fa
Feedback
Ethiopian Trading Businesses Corporation (ETBC)

Ethiopian Trading Businesses Corporation (ETBC)

رفتن به کانال در Telegram
1 631
مشترکین
+124 ساعت
+97 روز
+1330 روز
آرشیو پست ها
የሙዝ ምርት ላይ ያተኮረ ሃገራዊ ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል የኢትዮጵያ አበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ አምራች ላኪዎች ማህበር ያዘጋጀውና የሙዝ ወጪ ንግድ ላይ ያተኮረ ሀገር አቀፍ ጉባዔ ‹‹በሙዝ እሴት
+7
የሙዝ ምርት ላይ ያተኮረ ሃገራዊ ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል የኢትዮጵያ አበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ አምራች ላኪዎች ማህበር ያዘጋጀውና የሙዝ ወጪ ንግድ ላይ ያተኮረ ሀገር አቀፍ ጉባዔ ‹‹በሙዝ እሴት ወደ ላቀ ስኬት›› በሚል መሪ ሃሳብ ነሐሴ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በሂልተን ሆቴል እየተካሄደ ይገኛል፡፡ በጉባዔው ጥሪ የተደረገላቸው ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ ሙዝ አምራቾች፣ አርሶአደሮች፣ ኢንቨስተሮች እና ባለድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን የሙዝ ምርት ዓለም አቀፍ የገበያ ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ የጥራት ማሻሻያና የባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ጥረት ወሳኝ መሆኑ ተመልክቷል። ኮርፖሬሽኑም ለገበያ የሚያቀርበውን የሙዝ ምርት ይዞ እየተሳተፈ የሚገኝ ሲሆን በዚህም ጠንካራ የገበያ ትስስር መፍጠር እንደሚቻል ይታመናል፡፡

ኮርፖሬሽኑ በለሚ ሁለገብ የገበያ ማዕከል ውስጥ የከፈተውን ሱፐርማርኬት የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በየጠዋት ገበያ ፕሮግራሙ እንደሚከተለው ቃኝቶታል

“በ2019 በጀት ዓመት የ13.4 ቢሊዮን ዶላር የወጪ ንግድ ገቢ እቅድን ለማሳካት በትኩረት ይሰራል” - ክቡር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ​(አዲስ አበባ​ ፣ ነሐሴ 6 ቀን 2018 ዓ.ም ) የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ክቡር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ከወጪ ምርት ላኪዎች ጋር በ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምና በ2019 ዕቅድ ዙሪያ ሰፊ ውይይት አካሂደዋል። ክቡር ሚኒስትሩ በመክፈቻ ንግግራቸው ወቅት እንደገለጹት፣ የወጪ ንግድ ዘርፉ በበጀት ዓመቱ ሀገራዊ የማክሮ-ኢኮኖሚ መረጋጋትን ለማምጣት ከፍተኛ እምርታ ነው። ለዚህ ውጤት መመዝገብ ላኪዎች ያበረከቱት አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን የጠቀሱት ክቡር ዶ/ር ካሳሁን፣ በቀጣይም የኢትዮጵያን ምርቶች በዓለም አቀፍ ገበያ በጥልቀት ለማስተዋወቅ በቁርጠኝነት እንደሚሠራ ገልጸዋል። በመድረኩ ላይ እንደተገለጸው፣ ኢትዮጵያ በ2018 በጀት ዓመት ከጠቅላላ የወጪ ንግድ ከ11.2 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ ገቢ ማግኘት የቻለች ሲሆን፤ ይህም የዕቅዱን 119.14% ያሳካ የላቀ አፈጻጸም ነዉ። በ2019 በጀት ዓመት የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ይበልጥ ለማሳደግ የ13.4 ቢሊዮን ዶላር የወጪ ንግድ ግብ የተቀመጠ ሲሆን፣ ይህንን ለማሳካትም በሥራ ሂደት የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በጋራ ለመፍታት ስምምነት ላይ ተደርሷል። እቅዱን እዉን ለማድረግም ሚኒስቴር መስሪያቤቱ ላኪዎችን በመደገፍና አመቺ ሁኔታዎችን በመፍጠር በትኩረት እንደሚሰራ ክቡር ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡ በውይይቱ ወቅት ከተሳታፊ ላኪዎች የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የቀረቡ ሲሆን፣ ክቡር ሚኒስትሩ ሰፊ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ክቡር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) መድረኩን ሲያጠቃልሉም ለ2019 በጀት ዓመት ስኬታማነት ሰባት ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎችን ያስቀመጡ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል ​ ምርቶችን በብዛት ከመላክ ባለፈ እሴት በመጨመርና ጥራትን በማረጋገጥ ተወዳዳሪ መሆን፤ ነባር ገበያዎችን ከማጠናከር ጎን ለጎን አዳዲስ ዓለም አቀፍ የገበያ መዳረሻዎችን መፈለግ፤ የወጪ ንግድን በዘመናዊ ዳታና ዲጂታል አሰራር በመደገፍ መምራት የሚሉት ይጠቃሳሉ፡፡ ይህ የውይይት መድረክ በላኪዎችና በመንግሥት መካከል ያለውን የጋራ ግንኙነት ይበልጥ ያጠናከረና ለ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ስኬታማነት ትልቅ መነሳሳትን የፈጠረ መሆኑ ተመልክቷል። የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር https://web.facebook.com/share/p/1DHUvN82DE

“በ2019 በጀት ዓመት የ13.4 ቢሊዮን ዶላር የወጪ ንግድ ገቢ እቅድን ለማሳካት በትኩረት ይሰራል” - ክቡር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ​(አዲስ አበባ​ ፣ ነሐሴ 6 ቀን 2018 ዓ.ም ) የንግድና ቀጣና
+2
“በ2019 በጀት ዓመት የ13.4 ቢሊዮን ዶላር የወጪ ንግድ ገቢ እቅድን ለማሳካት በትኩረት ይሰራል” - ክቡር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ​(አዲስ አበባ​ ፣ ነሐሴ 6 ቀን 2018 ዓ.ም ) የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ክቡር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ከወጪ ምርት ላኪዎች ጋር በ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምና በ2019 ዕቅድ ዙሪያ ሰፊ ውይይት አካሂደዋል። ክቡር ሚኒስትሩ በመክፈቻ ንግግራቸው ወቅት እንደገለጹት፣ የወጪ ንግድ ዘርፉ በበጀት ዓመቱ ሀገራዊ የማክሮ-ኢኮኖሚ መረጋጋትን ለማምጣት ከፍተኛ እምርታ ነው። ለዚህ ውጤት መመዝገብ ላኪዎች ያበረከቱት አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን የጠቀሱት ክቡር ዶ/ር ካሳሁን፣ በቀጣይም የኢትዮጵያን ምርቶች በዓለም አቀፍ ገበያ በጥልቀት ለማስተዋወቅ በቁርጠኝነት እንደሚሠራ ገልጸዋል። በመድረኩ ላይ እንደተገለጸው፣ ኢትዮጵያ በ2018 በጀት ዓመት ከጠቅላላ የወጪ ንግድ ከ11.2 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ ገቢ ማግኘት የቻለች ሲሆን፤ ይህም የዕቅዱን 119.14% ያሳካ የላቀ አፈጻጸም ነዉ። በ2019 በጀት ዓመት የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ይበልጥ ለማሳደግ የ13.4 ቢሊዮን ዶላር የወጪ ንግድ ግብ የተቀመጠ ሲሆን፣ ይህንን ለማሳካትም በሥራ ሂደት የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በጋራ ለመፍታት ስምምነት ላይ ተደርሷል። እቅዱን እዉን ለማድረግም ሚኒስቴር መስሪያቤቱ ላኪዎችን በመደገፍና አመቺ ሁኔታዎችን በመፍጠር በትኩረት እንደሚሰራ ክቡር ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡ በውይይቱ ወቅት ከተሳታፊ ላኪዎች የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የቀረቡ ሲሆን፣ ክቡር ሚኒስትሩ ሰፊ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ክቡር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) መድረኩን ሲያጠቃልሉም ለ2019 በጀት ዓመት ስኬታማነት ሰባት ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎችን ያስቀመጡ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል ​ ምርቶችን በብዛት

ኮርፖሬሽኑ የምስጋና የምስክር ወረቀት ተበረከተለት የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ባለፈው በጀት ዓመት የክረምት በጎ ሥራዎች ላይ ተሰማርተው ለከተማው አቅመ ደካማ ነዋሪዎች ከፍተኛ ድጋፍ ላደረጉ ተቋማት
ኮርፖሬሽኑ የምስጋና የምስክር ወረቀት ተበረከተለት የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ባለፈው በጀት ዓመት የክረምት በጎ ሥራዎች ላይ ተሰማርተው ለከተማው አቅመ ደካማ ነዋሪዎች ከፍተኛ ድጋፍ ላደረጉ ተቋማት ባዘጋጀው የምስጋና እና እውቅና መርሀ ግብር ላይ የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽንን የእውቅና የምስክር ወረቀት በመስጠት አመስግኗል፡፡ ኮርፖሬሽኑ ከመደበኛ ስራው ጎን ለጎን ማህበራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ የሚገኝ ሲሆን በቀጣይም ይህን አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል::

ኮርፖሬሽኑ ሰሚት በሚገኘው ለሚ የገበያ ማዕከል ውስጥ የከፈተው ሱፐር ማርኬት በቻናል 1 የቴሌቪዥን ጣቢያ ሲቃኝ ይምጡ! ይጎብኙ! ይሸምቱ!

የኮርፖሬሽኑ አመራርና ሰራተኞች የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር አካሄዱ እንደ ሀገር 800 ሚሊየን ችግኞች የሚተከሉበት የዘንድሮው የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ከዛሬ ማለዳ
+7
የኮርፖሬሽኑ አመራርና ሰራተኞች የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር አካሄዱ እንደ ሀገር 800 ሚሊየን ችግኞች የሚተከሉበት የዘንድሮው የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ከዛሬ ማለዳ ጀምሮ በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን አመራርና ሰራተኞችም በዚህ ታሪካዊ ቀን የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ቃሊቲ በሚገኘው በኮርፖሬሽኑ የቡና ማደራጃና ማዘጋጃ ማዕከል አካሂደዋል፡፡ የችግኝ ተከላውን መርሃ-ግብር ያስጀመሩት የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በኃይሉ ንጉሴ እንኳን ለዚህ በአንድ ጀንበር 800 ሚሊየን ችግኞች ለሚተከሉበት ታሪካዊ ቀን አደረሳችሁ በማለት እንደ ሃገር ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ ኢኒሺዬቲቭ አረንጓዴ ኢኮኖሚን ለማሳካት ከፍተኛ ጥረት መደረጉን ገልጸዋል፡፡ አያይዘውም እንደ ኮርፖሬሽን ባለፉት ዓመታት የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ሲካሄድ መቆየቱን በመጥቀስ በዛሬው ቀንም በኮርፖሬሽኑ እና በቅርንጫፍ ማዕከላት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሩ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ አክለውም ችግኝ ከመትከል ባለፈ ዋናው ተግባር መንከባከብና እንዲጸድቁ መከታተል በመሆኑ ልዩ ትኩረት እንዲሰጥ አስገንዝበዋል፡፡ ዛሬ በሃገር አቀፍ ደረጃ ከሚተከሉት 800 ሚሊየን ችግኞች ውስጥ እስከ 60 በመቶ የሚይዘው የማንጎ፣ ፓፓያ፣ አቮካዶና ቡና ችግኝ ነው፡፡ ይህም ኮርፖሬሽኑ ለገበያ የሚያቀርባቸው የግብርና ምርቶችን መጠንና ጥራት በማሳደግ ረገድ የጎላ አዎንታዊ ተጽዕኖ እንደሚኖረውይጠበቃል::