fa
Feedback
Ethiopian Trading Businesses Corporation (ETBC)

Ethiopian Trading Businesses Corporation (ETBC)

رفتن به کانال در Telegram
1 618
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-67 روز
-930 روز
آرشیو پست ها
በኢትዮጵያ የ118 ዓመታት የንግድ ሚኒስቴር ታሪክ የመጀመሪያው የንግድ ፖሊሲ (አዲስ አበባ ፡ ግንቦት 18 ቀን 2018 ዓ.ም) ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ወጥ ብሔራዊ የንግድ ፖሊሲ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ በይፋ አፅድቃለች። ይህ የላቀ ስኬት ሀገሪቱ የንግድ ሚኒስቴር ከተቋቋመበት የ118 ዓመታት ረጅም ታሪኳ ውስጥ ራሱን የቻለና የነፃ ገበያ ሥርዓቱን የሚመራ ወጥ የፖሊሲ ሰነድ ያገኘችበት የመጀመሪያው ታሪካዊ አጋጣሚ ሆኖ ተመዝግቧል። ቀደም ሲል ወጥ የሆነ የንግድ ፖሊሲ አለመኖሩና የንግድ ሕጎች በተለያዩ አዋጆችና መመሪያዎች ውስጥ ተበታትነው መገኘታቸው በገቢና ወጪ ንግድ መካከል ቅንጅት እንዳይኖር ከማድረጉም በላይ፣ በንግድ ሥርዓቱ ላይ ፍትሃዊ ውድድር እንዲጠፋ፣ ሕገ-ወጥነት እንዲስፋፋና ሸማቾች ለከፍተኛ ምሬት እንዲዳረጉ በምክንያትነት ይጠቀሳል። በአሁኑ ወቅት የጸደቀው ፖሊሲ እነዚህን መዋቅራዊ ክፍተቶች በመሙላት የሀገር ውስጥና የውጭ ንግድ አስተዳደርን በሳይንሳዊ መንገድ ለመምራት፣ የወጪ ንግድን በማዘመን ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ፣ የሀገር ውስጥ አምራቾችን በታሪፍና ማበረታቻዎች ለመደገፍ እንዲሁም የሸማቾችን መብትና ደህንነት ለመጠበቅ እጅግ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል። ይህ አዲስ ብሔራዊ የንግድ ፖሊሲ በዋናነት በነፃ ገበያ ኢኮኖሚ፣ በትብብርና ቅንጅት፣ በግልፅነትና ተገማችነት እንዲሁም በፍትሃዊ ውድድር መርሆዎች ላይ የተገነባ ነው። የሰነዱ አጠቃላይ ይዘትም የሀገር ውስጥ የግብይት ሥርዓትን ማዘመን፣ የገቢና ወጪ ንግድ አስተዳደር ማዕቀፍን ማጠናከር፣ ፍትሃዊ ንግድን ማስፈንና የዲጂታል ንግድ (E-commerce) ሥርዓትን መገንባት ላይ ያተኩራል። በአጠቃላይ ፖሊሲው በንግዱ ማኅበረሰብ ላይ ከፍተኛ መተማመንን በመፍጠር፣ የውጭ ኢንቨስትመንትን በመሳብና የሀገሪቱን የንግድ ምህዳር ወደ አዲስ ምዕራፍ በማሸጋገር የሀገሪቱን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ የተጣለ ትልቅ መሠረት ነው። Ethiopian Ministry of Trade and Regional Integration

የኮርፖሬሽኑ ምርቶች በለሚ ሁለገብ ገበያ ማዕከል በለሚ ሁለገብ ገበያ ማዕከል ውስጥ ወደሚገኘው የኮርፖሬሽኑ የምርት መሸጫ መደብር ቁጥር 08 ጎራ ይበሉ፡፡ የተለያዩ የአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም የፍ
+4
የኮርፖሬሽኑ ምርቶች በለሚ ሁለገብ ገበያ ማዕከል በለሚ ሁለገብ ገበያ ማዕከል ውስጥ ወደሚገኘው የኮርፖሬሽኑ የምርት መሸጫ መደብር ቁጥር 08 ጎራ ይበሉ፡፡ የተለያዩ የአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም የፍጆታ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ይሸምታሉ፡፡ ለግብይት ምቹ የሆነ፤ ሰፊ የመኪና ማቆሚያ ቦታ ያለው፡፡ ይምጡ! ይሸምቱ! ሰሚት፣ ከሰሚት ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አጠገብ፡፡

ኮርፖሬሽኑ በለሚ የገበያ ማዕከል ውስጥ ምርቶቹን ለሕብረተሰቡ በማቅረብ ተደራሽነቱን እያሰፋ ይገኛል የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ክብርት አዳነች አቤቤ የለሚ ሁለገብ የገበያ ማዕከልን ግንቦት 13 ቀን
+6
ኮርፖሬሽኑ በለሚ የገበያ ማዕከል ውስጥ ምርቶቹን ለሕብረተሰቡ በማቅረብ ተደራሽነቱን እያሰፋ ይገኛል የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ክብርት አዳነች አቤቤ የለሚ ሁለገብ የገበያ ማዕከልን ግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ.ም ለአገልግሎት ክፍት ባደረጉበት ወቅት ባደረጉት ንግግር በገበያ ማዕከሉ ማህበረሰባችን ለዕለት ፍጆታ የሚጠቀምባቸውን የሰብል ምርቶች፣ አትክልትና ፍራፍሬዎች፣ የበርበሬና የቅመማ ቅመም ምርቶች እና የኢንደስትሪ ምርቶች የአንድ ማዕከል የግብይት ስርዓት እውን አድርገናል ብለዋል። በማዕከሉ የሚቀርቡ ምርቶች ከ15 እስከ 20 በመቶ የዋጋ ቅናሽ የሚሸጥበት ፥ ዋጋ የሚያንረውን ህገ ወጥ የደላላ ሰንሰለት በመበጣጠስ ከአምራቹ ያልተቋረጠ ምርት የሚቀርብበትና የከተማውን ነዋሪዎች የኑሮ ጫናን የሚያቃልልም መሆኑንም አብራርተዋል። ዘመናዊ ማሞቂያና ማቀዝቀዣ ያላቸው 221 መጋዘኖች፣ የችርቻሮ ሱቆች፣ ሱፐር ማርኬቶችና ወፍጮ ቤቶችን ያካተተው ማዕከሉ በአንድ ጊዜ 250 ተሽከርካሪዎችን ማቆም የሚችል ፓርኪንግ እንዳለው ከንቲባዋ ጠቁመዋል፡፡ የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ዛሬ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት በሆነው የለሚ የገበያ ማዕከል ውስጥ አትክልትና ፍራፍሬዎችንና የፍጆታ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ በማቅረብ ላይ ይገኛል። የለሚ ሁለገብ የገበያ ማዕከል ለለሚ ኩራ፣ ለቦሌ እና የካ ክፍለ ከተሞች ነዋሪዎች አማካይ በሆነው ሰሚት ዋና መንገድ ላይ ይገኛል፡፡

Day 2 of #KazanForum2026 marked a significant milestone for Ethiopian Investment Holdings ! 🇪🇹 🇷🇺 Our CEO, Dr. Brook Taye
+2
Day 2 of #KazanForum2026 marked a significant milestone for Ethiopian Investment Holdings ! 🇪🇹 🇷🇺 Our CEO, Dr. Brook Taye, delivered a compelling address at the Russia-Ethiopia roundtable on investment and trade collaboration, underscoring EIH’s pivotal role in creating a secure and thriving investment environment in Ethiopia. What we highlighted: ✓ EIH’s expertise as a co-financer and project structurer ✓ Our market access facilitation through subsidiary companies and offtake agreements ✓ Active engagement with Russian partners on significant ongoing projects ✓ Ethiopia’s impressive economic growth in 2025 ✓ Strategic access to COMESA and AfCFTA markets Why Ethiopia? A premier destination for global investors with exceptional opportunities in manufacturing, agriculture, and emerging sectors. We invite Russian and international partners to explore these transformative opportunities with us. Let’s build prosperity together! 🤝 #EIH #Ethiopia #Investment #Trade #Russia #EconomicGrowth