dire tv አማርኛ

photo content
+3

photo content

photo content

ለኮሌጅና ዩኒቨርስቲ ምሩቃን በሙሉ **** በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የተዘጋጀ "ሥራና ሠራተኛ ማገናኛ ኤግዚቢሽን(Job Fair)" የፊታችን ረቡዕ ግንቦት 5/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:0
ለኮሌጅና ዩኒቨርስቲ ምሩቃን በሙሉ **** በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የተዘጋጀ "ሥራና ሠራተኛ ማገናኛ ኤግዚቢሽን(Job Fair)" የፊታችን ረቡዕ ግንቦት 5/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 ጀምሮ ኮንጎ ሜዳ በሚገኘው የድሬዳዋ ወጣቶችና ስፖርት አካዳሚ ሁለገብ ሜዳ የሚካሄድ ይሆናል። በዚህም ስራ ፈላጊ ምሩቃን የተለያዩ ድርጅቶች በቅጥር ሥራ የምታገኙበትን ሁኔታ ሊያመቻቹ እናንተን ስለሚጠብቁ የትምህርት ማስረጃዎቻችሁን በመያዝና በአካል በመገኘት  የዕድሉ ተጠቃሚ ትሆኑ ዘንድ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።                   የድሬዳዋ አስተዳደር                    ሥራና ክህሎት ቢሮ