uz
Feedback
ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።

ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።

Kanalga Telegram’da o‘tish

📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623

Ko'proq ko'rsatish
3 285
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
-247 kunlar
-4930 kunlar
Postlar arxiv
#ተወዳጆች...! መጽሐፈ ስንክሳር ለልጆች በእኔነት አተራረክ አጠር መጠን ብሎ የተዘጋጀ፥እንዲኹም በተመጣጣኝ ዋጋ የቀረበ ሰናይ መጽሐፍ ነው ፤አዘጋጁን ዘኤልያስ እያመሰገንን ፥ተሻምተን ልጆቻችንን እ
#ተወዳጆች...!  መጽሐፈ ስንክሳር ለልጆች በእኔነት አተራረክ አጠር መጠን ብሎ የተዘጋጀ፥እንዲኹም በተመጣጣኝ ዋጋ የቀረበ ሰናይ መጽሐፍ ነው ፤አዘጋጁን  ዘኤልያስ እያመሰገንን ፥ተሻምተን ልጆቻችንን እንመግብ እንላለን ..! #ቻናሉን ሼር ማድረግ አይርሱ...! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📖#የበገና መማሪያ ተሻሻሽሎ የቀረበ📖 ከዚህ መጽሐፍ ላይ ያለው የማስተማር ዘዴ መምህሬ መምህር ሲሳይ እኔን ያስተማረበትና እኔ የማውቀው ብቻ ከ750 በላይ በገና ደርዳሪዎች ያፈሩበት /የተገኙበት/
📖#የበገና መማሪያ ተሻሻሽሎ የቀረበ📖 ከዚህ መጽሐፍ ላይ ያለው የማስተማር ዘዴ መምህሬ መምህር ሲሳይ እኔን ያስተማረበትና እኔ የማውቀው ብቻ ከ750 በላይ በገና ደርዳሪዎች ያፈሩበት /የተገኙበት/ ነው፡፡ በተጨማሪም መጽሐፉ ተማሪዎች ለብዙ ዓመታት ሲገጥማቸው የነበረውን የበገና አደራደር መለማመጃና መማሪያ መጽሐፍ ችግር የሚፈታ ሲሆን ይህን መጽሐፍ በትክክል አንብቦና ተረድቶ ለሚለማመድ ሁሉ በአጭር ጊዜ ውስጥ በገና መደርደር ይችላል የሚል እምነት አለኝ። ቀለል ባለ ዘዴ በገናን የመማሪያ መጽሐፍ ችግር ባለበት በአሁኑ ወቅት ይህ መጽሐፍ አንዲዘጋጅ የረዳን እግዚአብሔር አምላካችን የተመሰገነ ይሁን፡፡ አቤል ተክዑ ኢንጂነር የበገና መምህር 📚ግዮን መጻሕፍት @GhionBookStore1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/GhionBookStore1623

‹‹ወርሃ ፅጌ›› ፅጌ ማለት አበባ ማለት ሲሆን በዚህ ወር የፅጌሬዳ አበባ የሚፈካበት ወር ነው። ይቺ 40 ቀን "ወርሃ ፅጌ" በመባልም ይጠራል። ፅጌሬዳ በመአዛው እጅግ ያስደስታል ለአይንም ይማርካል
‹‹ወርሃ ፅጌ›› ፅጌ ማለት አበባ ማለት ሲሆን በዚህ ወር የፅጌሬዳ አበባ የሚፈካበት ወር ነው። ይቺ 40 ቀን "ወርሃ ፅጌ" በመባልም ይጠራል። ፅጌሬዳ በመአዛው እጅግ ያስደስታል ለአይንም ይማርካል እመቤታችንም በአበባው እንመስላታለን ጉድፍ የሌለባት ለነፍስም ለስጋም ደስ ምትል ውበት የስጋ ድንግልና የነፍስም ድንግል ናትና በእሷ መልክ ይሰየማል። በነገረ ማርያምም እደተፃፈው እመቤታችን መውለጃዋ ቀን ሲደር በአረጋዊው ዮሴፍ ማረፊያ ቦታ ፈልጎ ከብዙ ድካም በኋላ በከብቶች በረት በሚያርፉበት ግርግም ተወለደ በጨርቅ ጠቅልላም አስተኛችው። ጌታችን ኢየሱስም ሁለት አመት ሲሞላው ኄሮድስ ህፃኑን ክርስቶስን ሊገድለው ስለፈለገ መልአኩ "ተነስተህ እናቱን ና ብላቴናውን ይዘህ ወደ ግብፅ ሽሽ "ብሎ ለዮሴፍ ነገረው። እመቤታችንም ልጇን ይዛ ከዮሴፍ ጋር ወደ ግብፅ ከመስከረም-26-ህዳር-6 ተሰደደች። ፆመ ፅጌ የአዋጅ ፆም አይደለም የእመቤታችን ፍቅር ያለው ሰው በውዴታ ስደቷን ስቃዮዋን ለማስታወስ የፈለገ ብቻ በውዴታ የሚፆመው ፆም ነው። ፆመ ፅጌ የድንግልን ስደት ለምለም አካላቷ ያልጠና ሰውነቷ ጥፍሯ እስኪነቀል ድረስ በሀሩሩ በውርጭኝ ያለ ሀጢያቷ እንግልት በማየቷ በረከትን ለማግኘት እንፆማለን ማለት ነው። የተባረከ ፆም እንዲሆን ፍቃዷ ይሁንልን🙏

‹‹ወርሃ ፅጌ›› ፅጌ ማለት አበባ ማለት ሲሆን በዚህ ወር የፅጌሬዳ አበባ የሚፈካበት ወር ነው። ይቺ 40 ቀን "ወርሃ ፅጌ" በመባልም ይጠራል። ፅጌሬዳ በመአዛው እጅግ ያስደስታል ለአይንም ይማርካል
‹‹ወርሃ ፅጌ›› ፅጌ ማለት አበባ ማለት ሲሆን በዚህ ወር የፅጌሬዳ አበባ የሚፈካበት ወር ነው። ይቺ 40 ቀን "ወርሃ ፅጌ" በመባልም ይጠራል። ፅጌሬዳ በመአዛው እጅግ ያስደስታል ለአይንም ይማርካል እመቤታችንም በአበባው እንመስላታለን ጉድፍ የሌለባት ለነፍስም ለስጋም ደስ ምትል ውበት የስጋ ድንግልና የነፍስም ድንግል ናትና በእሷ መልክ ይሰየማል። በነገረ ማርያምም እደተፃፈው እመቤታችን መውለጃዋ ቀን ሲደር በአረጋዊው ዮሴፍ ማረፊያ ቦታ ፈልጎ ከብዙ ድካም በኋላ በከብቶች በረት በሚያርፉበት ግርግም ተወለደ በጨርቅ ጠቅልላም አስተኛችው። ጌታችን ኢየሱስም ሁለት አመት ሲሞላው ኄሮድስ ህፃኑን ክርስቶስን ሊገድለው ስለፈለገ መልአኩ "ተነስተህ እናቱን ና ብላቴናውን ይዘህ ወደ ግብፅ ሽሽ "ብሎ ለዮሴፍ ነገረው። እመቤታችንም ልጇን ይዛ ከዮሴፍ ጋር ወደ ግብፅ ከመስከረም-26-ህዳር-6 ተሰደደች። ፆመ ፅጌ የአዋጅ ፆም አይደለም የእመቤታችን ፍቅር ያለው ሰው በውዴታ ስደቷን ስቃዮዋን ለማስታወስ የፈለገ ብቻ በውዴታ የሚፆመው ፆም ነው። ፆመ ፅጌ የድንግልን ስደት ለምለም አካላቷ ያልጠና ሰውነቷ ጥፍሯ እስኪነቀል ድረስ በሀሩሩ በውርጭኝ ያለ ሀጢያቷ እንግልት በማየቷ በረከትን ለማግኘት እንፆማለን ማለት ነው። የተባረከ ፆም እንዲሆን ፍቃዷ ይሁንልን🙏

📚#መዝሙረ፡ዳዊት፡ንባቡና፡ትርጓሜው #መዝሙረ፡ዳዊት፡ መነኮሳት፡ካህናት፡መዘምራንም፡በዜማ፡ በንባብ ፡ በቤተ ፡ ክርስቲያን ፡ በመዓልትም ፡ በሌሊትም ፡ ሳያቋርጡ ፡ እን ዲጸልዩበት፤ ምእመናንም ፡ ከ
📚#መዝሙረ፡ዳዊት፡ንባቡና፡ትርጓሜው #መዝሙረ፡ዳዊት፡ መነኮሳት፡ካህናት፡መዘምራንም፡በዜማ፡ በንባብ ፡ በቤተ ፡ ክርስቲያን ፡ በመዓልትም ፡ በሌሊትም ፡ ሳያቋርጡ ፡ እን ዲጸልዩበት፤ ምእመናንም ፡ ከሌላው ፡ ጸሎት፡ይልቅ፡እሱን፡መላልሰው፡ እንዲጸልዩ ፡ የታዘዙ ፤ ኤፌ ፡ ፭ ፡ ፲፱ ። መዝሙር ፡ ፴፫ ፡ ፩ ። በሰማይና በምድር ፡ ያሉ ፡ ሁሉ ፡ በዳዊት ፡ ቃል ፡ ይዘምራሉ ፡ ተብሎ ፡ የተነገረለት፡ በመሆኑ ፡ ከሁሉ ፡ ይበልጥ ፡ ተፈላጊ ፡ መሆኑ ፡ ሲታወቅ ፡ የትርጓሜውም ፡ ዋና ፡ ጥቅሙ፡ ምስጢሩን ፡ ሳያውቁ ፡ የሚጸልዩበት ምእመናን ፡ ምስጢሩን ፡ ዐውቀው ፡ እንዲጸልዩ ፡ ማድረግ ፡ ነው ።-ስለዚህ ፡ ይኸ ፡ መዝሙረ ፡ ዳዊት ፡ ከጥንት ፡ አባቶች ፡ እንደ ፡ ተረ ጐሙትና ፡ ሲወርድ ፡ ሲዋረድ ፡ እንደ ፡ መጣው ፡ ንባቡና ፡ ትርጓሜው ፡ ተጽፎና ፡ ታርሞ ፡ በግርማዊ ፡ ጃንሆይ ፡ ቀዳማዊ ፡ ኃይለ ፡ ሥላሴ ፡ ትእ ዛዝ ፡ በብፁዕ ፡ አቡነ ፡ ባስልዮስ ፡ ፈቃድ ፡ ባ፲፱፻፶ (1950)፡ ዓ ∙ ም ፡ ታተመ ▪ [''አባ ፡ ቴዎፍሎስ ፡ የሐረር ፡ ጳጳስና ፡ የኢትዮጵያ ፡ ሊቀ ፡ ጳጳሳት ፡ ዋና ፡ እንደራሴ "] 📚ግዮን መጻሕፍት  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📖#ዜና_አበው 📖 [ዘውእቱ መጽሐፈ ገነት ካልዕ] #የአባቶች ንግግር የመንፈሳዊ ሕይወት ትርጉም ነው፡፡ በቅድስና አኗኗር ውስጥ የሚነገሩ ቃላቶች የመንፈስ ቅዱስ ቅዱስ ፍሬዎች ናቸው፡፡ የእግዚአብሔ
📖#ዜና_አበው 📖 [ዘውእቱ መጽሐፈ ገነት ካልዕ] #የአባቶች ንግግር የመንፈሳዊ ሕይወት ትርጉም ነው፡፡ በቅድስና አኗኗር ውስጥ የሚነገሩ ቃላቶች የመንፈስ ቅዱስ ቅዱስ ፍሬዎች ናቸው፡፡ የእግዚአብሔር የባሕርይ መገለጫዎቹን ማደሪያዎቹ በሆኑ በቅዱሳን ኑሮ ላይ እናገኛቸዋለን፡፡ ያ የመንፈስ ፍሬም ነገረ እግዚአብሔር ይባላል፡፡ ቢሰሙት የማይሰለቹት ቢያወሩት የማይጠግቡት ሁልጊዜ መንፈስን የሚያድስ ህሊናን የሚያለመልም ንግግር ነው። በመምህር አብርሃም ፈቃዴ ተተርጉሞ የቀረበልን ዜና አበዊነ ቅዱሳን የሚለው መጽሐፍም ይሄው የአባቶች ጥልቅ ድንቅ የሕይወት ጣዕመ ንግግር ነው᎓᎓ በዘመናቸው ደርሰን በአካለ ሥጋ የማናያቸው አባቶቻችን ዕለት ዕለት እንዲመክሩን የሕይወት ጣዕማቸው ይሄው ደርሶናል፡፡ ወንጌል በሕይወት ስትገለጥ ምን እንደምትመስል ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ መጽሐፍ ነው፡፡በጣዕመ መንፈስ ቅዱስ ከታሹ አባቶች ጋራ ማውራት ምን ያህል ጥቅም እንዳለው ለመረዳት እስከ መጨረሻው ማንበብ ነው። #የኔታ_ገብረ_መድኅን_እንየው 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

♦ነፍሳችሁ በደጋጎች በፃድቃን ጎን እንዲያርፍ የእግዚአብሔር ፍቃድ ይሁን 🙏 🖤 #ነፍስ_ይማር 🖤🖤 በአማራ ክልል በሰሜን ሸዋ ዞን በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ በአረርቲ ከተማ አስተዳደር አረርቲ ማር
+2
♦ነፍሳችሁ በደጋጎች በፃድቃን ጎን እንዲያርፍ የእግዚአብሔር ፍቃድ ይሁን 🙏 🖤 #ነፍስ_ይማር 🖤🖤 በአማራ ክልል በሰሜን ሸዋ ዞን በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ በአረርቲ ከተማ አስተዳደር አረርቲ ማርያም ቤተክርስቲያን አመታዊ ክብረበዓልን አስመልክቶ ከጠዋቱ 1:45 ላይ እየተሰራ ያለው ቤተክርስቲያን እየተጎበኘ ባለበት ‎ሰዓት ለፊኒሺንግ የተረበረበ እንጨት ተደርምሶ በርካታ ምእመናን ላይ የሞትና የአካል ጉዳት ደርሷል ። የቅዱሳኑ አምላክ ነፍሳቸዉን በቅዱሳን #ዘንድ_በሰላም_ያሳርፋቸዉ 🤲

#እናታችን_እመቤታችን ብዙኃን ''ማርያም'' ----- በቤተ ክርስቲያናችን ከሚዘከሩ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ክብረ በዓላት መካከል መስከረም ፳፩ ቀን የሚውለው በዓል ‹‹ብዙኃን ማርያም››
#እናታችን_እመቤታችን ብዙኃን ''ማርያም'' ----- በቤተ ክርስቲያናችን ከሚዘከሩ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ክብረ በዓላት መካከል መስከረም ፳፩ ቀን የሚውለው በዓል ‹‹ብዙኃን ማርያም›› በመባል ይታወቃል፡፡ በዓሉ በሁለት ዐበይት ምክንያቶች ይከበራል፤ የመጀመሪያው ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ሃይማኖታዊ ውሳኔ ለማዘጋጀት ከሩቅም ከቅርብም የተሰባበሰቡት ቀን፤ ሁለተኛው ደግሞ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት ዕፀ መስቀል በግሸን ደብረ ከርቤ የተቀመጠበት ዕለት መኾኑ ነው፡፡ ❝#ርግቤ ሆይ ነዪ ሐዋርያት የሚያመሰግኑሽ መላእክትም የሚላላኩልሽ #መልካሜ ሆይ ነዪ። #የሕይወት_ውበት ከሊባኖስ ወጥተሽ ነዪ።❞    "#ለኲሉ_ፍጥረት_ትተነብል"          "#ለፍጥረት_ሁሉ_ትለምናለች" ''እንኳን አደረሰን!'' 📚ግዮን መጻሕፍት  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

✨#ዜና_መጽሐፍ 📖#አንጋረ_ሊቃውንት📖 #ትናንት የሌለው ዛሬ፣ መነሻ የሌለው መድረሻ የለውም፡፡ የእኛ ዛሬነት የትናንት መነሻነት ሲኾን፤ የዛሬው ማንነታችን ደግሞ ለነገዎቹ መነሻ ነው፡፡ “በቃል ያ
#ዜና_መጽሐፍ 📖#አንጋረ_ሊቃውንት📖 #ትናንት የሌለው ዛሬ፣ መነሻ የሌለው መድረሻ የለውም፡፡ የእኛ ዛሬነት የትናንት መነሻነት ሲኾን፤ የዛሬው ማንነታችን ደግሞ ለነገዎቹ መነሻ ነው፡፡ “በቃል ያለ ይረሳል፣ በመጽሐፍ ያለ ይወረሳል” እንዲሉ፤ የዛሬ እኛዎች የትናንት ዛሬዎች፣ የነገ ትናንቶች እንደ መኾናችን መጠን፤ ከቀድሞ ጀምሮ ቃል በቃል ሲነገር የመጣውን የአባቶቻችን ብሂል ለዛሬ ተጠቅመንበት ቀጣይ ትውልድም እንዲጠቀምበት ለማስቻል መ/ር ሐዲስ ደከመኝና ስለቸኝ ሳይሉ ከአበው ቃል በቃል የመጣውንና ከመጻሕፍት ያገኙትን አሰባስበው ያቀረቡልን በመኾናቸው የአባቶች በረከት አይለይዎት በማለት ልባዊ ምኞቴን እገልጻለሁ። በዚሁ አጋጣሚ ቀደምት አባቶቻችን እንኳን ፍቅራቸውን፤ ሊያስተላልፉ የፈለጉትን መልዕክት ለጆሮ በማይጎረብጥ፣ ልብን በሚመስጥ ኹኔታ ይገልጹ እንደ ነበር መረዳት ችያለሁ፡፡ #መምህር_ዳግማዊ_ሙሴ [የመጽሐፈ ምንኃር አዘጋጅ] #አንብበው_ሲጨርሱ_ሼር_ማድረግ_አይርሱ! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

✨✨✨✨✨✨ † ቅዱስ መስቀል † ❝መስቀል ሰይጣንን የሚያጠፋ ምሳር ነው ፤ የአጋንንትንም ራሶች የሚቆርጥ ሰይፍ ነው ፤ መስቀል ርኩሳን መናፍስትን የሚወጋቸው የእሳት ዘገር ነው ፤ የአመስቴማውያንንም
✨✨✨✨✨✨ † ቅዱስ መስቀል †     ❝መስቀል ሰይጣንን የሚያጠፋ ምሳር ነው ፤ የአጋንንትንም ራሶች የሚቆርጥ ሰይፍ ነው ፤ መስቀል ርኩሳን መናፍስትን የሚወጋቸው የእሳት ዘገር ነው ፤ የአመስቴማውያንንም ሠራዊት የሚመታ የመብረቅ ጦር ነው፡፡ መስቀል ማኅተመ ሥላሴ የሌለው ሰው ወደ እርሱ ሊቀርበው የማይቻለው አምባ መጠጊያ ነው። መስቀል ከግራም ከቀኝም ለሚመጣ ጠላት የጽድቅ ጋሻ ነው፡፡ መስቀል የጦር ውጋት ሊቀድደው ፣ የቀስትና የዘንግም ጫፍ ሊበሳው የማይችል የሃይማኖት ጥሩር ነው፡፡ መስቀል አማሌቃውያንን ለመዋጋት በራፊድ በረሐ በተዘረጋው በሙሴ እጅ አምሳል የተሠራ ነው፡፡ መስቀል በሙሴ እጅ ወደ ውስጥ በተጨመረ ጊዜ መራራውን ውኃ በሱር በረሐ ያጣፈጠ ነው፡፡ መስቀል የቅድስናና የንጽሕና ማኅተም ነው፡፡ ❞ [  ውዳሴ መስቀል  ] ✨እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ አደረሰን ! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

                          †                                                                        🕊                       🕊          †    መስቀል    †          🕊 🌼    --------------- † ---------------    🌼 ❝  መስቀል ሰይጣንን የሚያጠፋ ምሳር ነው ፤ የአጋንንትንም ራሶች የሚቆርጥ ሰይፍ ነው ፤ መስቀል ርኩሳን መናፍስትን የሚወጋቸው የእሳት ዘገር ነው ፤ የአመስቴማውያንንም ሠራዊት የሚመታ የመብረቅ ጦር ነው፡፡ መስቀል ማኅተመ ሥላሴ የሌለው ሰው ወደ እርሱ ሊቀርበው የማይቻለው አምባ መጠጊያ ነው። መስቀል ከግራም ከቀኝም ለሚመጣ ጠላት የጽድቅ ጋሻ ነው፡፡ መስቀል የጦር ውጋት ሊቀድደው ፣ የቀስትና የዘንግም ጫፍ ሊበሳው የማይችል የሃይማኖት ጥሩር ነው፡፡ መስቀል አማሌቃውያንን ለመዋጋት በራፊድ በረሐ በተዘረጋው በሙሴ እጅ አምሳል የተሠራ ነው፡፡ መስቀል በሙሴ እጅ ወደ ውስጥ በተጨመረ ጊዜ መራራውን ውኃ በሱር በረሐ ያጣፈጠ ነው፡፡ መስቀል የቅድስናና የንጽሕና ማኅተም ነው፡፡ ❞ [  ውዳሴ መስቀል  ] ✨እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ አደረሰን !

#የመጽሐፍ_ቅዱስ_ታሪኮች_ለልጆች #የልጆች የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች በመጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር የታተመ ውስጡ ከለርድ ልጆችን በሚማርክ መልኩ የተዘጋጀ ነው። ልጆቻችንን የነገ የቤተክርስቲያን ተረካቢ እንደ
#የመጽሐፍ_ቅዱስ_ታሪኮች_ለልጆች #የልጆች የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች በመጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር የታተመ ውስጡ ከለርድ ልጆችን በሚማርክ መልኩ የተዘጋጀ ነው። ልጆቻችንን የነገ የቤተክርስቲያን ተረካቢ እንደመኾናቸው በሃይማኖትና በወንጌል ኮትኩተን በማሳደግ ኃላፊነታችን እንወጣ ዘንድ እንዲያስፈልግ ልብ ይሏል ! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

#ገድለ_አቡነ_ሐራ_ድንግል #ማኅቶተ ቤተክርስቲያን ጳውሎስ ከመዠመሪያ አንሥቶ የነበሩ የቅዱሳንን ስም እየጠራ ገድላቸውን እየጠቀሰ በቃልም በመልእክትም ያስተምር ነበር፡፡ ዕብ. ፲፩፥፴፪ “እንግዲህ ም
#ገድለ_አቡነ_ሐራ_ድንግል #ማኅቶተ ቤተክርስቲያን ጳውሎስ ከመዠመሪያ አንሥቶ የነበሩ የቅዱሳንን ስም እየጠራ ገድላቸውን እየጠቀሰ በቃልም በመልእክትም ያስተምር ነበር፡፡ ዕብ. ፲፩፥፴፪ “እንግዲህ ምን እላለሁ፤ የጌዴዎንን፣ የባርቅን፣ የዮፍታሔን፣ የሶምሶንን፣ የዳዊትን፣ የሳሙኤልን የሌሎችንም ነቢያት ነገር ልነግራችሁ ቀን ያጥርብኛልና፡፡ በሃይማኖት የተጋደሉትን ነገሥታትን ድል የነሡትን ዋጋቸውን ያገኙትን ትሩፋት የሠሩትን ተስፋቸውን ያገኙትን የአንበሶችን አፍ የዘጉትን ዋዕየ እሳትን ያጠፉትን፣ ከጦር ስለት የዳኑትን፣ በመከራቸው የፀኑትን በሰልፍ ጊዜ የበረቱትን፣ የጠላቶቻቸውን ጭፍራ ያሳደዱትን ነገር እንዳልነግራችሁ ቀን ያጥረኛል፡፡” “ከመከራ እንዲድኑ አልወደዱምና፤ የገረፏቸው የዘበቱባቸው፣ አስረው ያጋዟቸውም አሉ፤ በመጋዝ የሰነጠቋቸው፣ በድንጊያ የደበደቧቸው፣ በሰይፍ ስለት የገደሏቸው አሉ፤ ማቅ የተልባ እግር የፍየል ሌጦ ለብሰው ዞሩ፤ ተጨነቁ፣ ተቸገሩ፣ መከራ ተቀበሉ፣ ተራቡ፣ ተጠሙ፡፡” ዕብ. ፲፩፥፴፪ ብርሃነ ዓለም ጳውሎስ እንዲህ እያለ በጠቅላላው እግዚአብሔርን ስለማመናቸው ምክንያት ቅዱሳን ላይ የደረሰባቸውን መከራና የቻሉትን መቻል ካስዘከረ በኋላ ገድላቸውን እያሰብን እንድንማርበትና እኛም አሰረ ፍኖታቸውን እንድንከተል ቀጥሎ “ስለዚህም እንደደመና የሚከቡን እነዚህ ሁሉ ምስክሮች ያሉን እኛ የኃጢአትን ትብትብና ሸክም አውርደን እንጣል፤ ሃይማኖት ወደሚያስገኝልን ወደሚጠብቅልን ተስፋችን በትዕግሥት እንገሥግሥ” ይለናል፡፡ ፲፪፥፩ #ገድላቸውን አንብበን ከበረከታቸው የምንሳተፍ ያድርገን! 👉#ማሳሰቢያ የቀረን የተወሰነ ፍሬ ነውና እንዳያመልጥዎ

📖#አንድሮሜዳ📖 #የዶክተር_ሮዳስ አንድሮሜዳ የተሰኘው መጽሐፍ የጥንት ኢትዮጵያውያን የሕዋ ሥልጣኔ ከዘመናዊው ሳይንስ አንጻር በደንብ ፍንትው አድርጎ የሚያብራራ እንዲሁም ከሕጻናት እስከ አዋቂ እን
📖#አንድሮሜዳ📖 #የዶክተር_ሮዳስ አንድሮሜዳ የተሰኘው መጽሐፍ የጥንት ኢትዮጵያውያን የሕዋ ሥልጣኔ ከዘመናዊው ሳይንስ አንጻር በደንብ ፍንትው አድርጎ የሚያብራራ እንዲሁም ከሕጻናት እስከ አዋቂ እንዲረዳው ተቀምሞ የተዘጋጀ ለልጆች ደግሞ ንቃተ ሕሊናን የሚያስጎነጭ ጥዑም ጦማር ነው ። ለዚህ ሳምንት ለልዩ ቅናሽ የመረጥነው መጽሐፍ ነው ። ቻናሉን #ሼር በማድረግ ወዳጆቻችሁን ተጠቃሚ ከድርጉ!

📖#ሐተታ_ዘቅዱስ_አትናቴዎስ #ያለሀሰት ቅዱስ አትናቴዎስ ለቤተክርስትያን አምድ ከምንላቸው ቅዱሳን አባቶቻችን አንዱና ዋነኛው መኾኑ አያጠያይቅም ታድድያ ከእርሱ ግሩማን አበርክቶዎች መካከል "ተስእሎ
📖#ሐተታ_ዘቅዱስ_አትናቴዎስ #ያለሀሰት ቅዱስ አትናቴዎስ ለቤተክርስትያን አምድ ከምንላቸው ቅዱሳን አባቶቻችን አንዱና ዋነኛው መኾኑ አያጠያይቅም ታድድያ ከእርሱ ግሩማን አበርክቶዎች መካከል "ተስእሎተ አንትያኮስ" የተሰኘውን መጽሐፍ #መምህር_ቃለ ጽድቅ_ሕግነህ በተዋበ እና ለንባብ ምቹ አድርገው የተረጎሙት ሲኾን ➱ቅዱስ አትናቴዎስ በዚህ መጽሐፍ ከሚመልሳቸው ጥያቄዎች .....አንትያኮስ፡ ርኩሳን መናፍስት የሆኑ አጋንንት ከቅዱሳት መጻሕፍት የሚፈሩት የጸሎት ዐይነት የቱ ነው? ➮ጥያቄ ፦ በውኑ ለኃጥአን ነፍሳት በዚህ ዓለም ዘመዶቻቸው የመታሰቢያ(ተዝካር) ቍርባን፣ ጸሎትና ምጽዋት ቢያደርጉላቸው በዚያኛው ዓለም ይጠቅማቸዋልን? ➮ጥያቄ ፦ ለሰው እጅ ሥራዎች እንዳንሰግድ እግዚአብሔር በነቢያቱ አዝዞናልና ለምን የሰው እጅ ለሠራው ለቅዱሳን ሥዕልና ለቅዱስ መስቀሉ እንሰግዳለን? ➮አንትያኮስ፡- ከኃጢአት ሁሉ የሚበልጠው ኃጢአት የቱ ነው? ➮አንትያኮስ፡- ብዙ በደልንና ኃጢአትን የሠራ ሰው ቢኖር ከዚያም በኋላ ንስሓ ቢገባ፤ እንደገና ተመልሶ ኃጢአት ቢሠራ እግዚአብሔር ንስሓውን ይቀበለዋልን ወይስ አይቀበለውም? #ይህንና መሰል ጥያቄዎችን ከነ መልሶቻቸው የያዘ ልዩ መጽሐፍ በመኾኑ እንድታነቡት ግብዣችን ነው! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL ,በEMS እንዲሁም የ delivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። 📱ይደውሉልን ፦0913083816 Telegram https://t.me/GhionBookStore1623