ch
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

前往频道在 Telegram
1 744
订阅者
+224 小时
+37
-130
帖子存档
🇪🇹በወቅታዊ የሀገር ጉዳይ ላይ የተደረገ ውይይት🇪🇹 ================================== ✍️በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሰራተኞችን ጨምሮ በድሬዳዋ አስተዳደር ቴክኒክና ሞያ እና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ስር የሚገኙ ተቋማት ሰራተኞች ጋር ዘመቻ ለህብረብሔራዊ አንድነት የትና እንዴት እንዝመት? በሚል ሃሳብ ዙሪያ የውይይት መድረክ ተካሄደ። ✍️በውይይት መድረኩም የቢሮው ሀላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው የተገኙ ሲሆን እየተመዘገበ ያለውን አኩሪ እና አንጸባራቂ ድል በማስመልከት የእንኳን ደስ አላችሁ መልክት በማስተላለፍ በቀጣይም ይህንን ድል አስጠብቆ ለመቀጠል በተለይም ሰራተኛው በልማትና መልካም አስተዳደር ግንባር በቁርጠኝነት ተሰልፎ ሀላፊነቱን እንዲወጣ አሳስበዋል። ህዳር 24/2014 ዓ.ም ድሬዳዋ ኢትዮ ጣሊያን ኮምንኬሽን

🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹 ሪብራንዲንግ 🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹 =============================== ✍️በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሰራተኞችን ጨምሮ በድሬዳዋ አስተዳደር ቴክኒክና ሞያ እና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ስር የሚገኙ ተቋማት ሰራተኞች በሪብራንዲንግ ፅንሰ ሃሳብ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሄደ፤ በመድረኩም ከፐብሊክ ሰርቪስ በመጡ ባለሞያ ሰፊ ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን ተሳታፊዎችም በቂ ግንዛቤ የጨበጡበት ሆኗል። ✍️ ከመድረኩ ጎን ለጎን በህልውና ዘመቻው በጀግንነት ግንባር ለሚገኘው መከላከያ ሰራዊታችን የደም ልገሳ ማድረግ ተችሏል። ህዳር 21/2014 ዓ.ም ድሬዳዋ የኢትዮ ጣሊያን ኮምንኬሽን

🇪🇹ደማችንን ለጀግናው መከላከያ ሰራዊታችን🇪🇹 ✍️በነገው እለት ህዳር 21/2014 ዓ.ም ከሰዓት ከሚኖረን የሪብራንዲንግ የገለጻ መድረክ ጎን ለጎን ለጀግናው መከላከያ ሰራዊታችን የደም ልገሳ ስለምናደርግ ሁሉም የኮሌጁ ማህበረሰብ ተሳታፊ አንዲሆን ጥሪ እናደርጋለን።

🇪🇹 የአልባሳት ድጋፍ በጦርነት ለተፈናቀሉ ወገኖቻችን🇪🇹 ✍️በድሬዳዋ አስተዳደር የቴክኒክና ሞያ እና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ በስሩ የሚገኙ ተቋማትን በመማስተባበር የተለያዩ አልባሳትን በማሰባሰብ በጦርነት ለተፈናቀሉ እና ለችግር ለተጋለጡ ወገኖቻቸን ድጋፍ አድርጓል፤ ✍️ይህንንም ድጋፍ በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅም በግንባር ቀደምነት አጠቃላይ ሰራተኛውን እና ሰልጣኝ ተማሪዎችን በማስተባበር ማሰባሰብ ችሏል፤ ✍️ለዚህም ድጋፍ መሳካት የድርሻችሁን ለተወጣችሁ የኮሌጁ ሰራተኞችና ሰልጣኝ ተማሪዎች የላቀ ምስጋናውን ያቀርባል። ህዳር 17/2014 ዓ.ም ድሬዳዋ

🇪🇹ስንቅ ለሀገር መከላከያ ሰራዊት🇪🇹 ✍️በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅን ጨምሮ በድሬዳዋ አስተዳደር የቴክኒክና ሞያ እና የኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ ስር የሚገኙ ተቋማት ሰራተኞች በአንድት ለጀግናው የሀገራችን መከላከያ ሰራዊት ስንቅ ማዘጋጀት ተችሏል፤ ✍️በዚህም ስንቅ የማዘጋጀት ተግባር ላይ የቢሮው ሀላፊን ጨምሮ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች ተሳታፊ ሆነዋል፤ ✍️በተጨማሪም የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጁሀር በቦታው በመገኘት ሰራተኞችን አበረታተዋል። ህዳር 15/2014 ዓ.ም ድሬዳዋ

#NOMORE #HaaGahu #በቃ #OnEthiopia #DireDawa #Ethio-Italy #Polytechnic #College 🇪🇹#Management

"ተግባራዊ ጥናትና ምርምር በቴክኖሎጂ ሽግግር" ----‑------------------------------------------------------ ✍️በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አበይት ተልዕኮዎችን በትግበራ ምዕራፍ ውጤታማ በሆነ መልኩ መፈጸም እንዲያስችል የተለያዩ ጥናቶችን በማካሄድ ላይ ይገኛል፤ ከእነዚህም ጥናቶች የቴክኖሎጂ ሽግግር አተገባበርን የተሻለና ውጤታማ ለማድረግ የሚረዳ የዳሰሳ ጥናት ለኮሌጁ የስራ አመራር ቀርቦ በቀጣይ ለሚደረገው ተግባራዊ ጥናትና ምርምር ጠቃሚ የሆኑ ሀሳብና አስተያየት ተሰጥቶበታል። ✍️በተጨማሪም የተመረጡ የቴክኖሎጂ ናሙናዎችን ለመስራት የቀረበ ፕሮፖዛል ላይም መወያየት ተችሏል፤ በተለይም ተረፈ ምርትን ወደ ምርትነት ለመቀየር የሚሰሩ ስራዎች ትኩረት ተሰጥቶባቸው እንዲሰሩና ኮሌጁም መሰል እንቅስቃሴዎችን ከግብአት ማሟላት ጀምሮ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ የኮሌጁ ዲን አስታውቀዋል።

#NOMORE ON ETHIOPIA #MORE FOR ENDF ✍️በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣልያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አሠልጣኝ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች ለጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት ሁለተኛ ዙር ድጋፍ አደረጉ። ✍️በድጋፍ መድረኩም ሁሉም ሰራተኛ ከደሞዝ ባሻገር ስንቅ በማዘጋጀት እንዲሁም ልዩልዩ የአይነት ድጋፎች ለማድረግ ተነሳሽነቱንና ቁርጠኝነቱን አሳይቷል። ✍️በማጠቃለያውም የቀድሞ የሀገር መከላከያ ሠራዊትና አየር ሀይል አባል የነበሩ የመንግስትን ጥሪ ተቀብለው ወደ ግንባር ለመዝመት በዝግጅት ላይ ለሚገኙ የኮሌጁ ሰራተኞች የሞራል ድጋፍ ተደርጎላቸዋል። ህዳር 09/03/2014 ዓ.ም ድሬዳዋ