es
Feedback
ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።

ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።

Ir al canal en Telegram

📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623

Mostrar más
3 309
Suscriptores
-224 horas
-97 días
-3630 días
Archivo de publicaciones
#እናታችን_እመቤታችን ብዙኃን ''ማርያም'' ----- በቤተ ክርስቲያናችን ከሚዘከሩ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ክብረ በዓላት መካከል መስከረም ፳፩ ቀን የሚውለው በዓል ‹‹ብዙኃን ማርያም››
#እናታችን_እመቤታችን ብዙኃን ''ማርያም'' ----- በቤተ ክርስቲያናችን ከሚዘከሩ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ክብረ በዓላት መካከል መስከረም ፳፩ ቀን የሚውለው በዓል ‹‹ብዙኃን ማርያም›› በመባል ይታወቃል፡፡ በዓሉ በሁለት ዐበይት ምክንያቶች ይከበራል፤ የመጀመሪያው ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ሃይማኖታዊ ውሳኔ ለማዘጋጀት ከሩቅም ከቅርብም የተሰባበሰቡት ቀን፤ ሁለተኛው ደግሞ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት ዕፀ መስቀል በግሸን ደብረ ከርቤ የተቀመጠበት ዕለት መኾኑ ነው፡፡ ❝#ርግቤ ሆይ ነዪ ሐዋርያት የሚያመሰግኑሽ መላእክትም የሚላላኩልሽ #መልካሜ ሆይ ነዪ። #የሕይወት_ውበት ከሊባኖስ ወጥተሽ ነዪ።❞    "#ለኲሉ_ፍጥረት_ትተነብል"          "#ለፍጥረት_ሁሉ_ትለምናለች" ''እንኳን አደረሰን!'' 📚ግዮን መጻሕፍት  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

✨#ዜና_መጽሐፍ 📖#አንጋረ_ሊቃውንት📖 #ትናንት የሌለው ዛሬ፣ መነሻ የሌለው መድረሻ የለውም፡፡ የእኛ ዛሬነት የትናንት መነሻነት ሲኾን፤ የዛሬው ማንነታችን ደግሞ ለነገዎቹ መነሻ ነው፡፡ “በቃል ያ
#ዜና_መጽሐፍ 📖#አንጋረ_ሊቃውንት📖 #ትናንት የሌለው ዛሬ፣ መነሻ የሌለው መድረሻ የለውም፡፡ የእኛ ዛሬነት የትናንት መነሻነት ሲኾን፤ የዛሬው ማንነታችን ደግሞ ለነገዎቹ መነሻ ነው፡፡ “በቃል ያለ ይረሳል፣ በመጽሐፍ ያለ ይወረሳል” እንዲሉ፤ የዛሬ እኛዎች የትናንት ዛሬዎች፣ የነገ ትናንቶች እንደ መኾናችን መጠን፤ ከቀድሞ ጀምሮ ቃል በቃል ሲነገር የመጣውን የአባቶቻችን ብሂል ለዛሬ ተጠቅመንበት ቀጣይ ትውልድም እንዲጠቀምበት ለማስቻል መ/ር ሐዲስ ደከመኝና ስለቸኝ ሳይሉ ከአበው ቃል በቃል የመጣውንና ከመጻሕፍት ያገኙትን አሰባስበው ያቀረቡልን በመኾናቸው የአባቶች በረከት አይለይዎት በማለት ልባዊ ምኞቴን እገልጻለሁ። በዚሁ አጋጣሚ ቀደምት አባቶቻችን እንኳን ፍቅራቸውን፤ ሊያስተላልፉ የፈለጉትን መልዕክት ለጆሮ በማይጎረብጥ፣ ልብን በሚመስጥ ኹኔታ ይገልጹ እንደ ነበር መረዳት ችያለሁ፡፡ #መምህር_ዳግማዊ_ሙሴ [የመጽሐፈ ምንኃር አዘጋጅ] #አንብበው_ሲጨርሱ_ሼር_ማድረግ_አይርሱ! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

✨✨✨✨✨✨ † ቅዱስ መስቀል † ❝መስቀል ሰይጣንን የሚያጠፋ ምሳር ነው ፤ የአጋንንትንም ራሶች የሚቆርጥ ሰይፍ ነው ፤ መስቀል ርኩሳን መናፍስትን የሚወጋቸው የእሳት ዘገር ነው ፤ የአመስቴማውያንንም
✨✨✨✨✨✨ † ቅዱስ መስቀል †     ❝መስቀል ሰይጣንን የሚያጠፋ ምሳር ነው ፤ የአጋንንትንም ራሶች የሚቆርጥ ሰይፍ ነው ፤ መስቀል ርኩሳን መናፍስትን የሚወጋቸው የእሳት ዘገር ነው ፤ የአመስቴማውያንንም ሠራዊት የሚመታ የመብረቅ ጦር ነው፡፡ መስቀል ማኅተመ ሥላሴ የሌለው ሰው ወደ እርሱ ሊቀርበው የማይቻለው አምባ መጠጊያ ነው። መስቀል ከግራም ከቀኝም ለሚመጣ ጠላት የጽድቅ ጋሻ ነው፡፡ መስቀል የጦር ውጋት ሊቀድደው ፣ የቀስትና የዘንግም ጫፍ ሊበሳው የማይችል የሃይማኖት ጥሩር ነው፡፡ መስቀል አማሌቃውያንን ለመዋጋት በራፊድ በረሐ በተዘረጋው በሙሴ እጅ አምሳል የተሠራ ነው፡፡ መስቀል በሙሴ እጅ ወደ ውስጥ በተጨመረ ጊዜ መራራውን ውኃ በሱር በረሐ ያጣፈጠ ነው፡፡ መስቀል የቅድስናና የንጽሕና ማኅተም ነው፡፡ ❞ [  ውዳሴ መስቀል  ] ✨እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ አደረሰን ! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

                          †                                                                        🕊                       🕊          †    መስቀል    †          🕊 🌼    --------------- † ---------------    🌼 ❝  መስቀል ሰይጣንን የሚያጠፋ ምሳር ነው ፤ የአጋንንትንም ራሶች የሚቆርጥ ሰይፍ ነው ፤ መስቀል ርኩሳን መናፍስትን የሚወጋቸው የእሳት ዘገር ነው ፤ የአመስቴማውያንንም ሠራዊት የሚመታ የመብረቅ ጦር ነው፡፡ መስቀል ማኅተመ ሥላሴ የሌለው ሰው ወደ እርሱ ሊቀርበው የማይቻለው አምባ መጠጊያ ነው። መስቀል ከግራም ከቀኝም ለሚመጣ ጠላት የጽድቅ ጋሻ ነው፡፡ መስቀል የጦር ውጋት ሊቀድደው ፣ የቀስትና የዘንግም ጫፍ ሊበሳው የማይችል የሃይማኖት ጥሩር ነው፡፡ መስቀል አማሌቃውያንን ለመዋጋት በራፊድ በረሐ በተዘረጋው በሙሴ እጅ አምሳል የተሠራ ነው፡፡ መስቀል በሙሴ እጅ ወደ ውስጥ በተጨመረ ጊዜ መራራውን ውኃ በሱር በረሐ ያጣፈጠ ነው፡፡ መስቀል የቅድስናና የንጽሕና ማኅተም ነው፡፡ ❞ [  ውዳሴ መስቀል  ] ✨እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ አደረሰን !

#የመጽሐፍ_ቅዱስ_ታሪኮች_ለልጆች #የልጆች የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች በመጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር የታተመ ውስጡ ከለርድ ልጆችን በሚማርክ መልኩ የተዘጋጀ ነው። ልጆቻችንን የነገ የቤተክርስቲያን ተረካቢ እንደ
#የመጽሐፍ_ቅዱስ_ታሪኮች_ለልጆች #የልጆች የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች በመጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር የታተመ ውስጡ ከለርድ ልጆችን በሚማርክ መልኩ የተዘጋጀ ነው። ልጆቻችንን የነገ የቤተክርስቲያን ተረካቢ እንደመኾናቸው በሃይማኖትና በወንጌል ኮትኩተን በማሳደግ ኃላፊነታችን እንወጣ ዘንድ እንዲያስፈልግ ልብ ይሏል ! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

#ገድለ_አቡነ_ሐራ_ድንግል #ማኅቶተ ቤተክርስቲያን ጳውሎስ ከመዠመሪያ አንሥቶ የነበሩ የቅዱሳንን ስም እየጠራ ገድላቸውን እየጠቀሰ በቃልም በመልእክትም ያስተምር ነበር፡፡ ዕብ. ፲፩፥፴፪ “እንግዲህ ም
#ገድለ_አቡነ_ሐራ_ድንግል #ማኅቶተ ቤተክርስቲያን ጳውሎስ ከመዠመሪያ አንሥቶ የነበሩ የቅዱሳንን ስም እየጠራ ገድላቸውን እየጠቀሰ በቃልም በመልእክትም ያስተምር ነበር፡፡ ዕብ. ፲፩፥፴፪ “እንግዲህ ምን እላለሁ፤ የጌዴዎንን፣ የባርቅን፣ የዮፍታሔን፣ የሶምሶንን፣ የዳዊትን፣ የሳሙኤልን የሌሎችንም ነቢያት ነገር ልነግራችሁ ቀን ያጥርብኛልና፡፡ በሃይማኖት የተጋደሉትን ነገሥታትን ድል የነሡትን ዋጋቸውን ያገኙትን ትሩፋት የሠሩትን ተስፋቸውን ያገኙትን የአንበሶችን አፍ የዘጉትን ዋዕየ እሳትን ያጠፉትን፣ ከጦር ስለት የዳኑትን፣ በመከራቸው የፀኑትን በሰልፍ ጊዜ የበረቱትን፣ የጠላቶቻቸውን ጭፍራ ያሳደዱትን ነገር እንዳልነግራችሁ ቀን ያጥረኛል፡፡” “ከመከራ እንዲድኑ አልወደዱምና፤ የገረፏቸው የዘበቱባቸው፣ አስረው ያጋዟቸውም አሉ፤ በመጋዝ የሰነጠቋቸው፣ በድንጊያ የደበደቧቸው፣ በሰይፍ ስለት የገደሏቸው አሉ፤ ማቅ የተልባ እግር የፍየል ሌጦ ለብሰው ዞሩ፤ ተጨነቁ፣ ተቸገሩ፣ መከራ ተቀበሉ፣ ተራቡ፣ ተጠሙ፡፡” ዕብ. ፲፩፥፴፪ ብርሃነ ዓለም ጳውሎስ እንዲህ እያለ በጠቅላላው እግዚአብሔርን ስለማመናቸው ምክንያት ቅዱሳን ላይ የደረሰባቸውን መከራና የቻሉትን መቻል ካስዘከረ በኋላ ገድላቸውን እያሰብን እንድንማርበትና እኛም አሰረ ፍኖታቸውን እንድንከተል ቀጥሎ “ስለዚህም እንደደመና የሚከቡን እነዚህ ሁሉ ምስክሮች ያሉን እኛ የኃጢአትን ትብትብና ሸክም አውርደን እንጣል፤ ሃይማኖት ወደሚያስገኝልን ወደሚጠብቅልን ተስፋችን በትዕግሥት እንገሥግሥ” ይለናል፡፡ ፲፪፥፩ #ገድላቸውን አንብበን ከበረከታቸው የምንሳተፍ ያድርገን! 👉#ማሳሰቢያ የቀረን የተወሰነ ፍሬ ነውና እንዳያመልጥዎ

📖#አንድሮሜዳ📖 #የዶክተር_ሮዳስ አንድሮሜዳ የተሰኘው መጽሐፍ የጥንት ኢትዮጵያውያን የሕዋ ሥልጣኔ ከዘመናዊው ሳይንስ አንጻር በደንብ ፍንትው አድርጎ የሚያብራራ እንዲሁም ከሕጻናት እስከ አዋቂ እን
📖#አንድሮሜዳ📖 #የዶክተር_ሮዳስ አንድሮሜዳ የተሰኘው መጽሐፍ የጥንት ኢትዮጵያውያን የሕዋ ሥልጣኔ ከዘመናዊው ሳይንስ አንጻር በደንብ ፍንትው አድርጎ የሚያብራራ እንዲሁም ከሕጻናት እስከ አዋቂ እንዲረዳው ተቀምሞ የተዘጋጀ ለልጆች ደግሞ ንቃተ ሕሊናን የሚያስጎነጭ ጥዑም ጦማር ነው ። ለዚህ ሳምንት ለልዩ ቅናሽ የመረጥነው መጽሐፍ ነው ። ቻናሉን #ሼር በማድረግ ወዳጆቻችሁን ተጠቃሚ ከድርጉ!

📖#ሐተታ_ዘቅዱስ_አትናቴዎስ #ያለሀሰት ቅዱስ አትናቴዎስ ለቤተክርስትያን አምድ ከምንላቸው ቅዱሳን አባቶቻችን አንዱና ዋነኛው መኾኑ አያጠያይቅም ታድድያ ከእርሱ ግሩማን አበርክቶዎች መካከል "ተስእሎ
📖#ሐተታ_ዘቅዱስ_አትናቴዎስ #ያለሀሰት ቅዱስ አትናቴዎስ ለቤተክርስትያን አምድ ከምንላቸው ቅዱሳን አባቶቻችን አንዱና ዋነኛው መኾኑ አያጠያይቅም ታድድያ ከእርሱ ግሩማን አበርክቶዎች መካከል "ተስእሎተ አንትያኮስ" የተሰኘውን መጽሐፍ #መምህር_ቃለ ጽድቅ_ሕግነህ በተዋበ እና ለንባብ ምቹ አድርገው የተረጎሙት ሲኾን ➱ቅዱስ አትናቴዎስ በዚህ መጽሐፍ ከሚመልሳቸው ጥያቄዎች .....አንትያኮስ፡ ርኩሳን መናፍስት የሆኑ አጋንንት ከቅዱሳት መጻሕፍት የሚፈሩት የጸሎት ዐይነት የቱ ነው? ➮ጥያቄ ፦ በውኑ ለኃጥአን ነፍሳት በዚህ ዓለም ዘመዶቻቸው የመታሰቢያ(ተዝካር) ቍርባን፣ ጸሎትና ምጽዋት ቢያደርጉላቸው በዚያኛው ዓለም ይጠቅማቸዋልን? ➮ጥያቄ ፦ ለሰው እጅ ሥራዎች እንዳንሰግድ እግዚአብሔር በነቢያቱ አዝዞናልና ለምን የሰው እጅ ለሠራው ለቅዱሳን ሥዕልና ለቅዱስ መስቀሉ እንሰግዳለን? ➮አንትያኮስ፡- ከኃጢአት ሁሉ የሚበልጠው ኃጢአት የቱ ነው? ➮አንትያኮስ፡- ብዙ በደልንና ኃጢአትን የሠራ ሰው ቢኖር ከዚያም በኋላ ንስሓ ቢገባ፤ እንደገና ተመልሶ ኃጢአት ቢሠራ እግዚአብሔር ንስሓውን ይቀበለዋልን ወይስ አይቀበለውም? #ይህንና መሰል ጥያቄዎችን ከነ መልሶቻቸው የያዘ ልዩ መጽሐፍ በመኾኑ እንድታነቡት ግብዣችን ነው! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL ,በEMS እንዲሁም የ delivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። 📱ይደውሉልን ፦0913083816 Telegram https://t.me/GhionBookStore1623

📚ግዮን መጻሕፍት @GhionBookStore1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/GhionBookStore1623

✨📖 #ወንጌል_ቅዱስ ✨📖 .....፱/ ወእመኒ ዐይንከ ታስሕተከ ምልሓ ወግድፋ እምላዕሌከ፤ ዓይንህ ብታስትህ አውጥተህ ጣላት፡፡ እስመ ይኄይሰከ ነቋረከ ትባእ ውስተ ሕይወት እምእንዘ ክልኤ ዐይን ብ
✨📖 #ወንጌል_ቅዱስ ✨📖 .....፱/ ወእመኒ ዐይንከ ታስሕተከ ምልሓ ወግድፋ እምላዕሌከ፤ ዓይንህ ብታስትህ አውጥተህ ጣላት፡፡ እስመ ይኄይሰከ ነቋረከ ትባእ ውስተ ሕይወት   እምእንዘ ክልኤ ዐይን ብከ ትትወደይ ውስተ እሳተ ገሃነም፡፡ ➮ዛሬ በዚህ _ ዓለም ሁነህ ኑረህ፤ ኋላ ገሃነም ከምት ወርድ፤ ዛሬ በዚህ ዓለም አንድ ": ዓይን ሁነህ ኑረህ ኋላ መንግሥተ ሰማያት ብትገባ ይሻለሃልና፡፡ #አንድም ወእመኒ ዓይንከ ብለህ ሁሉ ንም አንብብ፡፡➮#የነቀፍከውን ኤጲስ ቆጶስ ሹመህ ኑረህ ኋላ ገሃነም ከምትወርድ ፤ ዛሬ በዚህ ዓለምየነቀፍከውን ኤጲስ ቆጶስ ሽረህ ያልነቀፍከውን ኤጲስ ቆጶስ ሹመህ ኑረህ ኋላ መንግሥተ ሰማያት ብትገባ ይሻልሃልና፡፡ ዑቁ ኢታስተሐቅርዎ ለአሐዱ እምእሉ ንዑሳን፤ ➮#በእኔ ካመኑ ከምእመናን አንዱን አትናቁ አታቃሉ እንዳትንቁእንዳታቃልሉ አስተውሉ፡፡ #የማቴዎስ_ወንጌል_ከምዕራፍ_፲፰ ✨ወንጌላችንን እንዲህ አንድ በአንድ እስከ ትርጓሜው ማወቅ ግድ ነው !ከቀድሞ አባቶች ሲተረጎም የመጣው ንባቡና ትርጓሜው በአንድምታ አድርገው  ለአይን ጎላ ባለ ና ለንባብ ደግሞ በቀለም የተለየ ና በምቹ  ኹኔታ ያቀረቡልልን #መጋቢ ሐዲስ ቃለ ሕይወትን እያመሰገንን እጅግ ወሳኝ  በመኾኑ ባያመልጠን መልካም ነው እንላለን! 📚ግዮን መጻሕፍት @GhionBookStore1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/GhionBookStore1623

አዎ:- የእመቤታችን የማርያም ዐሳብ እንደ አምላክ ዐሳብ ነው! ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ "እኛ የክርስቶስ ልብ አለን" ብሏል። ፩ቆሮ ፪: ፲፮። ልብ ማለት አዕምሮ ነው። ዐሳብ የሚቀዳው ከልብ ነው። "
አዎ:- የእመቤታችን የማርያም ዐሳብ እንደ አምላክ ዐሳብ ነው! ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ "እኛ የክርስቶስ ልብ አለን" ብሏል። ፩ቆሮ ፪: ፲፮። ልብ ማለት አዕምሮ ነው። ዐሳብ የሚቀዳው ከልብ ነው። "አምላክህንም እግዚአብሔርን በፍጹም ልብህ፥ በፍጹምም ነፍስህ፥ በፍጹምም ኀይልህ ውደድ።" ሲል አዕምሮን ወይም ዐሳብን ያመለክታል። ዘዳ ፮ : ፭። ዐሳብ፣ ልብ እና አዕምሮ የሚሉትን የሚተካኩ ቃላት በተለዋዋጭነት ልንጠቀምባቸው እንችላለን። ቅዱስ ጳውሎስ እኔ ብቻ የክርስቶስ ልብ አለኝ አለማለቱንም ልብ እንበል። እኛ ነው ያለው። እኛ ሲል እርሱን የሚመስሉትን፣ የሚያኽሉትን፣ የሚበልጡትንም ኹሉ ያጠቃልላል። ከሚበልጡት አንዷ ድንግል ማርያም ናት። ቅዱስ ዳዊትን እግዚአብሔር እንደ ልቤ ብሎታል። "እንደ ልቤ የኾነ ሰው ፈቃዴንም ኹሉ የሚያደርግ የእሴይን ልጅ ዳዊትን አገኘሁ" እንዲል። ሥራ ፲፫: ፳፪። እግዚአብሔር የእጁን ፍጡር እንደ ልቤ ብሎታል። እርሱ ያልቸገረውን አንተን ለምን ይቸግርሃል? ቅዱስ ጳውሎስ እኛ ካላቸው መኻል ከኹሉ በላይ ቀዳሚ የምትኾነው የእመቤታችን ዐሳብ እንደ አምላክ ዐሳብ ነው ማለት እጅግ በጣም ትክክል መኾኑን ተመልከት። በተለያየ ጥፋት ሲወድቁ ሲነሡ የኖሩት ቅዱስ ዳዊት እና ቅዱስ ጳውሎስ በዚህ ደረጃ ሲገለጡ በዘመኗ ኹሉ ያለ ስሕተት ያለ ኃጢአት በፈቃደ እግዚአብሔር ብቻ የኖረች እመቤት እንዲህ ስትገለጥ ለምን አመመህ? ነው ወይስ ከአምላክ ሕሊና እኩል ያደረግናት ይመስልሃል? እንደ እርሱ ማለት እንዳልኾነ ቅዱስ ዳዊት እና ቅዱስ ጳውሎስ የተገለጡበትን መላልሰህ አንብብ።

#ዶክተር_እጓለ ፦በተውሶ መነጽር እራስንና ማንነትን የማኮሰስ ደዌ #ያላገኛቸው ኢትዮጵያዊ ሊቅ ናቸው ። -#የኢትዮጵያን ሥነ-ጽሑፍ ያጠኑ፤ የመረመሩ ለነበሩ ጥንታዊ ሀገር በቀል ባህልና እውቀት አክብ
#ዶክተር_እጓለ ፦በተውሶ መነጽር እራስንና ማንነትን የማኮሰስ ደዌ #ያላገኛቸው ኢትዮጵያዊ ሊቅ ናቸው ። -#የኢትዮጵያን ሥነ-ጽሑፍ ያጠኑ፤ የመረመሩ ለነበሩ ጥንታዊ ሀገር በቀል ባህልና እውቀት አክብሮት ያላቸው ሊቅ በመኾናቸው የሀገራቸውን ጽሑፎች ሲያጠኑና ሲመረምሩ መንፈሳቸውና አእምሯቸው ከፍ ወዳለ መራቀቅ ደረጃ ከደረሱት ጥቂት ማሰብ ከሚችሉ ሊቃውንት መካከል እጓለ አንደኛው ናቸው። [ፍካሬ እጓለ በተመስገን ዋና የቀረበ] ....ከመጽሐፉ ለቅምሻ #ሰውን ጥቅም፤ ተድላ፣ ደስታ ብቻ ተፈላላጊ አድርጐ በመመልከት ፤ ይህንኑ ምኞቱን የሚያረካበት ትምህርት ብናቀርብለት የሚጐዳ፣ የሚበደል እንጂ የሚጠቀም አይደለም፡፡ ምክንያቱም ሰዎች በመላ ለዚህ ነገር ብቻ ቢሰለፉ በማኅበራዊ ኑሮ ውስጥ ያለው ውድድር መልኩን ለውጦ ያለመጠን አስቸጋሪና የሚያፋጅ ሊሆን ይችላል። በተለይም ይኸ እንዲህ ያለ ጥቅምን ብቻ የሚመለከት ትምህርት የሚያስገኘው ጠባይ ከሥልጣን ጋር የተገናኘ እንደሆን ነገር ጨርሶ ሊበላሽ ይችላል ለኔ ማለት ይሰፍናል። ---- ❝የሰው ልጅና ማድጋ ጆሮውን ካልያዙት አሟልጮ ይወድቃል!❞[እዝነ-ልቡናን ያጠይቃል] #በርግጥ ይህ መጽሐፍ በዓይነቱ እስካሁን በአማርኛ ከተጻፉ መጻሕፍት ሁሉ ብቸኛና ዘላቂ ይዞታ ያላቸው ድርሰተቶች ከምንላቸው ተቀዳሚው ነው! እንግዲያ ብቅ በሉና ደጋግማችኹ ሸምቱት ቅርስ ነውና! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

#የግዮን_ወንዝ #በዲያቆን_ሄኖክ_ኃይሌ የተጦመረው ይህ ጥዑም መጽሐፍ በድጋሚ ታትሟል! እንደሚታወቀው ደግሞ ሙሉ ገቢው ለታላቁ የምድራችን ቅድስተ ቅዱሳን ክፍሎች ውስጥ አንዱ ለኾነው ለደብረሊባኖስ ገ
#የግዮን_ወንዝ #በዲያቆን_ሄኖክ_ኃይሌ የተጦመረው ይህ ጥዑም መጽሐፍ በድጋሚ ታትሟል! እንደሚታወቀው ደግሞ ሙሉ ገቢው ለታላቁ የምድራችን ቅድስተ ቅዱሳን ክፍሎች ውስጥ አንዱ ለኾነው ለደብረሊባኖስ ገዳም ሕንጻ ማሰሪያ እንዲውል የተደረገ ነው ።እኛም ከንባቡ ተጠቅመን ጸኃፊውን እየመረቅን ገዳማችንን እንርዳ ...!

#ዜና_መጽሐፍ በወጉ ያልተዘከሩት ምሁር መጽሐፍ        ( ዶ/ር ሥርግው ሐብለሥላሴ) [ጸጋው ማሞ እንዳሰናዳው] ፨"ሥርግው ምን አልባትም በ20ኛው ክፍለ ዘመን ካሉት ብቸኛው የኢትዮጵያ የጥንታዊ ታሪክ ሊቅ ነው"  ይላሉ ኤርትራዊው የታሪክ ተመራማሪ ፕሮፌሰር "ባህሩ ተፍላ"  ስለ ጥረታቸውና ሀቃዊ የታሪክ ትንተናቸው ፕሮፌሰር መስፍን ወልተማሪያምም  "በመክሸፍ እንደ ኢትዮጵያ ታሪክ " መጽሐፋቸው ላይም ምሥክርነታቸውን በአድናቆት ሰጥተዋል። ተቀዳሚ ምሁር ፕሮፌሰር ሥርግው  ሐብለሥላሴ በሀገር ውስጥ እና ከሀገር ውጭ ተምረው ባካበቱት ሰፊ እውቀት ላይ ተንተርሰው አያሌ የታሪክ ጥናቶችን እንዳካፈሉን ይታወቃል።  ከሁሉም በላይ ግን " የኢትዮጵያ  የብራና ጽሑፎች ማይክሮ ፊልም ድርጅት " ዳይሬክተር ሆነው በሰሩት  ዘመን ተሻጋሪ ሥራ የዓለም ሕዝብ ሁሉ ሲዘክራቸውም ይኖራል ። #የኢትዮጵያ ሕዝብ የእርሳቸውን  የድካም  ሥራዎች ተገንዝቦ ተገቢውን ክብር ሊቸራቸው ይገባል። ➮ከእርሳቸው የበዙ ሥራዎች መካከል አንዱ  እና ግዙፍ የሆነው "አማርኛ የቤተ ክርስቲያን መዝገበ ቃላት " ሲሆን ይኸውም በብርቱ ያላሰለሰ ጥረት እና ድካም የተሰራ፤ ዘመን የማይሽረው ከወረት የተሻገረ እጅግ ድንቅ ሥራ ነው። ይኸ ግዙፍ መዝገበ ቃላት በኢትዮጵያ እና በኢትዮጵያ ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን ውስጥ  ከጥንት ጀምሮ የነበሩ ተጽእኖ ፈጣሪ የሆኑ የታላላቅ  ሊቃውንትን ፣ ቅዱሳንን ፣ ገዳማትን እና አድባራትን ታሪክ በመረጃ የሰነደ ድንቅ ሥራ ነው ።  #ይኸ ታሪካዊ መዝገበ ቃላት ለታሪክ ተመራማሪዎች ፣ ለሥነ ጽሑፍ ሰዎች ፣ ለሥነ መለኮት አጥኝዎች ፣ ለሥነ ሰብእ መርማሪዎች እንደዚሁም ታሪክ ለሚወዱ ሰዎች እጅግ ጠቃሚ የሆነ መጽሐፍ ነው ። ለምሳሌ በገጽ 662 ላይ "ገላኔ"ን እንዲህ ያብራራልናል " /እመት/ በ19ኛው ምእት ዓመት የኖረች የጉድሩ ሴት። ባሉዋ ዋቅጅራ ይባላል። ከእነዚህ አብራክ የተገኘው ወንድ ልጅ  ነገሮ ይባላል...ይኸውም ተክለ ኢየሱስ የተባለው የኢትዮጵያን ታሪክን ጽፎ ያቆየን ነው " በማለት ይገልጽና መረጃውን ከታች ያስቀምጥልናል። ⨳ሌላው  የሚያሳስቱ ተመሳሳይ ስም ያላቸውን የተጽእኖ ፈጣሪ ሰዎችን እና የቦታ ስሞች በወጉ እንድንለይም ይጠቀመናል ።ለምሳሌ በዚህ መጽሐፍ ላይ ከ35 በላይ ዮሐንስ የሚባሉ ታላላቅ ታሪካዊ ሰዎች በግልጽ ተብራርተዋል ።  ጀርመኖች ታላቁን  "Encyclopedia of Aethiopica " ከመስራታቸው በፊት የተሰራ ምናልባትም ለዚህ ስራ ታላቅ ግብአት የሆነ መጽሐፍ ነው።  ◆አሁንም የፕሮፌሰር ሥርግው ሐብለሥላሴን የድካም ውጤት "ኢትዮፋጎስ የመጽሐፍ ማእከል"ከኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ ተመጻሕፍት አገልግሎት " ጋር በመተባበር በእጅ ጽሑፍ የነበረውን 13 ቅጽ አርትኦት በመሥራት በሁለት ግዙፍ መጽሐፍት በማሳተማቸው ከፍተኛ ክብር እና ምሥጋና ይገባቸዋል። ከእኛ የሚጠበቀው በከፍተኛ ልፋት ተጋጅቶ የቀረበልንን ጥሩ  ማዕድ መመገብ ብቻ ነው ። #ዶ/ር እጓለ ገብረዮሐንስ "ከመጻሕፍት   የሚደገሙት ጥሩዎቹ ናቸው " ይላሉ ።  እንደዚሁም 'ማርክ ትዋይን' የተባለ ሊቅ ደግሞ "ጥሩ መጽሐፍትን የማያነብ ሰው  ማንበብ ከማይችል ሰው አይሻልም " ይላል ። ይኸ መጽሐፍ ደግሞ ከጥሩዎቹ አንዱ ስለሆነ #በእያንዳንዱ ቤተ መጻሕፍት እና መደርደሪያ ውስጥ ሊገኝ የሚገባ ግሩም መጽሐፍ ነው ። 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼#ሰንበትን_በግዮን_ከቅዱሳት_መጻሕፍት_ጋር🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 ገብተዋል... 📖📖📖📖📖📚 #ትወደኛለህን ? እና #ፍቅር
+1
📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼#ሰንበትን_በግዮን_ከቅዱሳት_መጻሕፍት_ጋር🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 ገብተዋል... 📖📖📖📖📖📚 #ትወደኛለህን ? እና #ፍቅር ✨እነዚህን ኹለት ተወዳጅ መጻሕፍት #በቀሲስ_ታምራት_ውቤ የተቀመሙ ሲኾኑ አንደኛው እንደውም የቅዱስ ዮሐንስ ትምህርት ነበር በጥሩ ኹኔታ መልሰውታል.....ከታተሙ ሰንበት ያሉ ቢኾንም ቶሎ በማለቃቸው ብዙዎቻችን እጅ ሳይገባ አልቆ ነበር ፤ ኾኖም ለኛ በማሰብ ድጋሚ ስላሳተሙልን #ለቀሲስ ባሉበት እጅ ንሻችንን ይድረሳቸው እያልን፤ ኋላ እንዳያልቁብን ቶሎ ይያዙ ዘንድ እናሳስባለን ...! 💚💛❤️     #ሰናይ_ዕለተ_ሰንበት!🙏 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623