uz
Feedback
Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗

Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗

Kanalga Telegram’da o‘tish

Addis Ababa, Ethiopia Con-Site is a Comprehensive Construction Filed Works and Materials Reference Catalogue for Architects, Engineers, Consultants and Customer service. t.me/ConsitesolutionBot ☜|]Chat us! Buy ads: https://telega.io/c/consite

Ko'proq ko'rsatish
3 609
Obunachilar
-424 soatlar
-47 kun
+1130 kun
Postlar arxiv
ማስታወቂያ ለተጠባባቂ ማህበር ቤት ተመዝጋቢዎች
+5
ማስታወቂያ ለተጠባባቂ ማህበር ቤት ተመዝጋቢዎች

የዝግ ጨረታ ሽያጭ ማስታወቂያ
የዝግ ጨረታ ሽያጭ ማስታወቂያ

💥ተቋራጮችን ከመንግስት ግዢ አቅራቢዎች ዝርዝር ማገድ [Suspension from Suppliers List] ⚡️በመንግስት ግዢ ወቅት በሚፈፀሙ የስነ-ስርዓት ግድፈቶች ምክንያት ጥቅሜ ተነክቶብኛል የሚል አቅራቢ ወይም ተጫራች  ለግዢ ፈፃሚው የመንግስት አካል ወይም ለአቤቱታ አጣሪው ቦርድ አቤቱታ የማቅረብ መብት እንዳለው የአዋጁ አንቀፅ 70(1) እንዲሁም የመመሪያው አንቀፅ 43 ይገልፃሉ፡፡ ነገር ግን አቤቱታ የማይቀርብባቸው ጉዳዮችም እንዳሉ አንቀፅ 70(2) እና 44 በዝርዝር ያስቀምጣሉ፡፡    ⚡️ነገር ግን የዚህ ፅሁፍ አላማ በግዢ ፈፃሚ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ለኤጀንሲው በሚያቀርቡት አቤቱታ ላይ ተመሰረቶ ኤጀንሲው ተቋራጮችን ከተጫራቾች ወይም ከአቅራቢዎች ዝርዝር ሊያግድ ስለሚችልበት ሁኔታዎች ለመወያየት ስለሆነ ተጫራቾች ስለሚያቀርቡት አቤቱታ እና ስለአፈታት ስርዓቱ በሌላ ፅሁፍ እመለስበታለው፡፡ ⚡️የግዢ ፈፃሚ የመንግስት መስሪያ ቤት በተጫራቾች ወይም በአቅራቢዎች ሕገ-ወጥ ተግባር ወይም ሕጋዊ ጥቅሜን የሚነካ ተግባር ተፈፅሞብኛል ብሎ ሲያምን በአዋጁ አነቀፅ 12 መሰረት ለተቋቋመው የመንግስት ግዢና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ አቤቱታውን ማቅረብ እንደሚችል አንቀፅ 76(1) እንዲሁም የመመሪያው አንቀፅ 48(1) ይደነግጋሉ፡፡ አንቀፅ 15(7) በዕጩ ተወዳዳሪዎችና በአውራቢዎች ላይ የመ/ቤቶች የሚያቀርቡትን አቤቱታዎች መርምሮ ውሳኔ መስጠት የኤጀንሲው አንዱ ተግባር መሆኑን ይገልፃል፡፡ ⚡️በዚህም መሰረት ኢጀንሲው አቤቱታ ሲቀርብለት አቤቱታ ለቀረበበት ወይም ለተከሳሽ ዕጩ ተወዳዳሪ ወይም አቅራቢ አቤቱታ መቅረቡንና የአቤቱታዉን ይዘት የሚገልፅ ማስጠንቀቂያ በመላክ ያሳውቃል፡፡ ይህም የተከሳሽ በአስተዳደር ዉሳኔ አሰጣጥ ላይ የመሰማት መብቱን እነዲጠበቅ ይረዳል፡፡ ⚡️ይህ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ የደረሰው ‹ተከሳሽም› በ5 የስራቀናት ውስጥ የፅሁፍ መልሱንና የሰነድ ማስረጃዎችን ለኤጀንሲው ማስገባት እንዳለበት ከመመሪያው አንቀፅ 48.3 ንባብ መረዳት ይቻላል፡፡ ⚡️ኤጀንሲውም አቤቱታውን በተቀበለ በ15 የስራ ቀናት ውስጥ መርምሮ ውሳኔ በመስጠት ለተከራካሪዎቹ በፅሁፍ ማሳወቅ እንዳለበት የአዋጁ አንቀፅ 76(4) ከመመሪያው አንቀፅ 48.4 ጋር ይገልፃሉ፡፡ ለአቤቱታውም ሊሰጡ የሚችሉት ዉሳኔዎች አቤቱታውን ውድቅ ማድረግ፤ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ መስጠት፤ ወይም ዕጩ ተወዳዳሪውን ወይም አቅራቢውን በመንግስት ግዢ ላይ እንዳይሳተፍ ለተወሰነ ወይም ላልተወሰነ ጊዜ ከተወዳዳሪነት ወይም ከአቅራቢነት ማገድ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ⚡️ስለዚህ ተቋራጮች በቀረበባቸው አቤቱተታ ጥፋተኛ ሆነው ከተገኙ ለተወሰነ ወይም ላልተወሰነ ጊዜ በማንኛውም የመንግስት ጨረታ ላይ እንዳይወዳደሩ ሊታገዱ ይችላሉ ማለት ነው፡፡ ተጫራቾች ከማንኛውም የጨረታ ውድድር ሲታገዱ በተለምዶ በጥቁር መዝገብ ወይም “Black List” ውስጥ ገቡ ይባላል፡፡ ⚡️ዋናው ነገር ደግሞ ምን ምን ዓይነት ጥፋቶች ናቸው ተጫራቾችን በጥቁር መዝገብ እንዲገቡ የሚያደርጓቸው? የሚለው ነው፡፡ እነዚህም ነጥቦች በመመሪያው አንቀፅ 48.5.1 እና 48.5.2 ላይ በዝርዝር ተቀምተጠዋል፡፡ ⚡️በአንቀፅ 48.5.1 እንደተዘረዘሩትም የጨረታ ግምገማውን ውጤት ለማበላሸት ወይም ለመለወጥ አስበው  ለግዢ ሰራተኞች ሙስና መስጠት፤ የውሸት ወይም ተቀባይነት የሌላቸውን መረጃዎች በማቅረብ ማጭበርበር፤ የኤጀንሲው እግድ እያለባቸው በግዢ ላይ መሳተፍ/መወዳደር እንዲሁም ተጫራቾች ወይም አቀራቢዎች በዉሉ ከተገለፀው ጥራት የወረደ ዕቃ፤ ስራ፤ ወይም አገልግሎት በማጭበርበር ወይም ከገዢ ሰራተኞች/ባለስልጣናት ጋር በመመሳጠር ያቀረቡ እንደሆነ ኤጀነሲው ከሁለት ዓመት ጀምሮ እስካልተወሰነ ጊዜ ድረስ በማንኛውም የመንግስት ግዢ ላይ እንዳይሳተፉ ሊያግዳቸው ይችላል፡: ከእነዚህም ምክንያቶች በተጨማሪ ተጫራቾች ፍትሃዊ የዋጋ ወድድር ጥቅምን ለማሳጣት ከተወሰኑ ተጫራቾች ጋር በመመሳጠር የዋጋ ተመን ካወጡ/ከጣሉ፤ የግዢ ባለሙያዎች ወይም የግዢ ፈፃሚ መንግስት መ/ቤት ሰራተኞች ላይ የአካል ጉዳት ለማድረስ የዛተ/ያስፈራራ ወይም ጉዳት ያደረሰ እንደሆነ ወይም በኤጀነሲው  የተጣለበት እግድ ከተነሳበት ቀን ጀምሮ በሁለት ዓመታት ዉስጥ ሌላ ማንኛውም ከአቅራቢዎች ዝርዝር ሊያሳግድ የሚችል ጥፋት የፈፀመ እንደሆነ በተመሳሳይ ከሁለት ዓመት ጀምሮ እስካልተወሰነ ጊዜ ድረስ ሊታገድ ይችላል ማለት ነው፡፡ በአጭሩ ሙስና፣ ማጭበርበር፣ መመሳጠር፣ ወይም ዕግድን ጥሶ በጨረታ ላይ መወዳደር ተጫራቾችን/አቅራቢዎችን ከአቅራቢነት ዝርዝር ሊያሳግዳቸው ይችላል ማለት ነው፡፡ በሌላ በኩለ ደግሞ አንቀፅ 48.5.2 ላይ እንደተገለፁት ከመንግስት ጋር የግዢ ውል የተዋዋለው አቅራቢ በዉሉ የተገለፁትን ዕቃዎች፡ ስራዎች ወይም አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ ባለማቅረቡ ምክንያት የግዢ ፈፃሚው መ/ቤት ቀጥተኛ ወይም ተዘዋዋሪ ጉዳት [Direct or Consequential Loss] ያጋጠመው እንደሆነ ወይም የመ/ቤቱን ስራ ያጓተተ ወይም ያፋለሰ እንደሆነ አቅራቢው ከአቀራቢዎች መዝገብ ላይ ከስድስት ወር እስከ ሁለት ዓመት ድረስ ሊታገድ ይችላል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የጨረታ ውድድር እንዳሸነፈ በመ/ቤቱ የተገለፀለት አቅራቢ ውሉን ለመዋዋል ባለመቻሉ ወይም እምቢተኛ በመሆኑ ምክንያት መ/ቤቱ በዉሉ የተገለፀውን ዕቃ፣ ስራ ወይም አገልግሎት ከሌላ አቅራቢዎች ለመግዛት ሲል ጉዳት ያጋጠመዉ ወይም ስራዉን ያጓተተ ወይም ያፋለሰ እንደሆነ እነዲሁም የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ የተሰጠው አቀራቢ በሶስት ዓመት ውስጥ ሌላ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ ሊያስጥ የሚችል ጥፋት ፈፅሞ ከተገኘ ኤጀንሲው አቅራቢውን ከአቀራቢዎች መዝገብ ላይ ከስድስት ወር እስከ ሁለት ዓመት ድረስ ሊያግደው ይችላል፡፡ ⚡️ከአቀራቢዎች ዝርዝር መዝገብ ላይ ለተወሰነ ወይም ላልተወሰነ ጊዜ መታገድ ውጤቱም በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ተጫራቹ ወይም አቅራቢው በማንኛውም የመንግስት ግዢ ላይ መወዳደር አይችልም፡፡ እነዚህ በኤጀንሲው የሚጣሉት የዕግድም ይሁን የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ ቅጣቶች ግዢ ፈፃሚውን የመንግስት መ/ቤት በአቅራቢው ወይም በተጫራቹ ምክንያት የደረሰበትን የገንዘብ ኪሳራ ከመጠየቅ አያግደውም፡፡       

+2
Financial_Forecasting_Analysis_and_Modeling__1763279841.pdf9.56 MB

+1
Cost_Reduction_Control_Best_Practices__1762914294.pdf1.09 MB

UPVC ከአልሙኒየም ይልቅ ተመራጭ የሚያደርገው ውበቱ ብቻ ሳይሆን፣ ለረጅም ጊዜ ሳይዝግ፣ ቀለሙ ሳይለቅ፣ ሳያረጅ መቆየቱ እና በዋጋ ተመጣጣኝ መሆኑም ጭምር ነው! የUPVC ማቴሪያሎችን በመጠቀም በተ
UPVC ከአልሙኒየም ይልቅ ተመራጭ የሚያደርገው ውበቱ ብቻ ሳይሆን፣ ለረጅም ጊዜ ሳይዝግ፣ ቀለሙ ሳይለቅ፣ ሳያረጅ መቆየቱ እና በዋጋ ተመጣጣኝ መሆኑም ጭምር ነው! የUPVC ማቴሪያሎችን በመጠቀም በተለያዩ ዲዛይኖች በሮች፣ መስኮቶችና ፓርቲሽኖችን በተመጣጣኝ ዋጋ አምርተን በራሳችን ባለሙያዎች ያሉበት ቦታ ድረስ መጥተን እንገጥማለን! 📍 Location: ጋዜቦ አደባባይ፣ ሙልሙል ዳቦ ቤት አጠገብ 📞 Call us: 0930099146,0930099145 When Strength meets elegance delina upvc doors"👍

ለምን አስፈለገ? 1. ለጨረታ አዘጋጅ (Client/Owner):   - ሁሉንም ጨረታዎች በደንብ ለመመርመር፣     - ውድድርን ለማካሄድ፣ - እና ለማሸነፍ የታሰበውን ጨረታ አለመቀየሩን ለማረጋገጥ ያስፈልጋል። 2. ለጨረታ ሰጭ (Bidder): በዚህ ጊዜ ውስጥ የጨረታውን ውድድር ሳይለወጥ እንዲጠብቅ ቃል ይገባል። ዋጋውን ሊቀይር አይችልም። መደበኛው ጊዜ ምን ያህል ነው? - በኢትዮጵያ ውስጥ ለኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች፣ የጨረታ ፀንቶ የሚቆይበት ጊዜ በፕሮጀክቱ መጠን እና ውስብስብነት ላይ የተመሰረተ ነው። - በአብዛኛው ከ 90 (ዘጠና ) ቀናት እስከ 120 (መቶ ሃያ) ቀናት ድረስ ይወሰናል። - ለትላልቅ ፕሮጀክቶች (megaprojects) እስከ 180 (መቶ ሰማንያ) ቀናት ሊበልጥ ይችላል።
አስፈላጊነቱ :-
- ጨረታ ሰጩ ይህን ጊዜ ካላከበረ(ለምሳሌ ዋጋውን ቢቀይር ወይም ጨረታውን ቢሰብር)፣ የጨረታ ዋስትና (Bid Bond) ይወሰዳል። ይህ ለኩባንያው ትልቅ የገንዘብ ኪሳራ ሊያስከትል ይችላል። ትርጉም / Explanation of Key Terms - ጨረታ ፀንቶ የሚቆይበት ቀን / Bid Validity Period: ጨረታው "ሕያው" እና ተቀባይነት ያለው የሚቆይበት ጊዜ። - ጨረታ ሰጭ / Bidder: ፕሮጀክቱን ለማከናወን የሚጨርቅ ኩባንያ። - ጨረታ አዘጋጅ / Client/Owner/Employer: ፕሮጀክቱን የሚፈጽም (ለምሳሌ፡ መንግሥት፣ የግል ባለቤት)። - የጨረታ ዋስትና / Bid Bond / Bid Security: ጨረታ ሰጩ የጨረታውን ቃል እንደሚጠብቅ የሚያረጋግጥ የገንዘብ ዋስትና (ብዙም ሆኖ የባንክ ጋራንቲ)። ቃሉን ካልጠበቀ ይወሰዳል። - የጨረታ መግለጫ ቀን / Bid Opening Date: የተለማመዱት ጨረታዎች በህዝብ ፊት የሚከፈትበት ቀን፣ ከዚህ ቀን ጀምሮ የጨረታ ፀንቶ የሚቆይበት ጊዜ ይቆጠራል።

ለንግዱ ማህበረሰብ እና አዲስ ንግድ ፍቃድ ለማውጣት ለምትፈልጉ ዜጎች ። በቀጣይ የምሰጠው መረጃ ገንዘብ ከፍላችሁ የማታገኙን ስለሆነ በደንብ ከታዩት መልካም ነው። ትላንት አንድ የአ.አ ገቢዎች ቢሮ የታዘብኩት ነገር ቢኖር ከ5እና 6 ያለነሱ ግብር ከፋዮች በአጥር ጥግ እየሆኑ ለብቻ ለብቻ እንባ አውጥተው ሲያለቅሱ ተመልክቼ ምክንያታቸውን ስጠይቅ የመጣብኝ ግብር በፍፁም ልከፍለው አልችልም ቤተሰቤ ሊበተን ነው አንዴት መክፈል እችላለሁ ? እንዴት ንግድ ፍቃድ መመለስ እችላለሁ የሚሉ ድምፆችን አስምተውኛል። በእውነቱ ዜጎች እንደዚህ ሲጨነቁ መመልከት እጅጉን አሳሳቢ ነው። የእኔ ምክር የሂሳብ መዝገብ ለምትይዙ ነጋዴዎች። 1 የባንክ አካወታችሁ ላይ በፍፁም ከሽያጭ ውጭ ምንም ገንዘብ እንዳይገባ መጠንቀቅ አለባችሁ ተሳስቶ እንኳን ሰው ብር ቢልክላችሁ ከባድ ነው ነው የብሩን ምንጭ ትጠያቃላችሁ + ለተገዛው እቃ በሙሉ ከሂሳባችሁ መከፈል አለበት። ለምሳሌ በባንክ አካውንታችሁ 100,000 ብር ቢገባ ገቢዎች 100,000*35% =35,000 ብር ግብር ይጠይቃሉ ። 2 ሽያጫችሁ በትንሹ 21% ትርፍ ሊኖረው ይገባል ። ለምሳሌ አንድን ዕቃ በ100 ገዝታችሁ ከሆነ በትንሹ በ121 ብር መሸጥ ይኖርባችኋል ይህ ሳይሆን ቀርቶ በ100 ብር ገዝታችሁ በ110 ብር ብትሸጡ ገቢዎች 121_110=10*35% 3.5 እያንዳንዱ ሽያጭ ላይ ግብር ይጠይቃል ። 3 ብድር ከሌላ ሰው ስትበደሩ በውልና ማስረጃ መሆን አለበት አንድ ሰው በሰፈር ውል 1ሚሊዮን ብር ቢበደር መንግስት 1,000,000*35%=350,000 ብር ግብር ይጠይቃል ። 4 ዓመታዊ ጠቅላላ ሽያጭ ላይ የሚጣለው ትንሹ ግብር 2.5% መሆኑን አውቃችሁ እራሳችሁን ማዘጋጀት ይኖርባችኋል በኢትዮጵያ ንግድ ህግ መክሰር ያስቀጣል ። ለምሳሌ ድርጅታችሁ አመታዊ ሽያጭ 2ሚሊዮን ሆኖ 100,000 ብር ቢከስር 2,000,000*2.5%=50,000 ብር ግብር ትከፍላለችሁ። 5 ለንግዱ ከአወጣችሁት አስተዳደር ወጪዎች ውስጥ ኦዲተሮች 35% ውድቅ ማድረግ ይችላሉ ። ለምሳሌ በአመት ውስጥ ለንግዱ የወጣው ወጪ 100,000 ቢሆን ምንም እንኳን ደረሰኝ ቢኖረውም 35,000 ብሩን ውድቅ በማድረግ 35,000*35%=12,500 ተጨማሪ ግብር መጠየቅ ይችላል ። 6 ከሰው የተበደራችሁት ብድር ቢኖር ለአበዳሪው ግለሰብ ስትከፍሉ በስሙ በባንክ መክፈል ይኖርባችኋል ። ምሳሌ አንድ ነጋዴ ከቤተሰቡ ወይም ከወዳጆቹ 1ሚሊዮን ተበድሮ ከሆነ እና በዓመቱ 600,000 ቢከፍል 600,000 በባንክ መሆን አለበት ከአልሆነ ግን በተለያየ ጊዜ በካሽ ቢከፍል ውድቅ ተደርጎ በ600,000*35%=210,000 ብር ግብር ይከፍላል ። 6 አንድ ነጋዴ ከራሱ ሂሳብ ገንዘብ በዓመቱ ማውጣት የሚችለው የትርፉን መጠን ብቻ ነው። ምሳሌ አንድ ነጋዴ በዚህ ዓመት የተጣራ ተርፍ 400,000 ቢኖራው እና በሂሳቡ ላይ ከሽያጭ የተገኘ ገንዘብ 1,000,000 ቢኖረው አስቻኳይ ነገር ቢያጋጥመው 400,000 ብር ብቻ ማውጣት ይችላል 500,000 ብር ቢያወጣ 500,000_400,000=100,000*35%=35,000 ግብር ይከፍላል ። 7 outstanding inventory =( beginning + total purchase ) _ total sales ከአልሆነ እያንዳንዱን inventory ዝርዝር ማቅረብ ግዴታችሁ ነው። 8 አንዳዴ አልፎ አልፎ Lifo Fifo Average የሚባሉትም ልትጠየቁ ትችላላችሁ ነገር ግን አብዛኞቹ የኢትዮጵያ ነጋዴዎች Average ስለሚጠቀሙ እረኛው ብዙ አሳሳቢ አይደለም። Via Eliana Firew እንዴት ነው የምንዛለቀው 🤔🤔🤔🤔

የጨረታ ማስታወቂያ ፡- ለመንገድ ግንባታና ጥገና ስራ የሚያገለግሉ ገልባጭ መኪኖች ኪራይ
የጨረታ ማስታወቂያ ፡- ለመንገድ ግንባታና ጥገና ስራ የሚያገለግሉ ገልባጭ መኪኖች ኪራይ