uz
Feedback
Ethiopian Trading Businesses Corporation (ETBC)

Ethiopian Trading Businesses Corporation (ETBC)

Kanalga Telegram’da o‘tish

Ko'proq ko'rsatish
1 614
Obunachilar
+124 soatlar
-37 kunlar
-230 kunlar
Postlar arxiv
የኮርፖሬሽኑ አመራርና ሰራተኞች በ7ኛው ሃገራዊ ምርጫ አፈጻጸም ዙሪያ ተወያዩ የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎቸ ኮርፖሬሽን አመራርና ሰራተኞች በ7ኛው ሃገራዊ ምርጫ አፈጻጸም ዙሪያ የውይይት መድረክ በኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤት ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም አካሄዱ፡፡ የውይይቱ ዋና ዓላማ የድህረ ምርጫ ሥራዎችን በውጤታማነት በመፈጸም የተጀመረውን ጠንካራ መንግስት የመመስረት ግብ በተሟላ ሁኔታ ለማሳካት ያለመ መሆኑ ተገልጿል፡፡ የውይይት መድረኩን ያስጀመሩት የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በኃይሉ ንጉሴ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በስኬት በመጠናቀቁ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን በምርጫው ከምንም በላይ ሀገርና ህዝብ አሸንፈዋል ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡ አያይዘውም ከምርጫው መጠናቀቅ በኃላ የሚጠበቁ ሥራዎች መኖራቸውን ጠቁመው በተገቢው ሁኔታ የህዝብ ፍላጎትና ጥያቄዎችን ለመመለስ በቁርጠኝነት መስራት ይገባል ብለዋል፡፡ ‹‹ከምርጫ ድል ማግስት፣ ጠንካራ መንግስት›› በሚል ርዕስ ለውይይት የተዘጋጀውን ሰነድ የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ዘርፍ ም/ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት ሙሉቀን ዱባለ በዝርዝር ያቀረቡ ሲሆን በሰነዱ የ7ኛው ሃገራዊ ምርጫ አፈጻጸምና የመንግስት የድህረ ምርጫ ሥራዎች የሚሉት በዋንኛነት ከተካተቱት ርዕሰ ጉዳዮች ውስጥ ይገኙበታል፡፡ የቀረበውን ሰነድ መነሻ በማድረግ በቅድመ ምርጫ ስለነበረው ዝግጅትና ሂደት፣ በምርጫ ወቅት በታዩ ጉዳዮችና በቀጣይ በትኩረት ሊሰሩ በሚገቡ ጉዳዮች ላይ ውይይት ተደርጓል፡፡ የተለያዩ ጥያቀዎችና አስተያየቶች ቀርበው ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ በተለይም በ7ኛው ሃገራዊ ምርጫ በርካታ ህዝብ በነቂስ ወጥቶ ረዥም ሰዓታት ጠብቆ በሰላማዊ ሁኔታ መምረጥ መቻሉ እያደገ ላለው የዲሞክራሲ ልምምድ አንዱ ማሳያ ተደርጎ እንደሚወሰድ የተመላከተ ሲሆን በምርጫው የታየው ውጤታማነትን መንግስት በሚወስዳቸው ተግባራዊ እርምጃዎች የህዝብ ጥያቄዎችን በመመለስ ማሳየት እንዳለበት ተገልጿል፡፡ እንደ መንግስት የልማት ተቋም የመንግስትን ሃብት መጠበቅና በአግባቡ ማስተዳደር እንደሚገባ እንዲሁም ለህብረተሰቡ የሚቀርቡ የፍጆታ ምርቶችን በብዛትና በዓይነት ተደራሽ ለማድረግ ሁሉም አመራርና ሰራተኛ በቁርጠኝነት መሥራት እንዳለበት ተሰምሮበታል፡፡

የኮርፖሬሽኑ አመራርና ሰራተኞች በ7ኛው ሃገራዊ ምርጫ አፈጻጸም ዙሪያ ውይይት አደረጉ የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን አመራርና ሰራተኞች በ7ኛው ሃገራዊ ምርጫ አፈጻጸም ዙሪያ በኮርፖሬሽኑ ዋና
+7
የኮርፖሬሽኑ አመራርና ሰራተኞች በ7ኛው ሃገራዊ ምርጫ አፈጻጸም ዙሪያ ውይይት አደረጉ የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን አመራርና ሰራተኞች በ7ኛው ሃገራዊ ምርጫ አፈጻጸም ዙሪያ በኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤት ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ውይይት አካሄዱ፡፡ የውይይቱ ዋና ዓላማ የድህረ ምርጫ ሥራዎችን በውጤታማነት በመፈጸም የተጀመረውን ጠንካራ መንግስት የመመስረት ግብ በተሟላ ሁኔታ ለማሳካት ያለመ መሆኑ ተገልጿል፡፡ የውይይት መድረኩን ያስጀመሩት የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በኃይሉ ንጉሴ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በስኬት በመጠናቀቁ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን በምርጫው ከምንም በላይ ሀገርና ህዝብ አሸንፈዋል ብለዋል፡፡ አያይዘውም ከምርጫው መጠናቀቅ በኃላ የሚጠበቁ ሥራዎች መኖራቸውን ጠቁመው በተገቢው ሁኔታ የህዝብ ፍላጎትንና ጥያቄዎችን ለመመለስ በቁርጠኝነት መስራት ይገባል ብለዋል፡፡ ‹‹ከምርጫ ድል ማግስት፣ ጠንካራ መንግስት›› በሚል ርዕስ ለውይይት የተዘጋጀውን ሰነድ የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ዘርፍ ም/ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት ሙሉቀን ዱባለ በዝርዝር ያቀረቡ ሲሆን በሰነዱ የ7ኛው ሃገራዊ ምርጫ አፈጻጸምና የመንግስት የድህረ ምርጫ ሥራዎች የሚሉት በዋንኛነት ከተካተቱት ርዕሰ ጉዳዮች ውስጥ ይገኙበታል፡፡ የቀረበውን ሰነድ መነሻ በማድረግ በቅድመ ምርጫ ስለነበረው ዝግጅትና ሂደት፣ በምርጫ ወቅት በታዩ ጉዳዮችና በቀጣይ በትኩረት ሊሰሩ በሚገቡ ጉዳዮች ላይ ውይይት ተደርጓል፡፡ የተለያዩ ጥያቀዎችና አስተያየቶች ቀርበው ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ በተለይም በ7ኛው ሃገራዊ ምርጫ በርካታ ህዝብ በነቂስ ወጥቶ ረጅም ሰዓታት ጠብቆ በሰላማዊ ሁኔታ መምረጥ መቻሉ እያደገ ላለው የዲሞክራሲ ልምምድ አንዱ ማሳያ ተደርጎ እንደሚወሰድ የተመላከተ ሲሆን በምርጫው የታየው ውጤታማነት መን

የጤፍ ሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ.jpg7.82 KB

በኮርፖሬሽኑ የ2018 በጀት ዓመት አስራ አንድ ወራት የእቅድ አፈጻጸም እና የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ እቅድ ላይ ውይይት ተደረገ፤ በኮርፖሬሽኑ የ2018 በጀት ዓመት የአስራ አንድ ወራት የእቅድ አ
+8
በኮርፖሬሽኑ የ2018 በጀት ዓመት አስራ አንድ ወራት የእቅድ አፈጻጸም እና የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ እቅድ ላይ ውይይት ተደረገ፤ በኮርፖሬሽኑ የ2018 በጀት ዓመት የአስራ አንድ ወራት የእቅድ አፈጻጸም እና የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ እቅድ ላይ የኮርፖሬሽኑ የበላይ አመራሮች፣ የዘርፍ አማካሪዎች፣ ዳይሬክተሮችና የዋና ክፍል ኃላፊዎች በተገኙበት ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ውይይት ተካሄደ። መድረኩን የከፈቱት የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በኃይሉ ንጉሴ በበጀት ዓመቱ ያለፉት አስራ አንድ ወራት እቅድ ክንውንን በመገምገም የተሰሩና ያልተሰሩ ሥራዎችን ለመለየትና ለቀጣይ በጀት ዓመት ግብዓት ለመውሰድ መድረኩ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። በመድረኩ በየዘርፉ የነበረው የአስራ አንድ ወራት እቅድ አፈጻጸም በዝርዝር የቀረበ ሲሆን በእቅድ አፈጻጸም ወቅት የነበሩ ተግዳሮቶችና እንዚህን ተግዳሮቶች ለመቅረፍ በቀጣይ ትኩረት ተደርጎ ሊሰራባቸው በሚገቡ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል፡፡ በመድረኩ የኮርፖሬሽኑን ስትራቴጂያዊ እቅድና የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምን መነሻ በማድረግ የተዘጋጀ የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ እቅድ በየዘርፉ የቀረበ ሲሆን በዕቅዱ ውስጥ የተያዙት ግቦች ሊተገበሩ የሚችሉና ኮርፖሬሽኑን አንድ እርምጃ ወደፊት የሚያራምዱ መሆን እንዳለባቸው በማመላከት ሁሉም አመራርና ሰራተኛ ተቋሙን በሚመጥነው ደረጃ ላይ ለማስቀመጥ በቁጭት ሊሰራ እንደሚገባ ተሰምሮበታል፡፡ በመጨረሻም ዋና ስራ አስፈጻሚው በ2019 በጀት ዓመት ልዩ ትኩረት ተሰጥቷቸው ሊሰሩ በሚገባቸው ዋና ዋና ተግባራት (Grand Initiatives) ላይ አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡

የኮርፖሬሽኑን የፋይናንስ አፈጻጸምና አሰራር ለመገምገምና አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ መድረክ ተካሄደ የኮርፖሬሽኑን የፋይናንስ አፈጻጸምና አሰራር ለመገምገምና ቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ መድረክ በኮ
+5
የኮርፖሬሽኑን የፋይናንስ አፈጻጸምና አሰራር ለመገምገምና አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ መድረክ ተካሄደ   የኮርፖሬሽኑን የፋይናንስ አፈጻጸምና አሰራር ለመገምገምና ቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ መድረክ በኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤት የኮርፖሬሽኑ ከፍተኛ አመራሮች እና በኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤትና በሁሉም ዘርፎች የሚገኙ የፋይናንስ ባለሙያዎች በተገኙበት ተካሄደ፡፡   ለውይይት መነሻ የሚሆን ሰነድ የኮርፖሬሽኑ ቺፍ ፋይናንስ ኦፊሰር የሆኑት ማቲያስ ፀጋዬ ያቀረቡ ሲሆን ሰነዱ ያነሳው አንኳር ጉዳዮች ላይ እንዲሁም በአጠቃላይ የኮርፖሬሽኑ የፋይናንስ አሰራር ላይ ያሉትን ጠንካራና ደካማ ጎኖች እና መሻሻል የሚያስፈልጋቸውን ጉዳዮች በተመለከተ ሰፊና ጥልቅ ውይይት ተደርጓል፡፡   በውይይቱም መጪውን የኦዲት ስራ በተሟላ ዝግጅት ለመጀመር ሁሉም የስራ ክፍሎች ዝግጁ መሆን እንዳለባቸውና የሂሳብ ስራዎችን ከዚህ ቀደም ከነበረው በተሻለ ፍጥነት፣ ጥራት እና ቅልጥፍና እንዲሰራና ይህንን ግብ ለማሳካትም ሁሉም የፋይናንስ ቡድን አባላት አስፈላጊውን ድጋፍ፣ ትብብርና ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የሂሳብ መዝገቦች በወቅቱ እንዲዘጉና ለኦዲት ስራው ዝግጁ እንዲደረጉ ዋና ስራ አስፈጻሚው አቅጣጫ ሰጥተዋል፡፡

የፌደራል ገቢዎች ከከፍተኛ ግብር ከፋዮች ጋር ባደረገው የታክስ አሰባሰብ ውይይት ላይ ተቋማት ቀደም ሲል ከነበረባቸው ውስብስብ እና ከፍተኛ ችግሮች በመውጣት ከገቢ ቢሮዎች ጋር በቅርበት በመስራትና መልካም ግንኙነትን በማጠናከር የግብር አሰባሰቡን ውጤታማነት የበለጠ ማሳደግ እንደሚቻል እምነት እንደለው ገለፀ። ለዚህም አንዱ ማሳያ የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ነው::