uz
Feedback
ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።

ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።

Kanalga Telegram’da o‘tish

📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623

Ko'proq ko'rsatish
3 285
Obunachilar
-324 soatlar
-197 kunlar
-4130 kunlar
Postlar arxiv
አዎ:- የእመቤታችን የማርያም ዐሳብ እንደ አምላክ ዐሳብ ነው! ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ "እኛ የክርስቶስ ልብ አለን" ብሏል። ፩ቆሮ ፪: ፲፮። ልብ ማለት አዕምሮ ነው። ዐሳብ የሚቀዳው ከልብ ነው። "
አዎ:- የእመቤታችን የማርያም ዐሳብ እንደ አምላክ ዐሳብ ነው! ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ "እኛ የክርስቶስ ልብ አለን" ብሏል። ፩ቆሮ ፪: ፲፮። ልብ ማለት አዕምሮ ነው። ዐሳብ የሚቀዳው ከልብ ነው። "አምላክህንም እግዚአብሔርን በፍጹም ልብህ፥ በፍጹምም ነፍስህ፥ በፍጹምም ኀይልህ ውደድ።" ሲል አዕምሮን ወይም ዐሳብን ያመለክታል። ዘዳ ፮ : ፭። ዐሳብ፣ ልብ እና አዕምሮ የሚሉትን የሚተካኩ ቃላት በተለዋዋጭነት ልንጠቀምባቸው እንችላለን። ቅዱስ ጳውሎስ እኔ ብቻ የክርስቶስ ልብ አለኝ አለማለቱንም ልብ እንበል። እኛ ነው ያለው። እኛ ሲል እርሱን የሚመስሉትን፣ የሚያኽሉትን፣ የሚበልጡትንም ኹሉ ያጠቃልላል። ከሚበልጡት አንዷ ድንግል ማርያም ናት። ቅዱስ ዳዊትን እግዚአብሔር እንደ ልቤ ብሎታል። "እንደ ልቤ የኾነ ሰው ፈቃዴንም ኹሉ የሚያደርግ የእሴይን ልጅ ዳዊትን አገኘሁ" እንዲል። ሥራ ፲፫: ፳፪። እግዚአብሔር የእጁን ፍጡር እንደ ልቤ ብሎታል። እርሱ ያልቸገረውን አንተን ለምን ይቸግርሃል? ቅዱስ ጳውሎስ እኛ ካላቸው መኻል ከኹሉ በላይ ቀዳሚ የምትኾነው የእመቤታችን ዐሳብ እንደ አምላክ ዐሳብ ነው ማለት እጅግ በጣም ትክክል መኾኑን ተመልከት። በተለያየ ጥፋት ሲወድቁ ሲነሡ የኖሩት ቅዱስ ዳዊት እና ቅዱስ ጳውሎስ በዚህ ደረጃ ሲገለጡ በዘመኗ ኹሉ ያለ ስሕተት ያለ ኃጢአት በፈቃደ እግዚአብሔር ብቻ የኖረች እመቤት እንዲህ ስትገለጥ ለምን አመመህ? ነው ወይስ ከአምላክ ሕሊና እኩል ያደረግናት ይመስልሃል? እንደ እርሱ ማለት እንዳልኾነ ቅዱስ ዳዊት እና ቅዱስ ጳውሎስ የተገለጡበትን መላልሰህ አንብብ።

#ዶክተር_እጓለ ፦በተውሶ መነጽር እራስንና ማንነትን የማኮሰስ ደዌ #ያላገኛቸው ኢትዮጵያዊ ሊቅ ናቸው ። -#የኢትዮጵያን ሥነ-ጽሑፍ ያጠኑ፤ የመረመሩ ለነበሩ ጥንታዊ ሀገር በቀል ባህልና እውቀት አክብ
#ዶክተር_እጓለ ፦በተውሶ መነጽር እራስንና ማንነትን የማኮሰስ ደዌ #ያላገኛቸው ኢትዮጵያዊ ሊቅ ናቸው ። -#የኢትዮጵያን ሥነ-ጽሑፍ ያጠኑ፤ የመረመሩ ለነበሩ ጥንታዊ ሀገር በቀል ባህልና እውቀት አክብሮት ያላቸው ሊቅ በመኾናቸው የሀገራቸውን ጽሑፎች ሲያጠኑና ሲመረምሩ መንፈሳቸውና አእምሯቸው ከፍ ወዳለ መራቀቅ ደረጃ ከደረሱት ጥቂት ማሰብ ከሚችሉ ሊቃውንት መካከል እጓለ አንደኛው ናቸው። [ፍካሬ እጓለ በተመስገን ዋና የቀረበ] ....ከመጽሐፉ ለቅምሻ #ሰውን ጥቅም፤ ተድላ፣ ደስታ ብቻ ተፈላላጊ አድርጐ በመመልከት ፤ ይህንኑ ምኞቱን የሚያረካበት ትምህርት ብናቀርብለት የሚጐዳ፣ የሚበደል እንጂ የሚጠቀም አይደለም፡፡ ምክንያቱም ሰዎች በመላ ለዚህ ነገር ብቻ ቢሰለፉ በማኅበራዊ ኑሮ ውስጥ ያለው ውድድር መልኩን ለውጦ ያለመጠን አስቸጋሪና የሚያፋጅ ሊሆን ይችላል። በተለይም ይኸ እንዲህ ያለ ጥቅምን ብቻ የሚመለከት ትምህርት የሚያስገኘው ጠባይ ከሥልጣን ጋር የተገናኘ እንደሆን ነገር ጨርሶ ሊበላሽ ይችላል ለኔ ማለት ይሰፍናል። ---- ❝የሰው ልጅና ማድጋ ጆሮውን ካልያዙት አሟልጮ ይወድቃል!❞[እዝነ-ልቡናን ያጠይቃል] #በርግጥ ይህ መጽሐፍ በዓይነቱ እስካሁን በአማርኛ ከተጻፉ መጻሕፍት ሁሉ ብቸኛና ዘላቂ ይዞታ ያላቸው ድርሰተቶች ከምንላቸው ተቀዳሚው ነው! እንግዲያ ብቅ በሉና ደጋግማችኹ ሸምቱት ቅርስ ነውና! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

#የግዮን_ወንዝ #በዲያቆን_ሄኖክ_ኃይሌ የተጦመረው ይህ ጥዑም መጽሐፍ በድጋሚ ታትሟል! እንደሚታወቀው ደግሞ ሙሉ ገቢው ለታላቁ የምድራችን ቅድስተ ቅዱሳን ክፍሎች ውስጥ አንዱ ለኾነው ለደብረሊባኖስ ገ
#የግዮን_ወንዝ #በዲያቆን_ሄኖክ_ኃይሌ የተጦመረው ይህ ጥዑም መጽሐፍ በድጋሚ ታትሟል! እንደሚታወቀው ደግሞ ሙሉ ገቢው ለታላቁ የምድራችን ቅድስተ ቅዱሳን ክፍሎች ውስጥ አንዱ ለኾነው ለደብረሊባኖስ ገዳም ሕንጻ ማሰሪያ እንዲውል የተደረገ ነው ።እኛም ከንባቡ ተጠቅመን ጸኃፊውን እየመረቅን ገዳማችንን እንርዳ ...!

#ዜና_መጽሐፍ በወጉ ያልተዘከሩት ምሁር መጽሐፍ        ( ዶ/ር ሥርግው ሐብለሥላሴ) [ጸጋው ማሞ እንዳሰናዳው] ፨"ሥርግው ምን አልባትም በ20ኛው ክፍለ ዘመን ካሉት ብቸኛው የኢትዮጵያ የጥንታዊ ታሪክ ሊቅ ነው"  ይላሉ ኤርትራዊው የታሪክ ተመራማሪ ፕሮፌሰር "ባህሩ ተፍላ"  ስለ ጥረታቸውና ሀቃዊ የታሪክ ትንተናቸው ፕሮፌሰር መስፍን ወልተማሪያምም  "በመክሸፍ እንደ ኢትዮጵያ ታሪክ " መጽሐፋቸው ላይም ምሥክርነታቸውን በአድናቆት ሰጥተዋል። ተቀዳሚ ምሁር ፕሮፌሰር ሥርግው  ሐብለሥላሴ በሀገር ውስጥ እና ከሀገር ውጭ ተምረው ባካበቱት ሰፊ እውቀት ላይ ተንተርሰው አያሌ የታሪክ ጥናቶችን እንዳካፈሉን ይታወቃል።  ከሁሉም በላይ ግን " የኢትዮጵያ  የብራና ጽሑፎች ማይክሮ ፊልም ድርጅት " ዳይሬክተር ሆነው በሰሩት  ዘመን ተሻጋሪ ሥራ የዓለም ሕዝብ ሁሉ ሲዘክራቸውም ይኖራል ። #የኢትዮጵያ ሕዝብ የእርሳቸውን  የድካም  ሥራዎች ተገንዝቦ ተገቢውን ክብር ሊቸራቸው ይገባል። ➮ከእርሳቸው የበዙ ሥራዎች መካከል አንዱ  እና ግዙፍ የሆነው "አማርኛ የቤተ ክርስቲያን መዝገበ ቃላት " ሲሆን ይኸውም በብርቱ ያላሰለሰ ጥረት እና ድካም የተሰራ፤ ዘመን የማይሽረው ከወረት የተሻገረ እጅግ ድንቅ ሥራ ነው። ይኸ ግዙፍ መዝገበ ቃላት በኢትዮጵያ እና በኢትዮጵያ ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን ውስጥ  ከጥንት ጀምሮ የነበሩ ተጽእኖ ፈጣሪ የሆኑ የታላላቅ  ሊቃውንትን ፣ ቅዱሳንን ፣ ገዳማትን እና አድባራትን ታሪክ በመረጃ የሰነደ ድንቅ ሥራ ነው ።  #ይኸ ታሪካዊ መዝገበ ቃላት ለታሪክ ተመራማሪዎች ፣ ለሥነ ጽሑፍ ሰዎች ፣ ለሥነ መለኮት አጥኝዎች ፣ ለሥነ ሰብእ መርማሪዎች እንደዚሁም ታሪክ ለሚወዱ ሰዎች እጅግ ጠቃሚ የሆነ መጽሐፍ ነው ። ለምሳሌ በገጽ 662 ላይ "ገላኔ"ን እንዲህ ያብራራልናል " /እመት/ በ19ኛው ምእት ዓመት የኖረች የጉድሩ ሴት። ባሉዋ ዋቅጅራ ይባላል። ከእነዚህ አብራክ የተገኘው ወንድ ልጅ  ነገሮ ይባላል...ይኸውም ተክለ ኢየሱስ የተባለው የኢትዮጵያን ታሪክን ጽፎ ያቆየን ነው " በማለት ይገልጽና መረጃውን ከታች ያስቀምጥልናል። ⨳ሌላው  የሚያሳስቱ ተመሳሳይ ስም ያላቸውን የተጽእኖ ፈጣሪ ሰዎችን እና የቦታ ስሞች በወጉ እንድንለይም ይጠቀመናል ።ለምሳሌ በዚህ መጽሐፍ ላይ ከ35 በላይ ዮሐንስ የሚባሉ ታላላቅ ታሪካዊ ሰዎች በግልጽ ተብራርተዋል ።  ጀርመኖች ታላቁን  "Encyclopedia of Aethiopica " ከመስራታቸው በፊት የተሰራ ምናልባትም ለዚህ ስራ ታላቅ ግብአት የሆነ መጽሐፍ ነው።  ◆አሁንም የፕሮፌሰር ሥርግው ሐብለሥላሴን የድካም ውጤት "ኢትዮፋጎስ የመጽሐፍ ማእከል"ከኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ ተመጻሕፍት አገልግሎት " ጋር በመተባበር በእጅ ጽሑፍ የነበረውን 13 ቅጽ አርትኦት በመሥራት በሁለት ግዙፍ መጽሐፍት በማሳተማቸው ከፍተኛ ክብር እና ምሥጋና ይገባቸዋል። ከእኛ የሚጠበቀው በከፍተኛ ልፋት ተጋጅቶ የቀረበልንን ጥሩ  ማዕድ መመገብ ብቻ ነው ። #ዶ/ር እጓለ ገብረዮሐንስ "ከመጻሕፍት   የሚደገሙት ጥሩዎቹ ናቸው " ይላሉ ።  እንደዚሁም 'ማርክ ትዋይን' የተባለ ሊቅ ደግሞ "ጥሩ መጽሐፍትን የማያነብ ሰው  ማንበብ ከማይችል ሰው አይሻልም " ይላል ። ይኸ መጽሐፍ ደግሞ ከጥሩዎቹ አንዱ ስለሆነ #በእያንዳንዱ ቤተ መጻሕፍት እና መደርደሪያ ውስጥ ሊገኝ የሚገባ ግሩም መጽሐፍ ነው ። 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼#ሰንበትን_በግዮን_ከቅዱሳት_መጻሕፍት_ጋር🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 ገብተዋል... 📖📖📖📖📖📚 #ትወደኛለህን ? እና #ፍቅር
+1
📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼#ሰንበትን_በግዮን_ከቅዱሳት_መጻሕፍት_ጋር🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 ገብተዋል... 📖📖📖📖📖📚 #ትወደኛለህን ? እና #ፍቅር ✨እነዚህን ኹለት ተወዳጅ መጻሕፍት #በቀሲስ_ታምራት_ውቤ የተቀመሙ ሲኾኑ አንደኛው እንደውም የቅዱስ ዮሐንስ ትምህርት ነበር በጥሩ ኹኔታ መልሰውታል.....ከታተሙ ሰንበት ያሉ ቢኾንም ቶሎ በማለቃቸው ብዙዎቻችን እጅ ሳይገባ አልቆ ነበር ፤ ኾኖም ለኛ በማሰብ ድጋሚ ስላሳተሙልን #ለቀሲስ ባሉበት እጅ ንሻችንን ይድረሳቸው እያልን፤ ኋላ እንዳያልቁብን ቶሎ ይያዙ ዘንድ እናሳስባለን ...! 💚💛❤️     #ሰናይ_ዕለተ_ሰንበት!🙏 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

#በዚህች ቀንም ልደቱን ባከበረ ጊዜ ወለተ ሔሮድያዳ በዘፈን አጥምዳ አስማለችው:: እርሱም የታላቁን ነቢይ ራስ አስቆርጦ በወጪት አድርጎ ሰጣት:: አበው "እምሔሶ ለሔሮድስ ይብላዕ መሐላሁ - ሔሮድስ
#በዚህች ቀንም ልደቱን ባከበረ ጊዜ ወለተ ሔሮድያዳ በዘፈን አጥምዳ አስማለችው:: እርሱም የታላቁን ነቢይ ራስ አስቆርጦ በወጪት አድርጎ ሰጣት:: አበው "እምሔሶ ለሔሮድስ ይብላዕ መሐላሁ - ሔሮድስ መሐላውን በበላ በተሻለው ነበር" ይላሉ:: #የቅዱስ_ዮሐንስ ራሱ በርራ ስትሔድ አካሉን ግን ደቀ መዛሙርቱ ቀብረውታል:: (ማቴ. 3:1, ማር. 6:14, ሉቃ. 3:1, ዮሐ. 1:6) ርጉም ሔሮድስ አንገቱን ካስቆረጠው በሁዋላ #የመጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ ራሱ የጸጋ ክንፍ ተሰጥቷት ጌታችን ወዳለበት #ደብረ_ዘይት ሔዳ በፊቱ ሰገደች:: #ቅዱሳን_ሐዋርያት በአዩት ነገር ተገርመው ራሱን እጅ ነሷት:: ከዚሕ በሁዋላ ጌታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስ ለቅዱስ ዮሐንስ ራስ የማስተማር ስልጣን ሰጥቶ አሰናበታት:: በመላው ዓለም #ለ15 ዓመታት ስትሰብክ ኑራ ሚያዚያ 15 ቀን ዓረቢያ ውስጥ ዓርፋለች:: "አስማተ-ዮሐንስ መጥምቅ (የመጥምቁ ዮሐንስ ስሞች)" 1.ነቢይ 2.ሐዋርያ 3.ሰማዕት 4.ጻድቅ 5.ካሕን 6.ባሕታዊ/ገዳማዊ 7.መጥምቀ መለኮት 8.ጸያሔ ፍኖት (መንገድ ጠራጊ) 9.ድንግል 10.ተንከተም (የብሉይና የሐዲስ መገናኛ ድልድይ) 11.ቃለ አዋዲ (አዋጅ ነጋሪ) 12.መምሕር ወመገሥጽ 13.ዘየዐቢ እምኩሉ (ከሁሉ የሚበልጥ) #ጌታችን_መድኃኔ_ዓለም #የመጥምቁ_ዮሐንስን ምትረት አስቦ ይቅር ይበለን:: ጸጋውን: በረከቱንና ክብሩንም ያሳድርብን!🙏🙏 ©መጽሐፈ ስንክሳር # እንኳን_አደረሰን! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 t.me/GhionBookStore1623

🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 ☘☘☘☘☘☘☘☘☘☘☘☘ 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼#ተወዳጅ ግዮናውያን እንኳን ለዘመነ ቅዱስ ማርቆስ በሰላም አሸጋገረን! #እንኳን_አደረሳችኹ!🌼
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 ☘☘☘☘☘☘☘☘☘☘☘☘ 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼#ተወዳጅ ግዮናውያን እንኳን ለዘመነ ቅዱስ ማርቆስ በሰላም አሸጋገረን! #እንኳን_አደረሳችኹ!🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼☘️☘️☘️☘️☘️☘️☘️☘️☘️☘️🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 #አምላካችን  ቅዱስ እግዚአብሔር አእምሮን ኹሉ የምታልፍ ሰላሙን እየቸረን በቁጣ ያይደለ በምህረቱ ዘወትር እየተዘከረን 'ይህችን ዓመት ተወኝ' ስንለው ልቡን ሳያጸና የተወደደችውን ይህችን ዕለት ያሳየን የጨመረልን ፤ ይመስገንልን ! እርሱ ዓመትን ሲጨምርልን በእኛ ላይ አላማ አለውና እኛም መጪውን ዘመን #በይቅርታ፤ በፍቅር፤በትኅትና፤ በበጎነት፤በታጋሽነት፤በየዋኀት ና በንጽሕና .... በመሰሉት በጎ ምግባራት ኹሉ ጥሙዳን ለመኾን አላማ ይዘን ደግሞም ሱታፌ አምላክ እያገኘን ወደ ቅዱስ እርሱ እርሱንም ወደ መምሰል የምናድግበት ያድርግልን ዘንድ በጎ ፈቃዱ ይኹንልን! ✨#ግዮን_መጻሕፍት ለመላው #የግዮን ቤተሰቦች ፳፻፲፰ የተባረከ ዓመት ይኾን ዘንድ እነህዲኹም ዓመቱን ብቻ ሳይኾን ስብእናችንም የሚቀየርበት፤ በዓሉም የፍቅርና የመተሳሰብ ያድርግልን፥ እያልን  በአያሌው የመሻት ስሜት ኾነን የሀገራችንን ሰላም እና አንድነት የቤተክርስቲያንንም ሰላምና ሉአላዊነት ሰፍኖ የምናይበት ይኹንልን ብለን ተመኘን  !🙏 #መልካም_አዲስ_ዓመት

📖'አባቶችህን፡ እወቅ'📖 'አባቶችህን፡ እወቅ፡ 'በሚል ፡ርዕስ ፡የተዘጋጀው፡ ይህ ፡መጽሐፍ ፡የዚህን ፡ነገረ ፡አበው፡ ትመህርት ፡ዓላማ፡ ለማሳካት፡ በሚረዳ መልኩ፡ ጥሩ ፡ኾኖ ፡የተዘጋጀ ፡መጽሐፍ
📖'አባቶችህን፡ እወቅ'📖 'አባቶችህን፡ እወቅ፡ 'በሚል ፡ርዕስ ፡የተዘጋጀው፡ ይህ ፡መጽሐፍ ፡የዚህን ፡ነገረ ፡አበው፡ ትመህርት ፡ዓላማ፡ ለማሳካት፡ በሚረዳ መልኩ፡ ጥሩ ፡ኾኖ ፡የተዘጋጀ ፡መጽሐፍ ፡ነው። #እኔ፡በበኩሌ፡ እንዲዘጋጁ ከምመኛቸው፡መጻሕፍት፡መካከል፡ አንደኛው፡ይህ ፡መጽሐፍ  ፡ነበር ።ስለኾነም ብዙ ፡ምንጮችን  ፡መመልከትን፡ የሚያሻውንና፡ ለይቶ፡ ጨምቆ ፡ለማቅረብ ብዙ ድካም ፡የሚጠይቀውን ፡ሥራ  በመሥራት፡ይህን መጽሐፍ  ፡አዘጋጅቶ ስላቀረበልን ወንድማችን #ዲያቆን_አቤል_ካሳሁንን ፡ከልብ ፡እያመሰገንኩ፡ እኛም፡ አንብበን ፡እንጠቀምበት ፡ዘንድ፡ እግዚአብሔር ፡ይርዳን ፡እላለሁ ። #መምህረ_ቤተክርስቲያን_ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ ➮ለተወሰነ ጊዜ ጠፍቶ የነበረው ይህ እጅግ ተፈላጊ እንዲኹም አስፈላጊ መጽሐፍ በድጋሚ የታተመ ቢኾንም ጥቂት ኮፒ ብቻ ስለኾነ የታተመው እንዳያመልጠን ..! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

ጷግሜ ፫ ✨ እንኳን አደረሰን✨ ዛሬ የበረቱ የዚኽቺ ኅብረት አባሎች ዘሬ ሌሊት [ጳጕሜን 2 ለ3 አጥቢያ] እንቅልፍ በዓይናቸው ሳይዞር በዓመቱ ቀኖች ቍጥር ልክ [365 ጊዜ] 'አቡነ ዘበሰማያት'ን ሲ
ጷግሜ ፫ ✨ እንኳን አደረሰን✨ ዛሬ የበረቱ የዚኽቺ ኅብረት አባሎች ዘሬ ሌሊት [ጳጕሜን 2 ለ3 አጥቢያ] እንቅልፍ በዓይናቸው ሳይዞር በዓመቱ ቀኖች ቍጥር ልክ [365 ጊዜ] 'አቡነ ዘበሰማያት'ን ሲጸልዩ በምስጋና ነደው እየበሩ መላእክትን በግብር መስለው ያድራሉ። እኛ በእነሱ ልክ [አባታችን ኾይን 365 ጊዜ] መጸለይ ቢያቅተን በአቅማችን ልክ [7 ጊዜም 12 ጊዜም እንደየተቻለን..] በምስጋና እንተባበራቸው። ነፍሳችን በጸሎት ቅዱሳኑን ትተባበራቸው ዘንድ #እግዚአብሔር ያበረታልን!!            ♱♱♱♱♱♱♱ 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623a

🌿🌿🌿🌿🌿 ጷግሜ ፫ ✨ እንኳን አደረሰን✨ ዛሬ የበረቱ የዚኽቺ ኅብረት አባሎች ዘሬ ሌሊት [ጳጕሜን 2 ለ3 አጥቢያ] እንቅልፍ በዓይናቸው ሳይዞር በዓመቱ ቀኖች ቍጥር ልክ [365 ጊዜ] 'አቡነ
🌿🌿🌿🌿🌿 ጷግሜ ፫ ✨ እንኳን አደረሰን✨ ዛሬ የበረቱ የዚኽቺ ኅብረት አባሎች ዘሬ ሌሊት [ጳጕሜን 2 ለ3 አጥቢያ] እንቅልፍ በዓይናቸው ሳይዞር በዓመቱ ቀኖች ቍጥር ልክ [365 ጊዜ] 'አቡነ ዘበሰማያት'ን ሲጸልዩ በምስጋና ነደው እየበሩ መላእክትን በግብር መስለው ያድራሉ። እኛ በእነሱ ልክ [አባታችን ኾይን 365 ጊዜ] መጸለይ ቢያቅተን በአቅማችን ልክ [7 ጊዜም 12 ጊዜም እንደየተቻለን..] በምስጋና እንተባበራቸው። ነፍሳችን በጸሎት ቅዱሳኑን ትተባበራቸው ዘንድ #እግዚአብሔር ያበረታልን!! ♱♱♱♱♱♱♱ ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📖ኦሪት ዘፍጥረት 📚 ...✍️ኦሪት ዘፍጥረት የኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ዋና ትምህርቶች ማለትም የነገረ ድኅነት፣ የነገረ ሰብእ፣ የነገረ ሥነ-ፍጥረት፣ ... መሠረት ነው፡፡ ኦሪት ዘፍጥረት ብዙ መተር
📖ኦሪት ዘፍጥረት 📚 ...✍️ኦሪት ዘፍጥረት የኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ዋና ትምህርቶች ማለትም የነገረ ድኅነት፣ የነገረ ሰብእ፣ የነገረ ሥነ-ፍጥረት፣ ... መሠረት ነው፡፡ ኦሪት ዘፍጥረት ብዙ መተርጉማን ትኩረት ሰጥተው በስፋትና በጥልቀት ካብራሯቸውና ከተረጎሟቸው ቅዱሳት መጻሕፍት አንዱ ነው፡፡ #እኔ_ያደረግሁት ከእነዚህ የተለያዩ አባቶች፣ ሊቃውንት እና መተርጉማን ሐሳቦች መካከል የተወሰኑትን አሰባስቦ ማቅረብ ነው፡፡ በማኅበረ ቅዱሳን የቴሌቪዥን መርሐ ግብር በተከታታይ ከቀረበው የኦሪት ዘፍጥረት ማብራሪያ ትምህርት የመጀመሪያዎቹ ዐሥር ምዕራፎች ትምህርት (ከምዕራፍ 1 -10) በዚህ መጽሐፍ ቀርቧል፡፡ በመጻሕፍት ትርጓሜ ውስጥ ልብ ሊባሉ የሚገባቸው ጉዳዮች አሉ። ከእነዚህ አንዱ ጉዳይ በቤተ ክርስቲያን መሠረታዊ አስተምህሮ (ዶክትሪን) እና በመተርጉማን ግላዊ አስተያየቶች መካከል ያለውን ልዩነት በሚገባ ለይቶ ማወቅ ነው፡፡ ..... በዚህ #መጽሐፍ የቀረቡትን የመተርጉማን ትርጓሜዎችና ማብራሪያዎች በአግባቡ ተረድተን #ለሕይወት እንድንጠቀምበት #የቃሉ ባለቤት #እግዚአብሔር ይርዳን፡፡ አሜን! #ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ #ኦሪት ዘፍጥረትን ብትን አድርጎ የሚያብራራ ብሎም ገቢውን ለታላቁ ማኅበር #ማኅበረ_ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት የተበረከተ ነው። ፨ይህ#መምህረ_መምህራን_ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ አበርክቶት ጥቂት ብቻ ነው የቀረ ሲኾን ይያዝ!!! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📖📖📖📖📖 #አፄ_ዘርዐ_ያዕቆብ_እና_ሥራዎቹ #አፄ_ዘርዐ_ያዕቆብ መንግሥት አጠቃላይ ቅጥር ግቢው በሁለት ዙር የተከበበ እና የታጠረ ሥፍራ ሲሆን፤ በአጥሩ ዙሪያም በቁጥር አሥራ ሦስት የሚደርሱ
📖📖📖📖📖 #አፄ_ዘርዐ_ያዕቆብ_እና_ሥራዎቹ #አፄ_ዘርዐ_ያዕቆብ መንግሥት አጠቃላይ ቅጥር ግቢው በሁለት ዙር የተከበበ እና የታጠረ ሥፍራ ሲሆን፤ በአጥሩ ዙሪያም በቁጥር አሥራ ሦስት የሚደርሱ የተለያዩ መጠሪያ ሥምና ተግባር(ግብር) ያላቸው በሮች (ዕድሞዎች) እናገኛለን። እነዚህ በሮች እያንዳንዳቸው የተለያየ ተግባር እና ስም ያላቸው ናቸው፡፡ ተግባራቸውን ወደ ኋላ የምናየው ሆኖ በስም ደረጃ ውድነሽ ደጅ፣ ጸር ዋጀት ደጅ፣ መርድ ደጅ፣ መጋረጃ ደጅ፣ መስቀል ደጅ፣ ውላጅ ደጅ፣ ግምጃ ማርያም ደጅ፣ ኢየሱስ ደጅ፣ ቁልፍ ደጅ በመባል ይታወቁ ነበር፡፡ በቤተ መንግሥቱ ውስጥ በርካታ ቤቶችና ድንኳኖች የነበሩ ሲሆን፤ የቀኝ በሀልቲሐት ቤት፣ የግራ በሀልቲሐት ቤት፣ የባሀልቲሐት ሽና ቤት፣ የንግሥቷ እናት ቤት፣ የዐቃቢ ሰዓት ቤት፣ የቀኝ ብሕትወደድ ቤት፣ የግራ ብሕትወደድ ቤት፣ የግብፅ ጳጳስ ቤት፣ የንጉሥ ዋና አዳራሽ ቤት፣ የሰቀላ (የጥበቃዎች ቤት፣ የአንበሶች ቤት፣ ከዚህ በተጨማሪ የቀኝ ጀጎላ ሦስት የተለያዩ ድንኳኖች(ደበና)ነበሩት፡፡ በመካከላቸው የተተከለው ድንኳን ዱለት ቤት፣ በቀኝ በኩል ያለው ግምጃ ድንኳን እና በግራ በኩል ያለው አቋት ግምጃ ድንኳን ተብሎ ይጠራ እንደነበረ ተዘግቦ ይገኛል።       [ከውስጥ ገጽ..] 🌿#ይህ የንጉሡ ዜና መዋዕል እኛ ዘንድ አለ! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📖❖ ሀብታም እና ደሀ📖 ...ባለጸጋው ድሀውን በየዕለቱ ደጃፉ ላይ ዓይኑ ስር ወድቆ እያየው ምንም ዓይነት ምጽዋት አልሰጠውም፡፡ ይህ ምስኪን ድሀ በጎዳና ወይም በተሰወረ በጠባብ መተላለፊያ ስላልወ
📖❖ ሀብታም እና ደሀ📖 ...ባለጸጋው ድሀውን በየዕለቱ ደጃፉ ላይ ዓይኑ ስር ወድቆ እያየው ምንም ዓይነት ምጽዋት አልሰጠውም፡፡ ይህ ምስኪን ድሀ በጎዳና ወይም በተሰወረ በጠባብ መተላለፊያ ስላልወደቀ ባለጸጋው አንዴ ወይም ሁለቴ ወይም ብዙ ጊዜ ሲገባና ሲወጣ አይቶታል፡፡ ነገር ግን ሲገባም ሆነ ሲወጣ በውድም ሆነ በግድ ሊያየው በሚችልበት ....... ...ስለ መተላለፋችን ምንም ዓይነት ቅጣት የማንቀበል ቢሆን ኖሮ እግዚአብሔር ሕሊናን የሚያህል ፈራጅ ዳኛ በውስጣችን አይፈጥርም ነበር፡፡ በዚህም እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ያለውን ፍቅር አሳይቷል፡፡ እግዚአብሔር ስለ መተላለፋችን ከዚህ በኋላ በሚኖረው ሕይወት የሚጠይቀን ቢሆንም የማያዳላውን ዳኛ ሕሊናን ግን በውስጣችን ፈጠረ፡፡ ይህ ዳኛ በዚህ ዓለም ሳለ ይረዳናል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ያለው ..... [ከመጽሐፉ የተወሰደ] ➮ወገን ራስን ለመፈተሽ አይነተኛ መርማሪ ነው ...! እመነኝ የት ጋር እንዳለህ ይነግርሀል!..ይያዝዝ📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623