uz
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Kanalga Telegram’da o‘tish

Ko'proq ko'rsatish
1 756
Obunachilar
+124 soatlar
+37 kunlar
+1830 kunlar
Postlar arxiv
🇪🇹የአቅድ ካስኬዲንግ 🇪🇹 ================= ✍️ በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2014 ዓ.ም መሪ እቅድ አዘጋጅቶ ለሂደቶችና ክፍሎች ማውረዱ ይታወሳል የዚህም ተግባር ቀጣይ የሆነው ለፈጻሚ የማውረዱ ስራ በአስተዳደር ሰራተኛው በኩል ተጠናቆ ወደ ስራ ተገብቷል፤ ለአሰልጣኝ መምህራን ደግሞ በአዲሱ የቴ/ሙ/ት/ስ ፖሊሲ እና ስትራቴጂ ተቃኝቶ ወደ ፈጻሚ የማውረዱ ስራ ተጀምሯል፤ ✍️ ይህንንም እቅድ በጥናት ላይ ተመስርቶ አዳዲስ አሰራሮችን በመዘርጋት ተፈጻሚ ለማድረግ ስራዎች ተሰርተዋል፤ ✍️ እቅዱን ወደ ፈጻሚ በማውረድ መድረኩ የኮሌጁ አመራሮች የተገኙ ሲሆን እቅዱ ሊያሰራ የሚችል እና ሁሉንም በተመሳሳይ ደረጃ ለመከታተልና ለመደገፍ በሚያስችል ልክ ተዘጋጅቷል ብለዋል። የኢትዮ ጣሊያን ኮምኒኬሽን ታህሳስ 07/2014 ዓ.ም ድሬዳዋ

🇪🇹በወቅታዊ የሀገራችን ጉዳይ ላይ ውይይት ተካሄደ🇪🇹 ==================================== ✍️ በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅን ጨምሮ በድሬዳዋ አስተዳደር ቴክኒክና ሙያ ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ስር የሚገኙ ተጠሪ ተቋማት ሰራተኞች በወቅታዊው የሀገራችን ጉዳይ ላይ ውይይት አደረጉ፤ ✍️ በውይይት መድረኩ ላይ የቢሮው ሀላፊ የተገኙ ሲሆን የመንግስት ዋና ፍላጎት እና አላማ ሰላምና ብልጽግናን ማምጣት ሲሆን ይህንንም ለማረጋገጥ አቅጣጫ መቀመጡን ገልጸዋል፤ ✍️ በሌላ በኩል በመድረኩ ተሳታፊ የነበሩ የቢሮውና ተጠሪ ተቋማት ሰራተኞችም አስተያየትና ሀሳባቸውን ሰጥተዋል በዚህም መንግስት መሰል ውሳኔዎችን እና አካሄዶችን በጥንቃቄ እንዲመለከትና እንዲመራ ስጋታቸውንም በመግለጽ አሳስበዋል። የኢትዮ ጣሊያን ኮምኒኬሽን ታህሳስ 07/2014 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኮሌጁ ኮምንኬሽን የፌስቡክ ገጽ ነው Like&Share በማድረግ ለሌሎች እንዲደርስ እናድርግ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://www.facebook.com/342320409823939/posts/949221202467187/?app=fbl ☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️

🇪🇹በዲስፒሊን እና በቅሬታ አቀራረብ መመሪያዎች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሄደ🇪🇹 ================================ ✍️በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ስራ አመራርን ጨምሮ በየደረጃው የሚገኙ የዲፓርትመንት ተጠሪዎችና አስተባባሪዎች እና የዲሲፕሊን እና ቅሬታ ሰሚ የኮሚቴ አባላት በዲሲፕሊን እና በቅሬታ አቀራረብ መመሪያዎች ላይ ግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በማዘጋጀት ውይይት ማድረግ ተችሏል፤ ✍️ በዚህም የግንዛቤ ማስጨበጫ የውይይት መድረክ ተሳታፊዎች ግልጽ ያልሆኑ ሀሳቦችን በማንሳት ግልጽነት መፍጠር ተችሏል በቀጣይም ለሌሎችም የኮሌጁ ሰራተኞች መሰል የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረኮች ቢዘጋጁ መልካም ይሆናል በሚል አስተያየት ተሰጥቷል፤ ✍️ በማጠቃለያውም የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አመራሮችና የኮሚቴ አባላት መመሪያዎችን በሚገባ ግንዛቤ ወስደው በቀጣይ የሚፈጠሩ እና የሚገጥሙ ጉዳዮችን በተቀመጠው የህግ አግባብ ከቸልተኝነትና አንድን ወገን ለመጥቀም ሆነ ለመጉዳት ከሚደረግ አግባብነት የሌለው አካሄድ በጸዳ እንዲፈጽሙ አቅጣጫ በመስጠት መድረኩን አጠቃለዋል። የኮሌጁ ኮምንኬሽን ክፍል 02/04/2014 ዓ.ም ድሬዳዋ

<<አለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን>> ____________________________ በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለ18ኛ ጊዜ የሚከበረውን የአለም የፀረ-ሙስና ቀን ምክንያት በማድረግ በተቋሙ የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና መከታተያ ክፍል አዘጋጅነት ለተቋሙ ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በማካሄድ ቀኑ ተከብሮ ውሏል። ህዳር 30/03/2014 ዓ.ም ድሬዳዋ

🇪🇹16ኛው የብሔር ብሔረሰቦች ቀን በአል🇪🇹 በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በከተማችን እየተከበረ ያለውን 16ኛውን የብሔር ብሔረሰቦች ቀን ክብረ በአል በሚከበርበት ስፍራ ላይ በኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራን የተሰራ ከእጅ ንክኪ ነፃ የሆነ የእጅ መታጠቢያን እንዲህ ባለ ሁኔታ አገልግሎት ላይ እንዲውል ተደርጓል።

🇪🇹በወቅታዊ የሀገር ጉዳይ ላይ የተደረገ ውይይት🇪🇹 ================================== ✍️በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሰራተኞችን ጨምሮ በድሬዳዋ አስተዳደር ቴክኒክና ሞያ እና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ስር የሚገኙ ተቋማት ሰራተኞች ጋር ዘመቻ ለህብረብሔራዊ አንድነት የትና እንዴት እንዝመት? በሚል ሃሳብ ዙሪያ የውይይት መድረክ ተካሄደ። ✍️በውይይት መድረኩም የቢሮው ሀላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው የተገኙ ሲሆን እየተመዘገበ ያለውን አኩሪ እና አንጸባራቂ ድል በማስመልከት የእንኳን ደስ አላችሁ መልክት በማስተላለፍ በቀጣይም ይህንን ድል አስጠብቆ ለመቀጠል በተለይም ሰራተኛው በልማትና መልካም አስተዳደር ግንባር በቁርጠኝነት ተሰልፎ ሀላፊነቱን እንዲወጣ አሳስበዋል። ህዳር 24/2014 ዓ.ም ድሬዳዋ ኢትዮ ጣሊያን ኮምንኬሽን

🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹 ሪብራንዲንግ 🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹 =============================== ✍️በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሰራተኞችን ጨምሮ በድሬዳዋ አስተዳደር ቴክኒክና ሞያ እና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ስር የሚገኙ ተቋማት ሰራተኞች በሪብራንዲንግ ፅንሰ ሃሳብ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሄደ፤ በመድረኩም ከፐብሊክ ሰርቪስ በመጡ ባለሞያ ሰፊ ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን ተሳታፊዎችም በቂ ግንዛቤ የጨበጡበት ሆኗል። ✍️ ከመድረኩ ጎን ለጎን በህልውና ዘመቻው በጀግንነት ግንባር ለሚገኘው መከላከያ ሰራዊታችን የደም ልገሳ ማድረግ ተችሏል። ህዳር 21/2014 ዓ.ም ድሬዳዋ የኢትዮ ጣሊያን ኮምንኬሽን

🇪🇹ደማችንን ለጀግናው መከላከያ ሰራዊታችን🇪🇹 ✍️በነገው እለት ህዳር 21/2014 ዓ.ም ከሰዓት ከሚኖረን የሪብራንዲንግ የገለጻ መድረክ ጎን ለጎን ለጀግናው መከላከያ ሰራዊታችን የደም ልገሳ ስለምናደርግ ሁሉም የኮሌጁ ማህበረሰብ ተሳታፊ አንዲሆን ጥሪ እናደርጋለን።

🇪🇹 የአልባሳት ድጋፍ በጦርነት ለተፈናቀሉ ወገኖቻችን🇪🇹 ✍️በድሬዳዋ አስተዳደር የቴክኒክና ሞያ እና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ በስሩ የሚገኙ ተቋማትን በመማስተባበር የተለያዩ አልባሳትን በማሰባሰብ በጦርነት ለተፈናቀሉ እና ለችግር ለተጋለጡ ወገኖቻቸን ድጋፍ አድርጓል፤ ✍️ይህንንም ድጋፍ በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅም በግንባር ቀደምነት አጠቃላይ ሰራተኛውን እና ሰልጣኝ ተማሪዎችን በማስተባበር ማሰባሰብ ችሏል፤ ✍️ለዚህም ድጋፍ መሳካት የድርሻችሁን ለተወጣችሁ የኮሌጁ ሰራተኞችና ሰልጣኝ ተማሪዎች የላቀ ምስጋናውን ያቀርባል። ህዳር 17/2014 ዓ.ም ድሬዳዋ