ch
Feedback
Ethiopian Trading Businesses Corporation (ETBC)

Ethiopian Trading Businesses Corporation (ETBC)

前往频道在 Telegram
1 621
订阅者
-124 小时
-17
-130
帖子存档
የጤፍ ሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ.jpg7.82 KB

በኮርፖሬሽኑ የ2018 በጀት ዓመት አስራ አንድ ወራት የእቅድ አፈጻጸም እና የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ እቅድ ላይ ውይይት ተደረገ፤ በኮርፖሬሽኑ የ2018 በጀት ዓመት የአስራ አንድ ወራት የእቅድ አ
+8
በኮርፖሬሽኑ የ2018 በጀት ዓመት አስራ አንድ ወራት የእቅድ አፈጻጸም እና የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ እቅድ ላይ ውይይት ተደረገ፤ በኮርፖሬሽኑ የ2018 በጀት ዓመት የአስራ አንድ ወራት የእቅድ አፈጻጸም እና የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ እቅድ ላይ የኮርፖሬሽኑ የበላይ አመራሮች፣ የዘርፍ አማካሪዎች፣ ዳይሬክተሮችና የዋና ክፍል ኃላፊዎች በተገኙበት ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ውይይት ተካሄደ። መድረኩን የከፈቱት የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በኃይሉ ንጉሴ በበጀት ዓመቱ ያለፉት አስራ አንድ ወራት እቅድ ክንውንን በመገምገም የተሰሩና ያልተሰሩ ሥራዎችን ለመለየትና ለቀጣይ በጀት ዓመት ግብዓት ለመውሰድ መድረኩ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። በመድረኩ በየዘርፉ የነበረው የአስራ አንድ ወራት እቅድ አፈጻጸም በዝርዝር የቀረበ ሲሆን በእቅድ አፈጻጸም ወቅት የነበሩ ተግዳሮቶችና እንዚህን ተግዳሮቶች ለመቅረፍ በቀጣይ ትኩረት ተደርጎ ሊሰራባቸው በሚገቡ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል፡፡ በመድረኩ የኮርፖሬሽኑን ስትራቴጂያዊ እቅድና የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምን መነሻ በማድረግ የተዘጋጀ የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ እቅድ በየዘርፉ የቀረበ ሲሆን በዕቅዱ ውስጥ የተያዙት ግቦች ሊተገበሩ የሚችሉና ኮርፖሬሽኑን አንድ እርምጃ ወደፊት የሚያራምዱ መሆን እንዳለባቸው በማመላከት ሁሉም አመራርና ሰራተኛ ተቋሙን በሚመጥነው ደረጃ ላይ ለማስቀመጥ በቁጭት ሊሰራ እንደሚገባ ተሰምሮበታል፡፡ በመጨረሻም ዋና ስራ አስፈጻሚው በ2019 በጀት ዓመት ልዩ ትኩረት ተሰጥቷቸው ሊሰሩ በሚገባቸው ዋና ዋና ተግባራት (Grand Initiatives) ላይ አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡

የኮርፖሬሽኑን የፋይናንስ አፈጻጸምና አሰራር ለመገምገምና አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ መድረክ ተካሄደ የኮርፖሬሽኑን የፋይናንስ አፈጻጸምና አሰራር ለመገምገምና ቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ መድረክ በኮ
+5
የኮርፖሬሽኑን የፋይናንስ አፈጻጸምና አሰራር ለመገምገምና አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ መድረክ ተካሄደ   የኮርፖሬሽኑን የፋይናንስ አፈጻጸምና አሰራር ለመገምገምና ቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ መድረክ በኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤት የኮርፖሬሽኑ ከፍተኛ አመራሮች እና በኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤትና በሁሉም ዘርፎች የሚገኙ የፋይናንስ ባለሙያዎች በተገኙበት ተካሄደ፡፡   ለውይይት መነሻ የሚሆን ሰነድ የኮርፖሬሽኑ ቺፍ ፋይናንስ ኦፊሰር የሆኑት ማቲያስ ፀጋዬ ያቀረቡ ሲሆን ሰነዱ ያነሳው አንኳር ጉዳዮች ላይ እንዲሁም በአጠቃላይ የኮርፖሬሽኑ የፋይናንስ አሰራር ላይ ያሉትን ጠንካራና ደካማ ጎኖች እና መሻሻል የሚያስፈልጋቸውን ጉዳዮች በተመለከተ ሰፊና ጥልቅ ውይይት ተደርጓል፡፡   በውይይቱም መጪውን የኦዲት ስራ በተሟላ ዝግጅት ለመጀመር ሁሉም የስራ ክፍሎች ዝግጁ መሆን እንዳለባቸውና የሂሳብ ስራዎችን ከዚህ ቀደም ከነበረው በተሻለ ፍጥነት፣ ጥራት እና ቅልጥፍና እንዲሰራና ይህንን ግብ ለማሳካትም ሁሉም የፋይናንስ ቡድን አባላት አስፈላጊውን ድጋፍ፣ ትብብርና ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የሂሳብ መዝገቦች በወቅቱ እንዲዘጉና ለኦዲት ስራው ዝግጁ እንዲደረጉ ዋና ስራ አስፈጻሚው አቅጣጫ ሰጥተዋል፡፡

የፌደራል ገቢዎች ከከፍተኛ ግብር ከፋዮች ጋር ባደረገው የታክስ አሰባሰብ ውይይት ላይ ተቋማት ቀደም ሲል ከነበረባቸው ውስብስብ እና ከፍተኛ ችግሮች በመውጣት ከገቢ ቢሮዎች ጋር በቅርበት በመስራትና መልካም ግንኙነትን በማጠናከር የግብር አሰባሰቡን ውጤታማነት የበለጠ ማሳደግ እንደሚቻል እምነት እንደለው ገለፀ። ለዚህም አንዱ ማሳያ የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ነው::

በኮሚሽኑ በየአስራ አምስት ቀን የሚዘጋጀው የግንቦት ወር 2ኛ ዙር ዲጂታል ፀረ-ሙስና ጋዜጣ *** ዲጂታል ጋዜጣውን ለማግኘት ከታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ 👇 https://heyzine.com/flip-book/0fcd16fbb0.html ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር! የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾 #NCRS ሞባይል መተግበሪያ #ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች https://play.google.com/store/apps/details... #ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231 ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/ ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/ ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149 ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን።