uz
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Kanalga Telegram’da o‘tish

Ko'proq ko'rsatish
1 743
Obunachilar
+224 soatlar
+37 kunlar
-730 kunlar
Postlar arxiv
የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ  ት/ቤት ተማሪዎች ጉብኝት። …………………………………………………………             በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ቀደም ሲል ከተለያዩ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ጋር በተደረገው ውይይትና በተደረሰው የጋራ መገባባትና በተዘጋጀው ዕቅድ መሰረት በዛሬው እለት የአፈቴሳ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በምህንድስና እና በሂሳብ ማለትም(STEM) ግንዛቤ ለማስጨበጥ በኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ  ጉብኝት አድርገዋል፡፡        በዚህም ተማሪዎቹ በኮሌጁ የተግባር ስልጠና የሚሰጥባችውን ዲፓርትመንቶች የጎበኙ ሲሆን  በዚህም የማኑፋክቸሪግ ትምህርትና ሰልጠና ክፍል እና የአውቶሞቲቭ ትምህርትና ሰልጠና ክፍል  አሰልጣኝ መምህራን ለጉብኝት ለመጡት ተማሪዎቹ የተግባር ስልጠና የሚስጥበትን ክፍሎች(workshops) በማስጎብኘት ስለቴክኒክና ሙያና በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በምህንድስና እና በሂሳብ (STEM) ተማሪዎቹ ግንዛቤ እንዲጨብጡ አድርጓል፡፡     በተጨማሪም ሌሎችም በድሬዳዋ አስተዳደር ስር የሚገኙ የአንደኛ ደረጃና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በተዘጋጀው ዕቅድና በተዘረጋው መርሃግብር መሰረት በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በመገኘት መሰል ጉብኝቶችን የሚያደርጉ ይሆናል፡፡   ድሬዳዋ ህዳር 9/2015 የኢትዮ ጣሊያን ኮምንኬሽን

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ላለፉት አራት ተከታታይ ቀናት ለተቋሙ ማኔጅመንት አባላትና ፑል አመራሮች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና አጠናቀቀ።      በ Public Enterpreneurship and Innovation Ecosystem Building(PEIEB) ላይ በተቋሙ አመራሮች አቶ ታደለ አሰፋ እና አቶ ተሾመ ሸዋዬ ላለፉት ቀናት ሲሰጥ የነበረው ስልጠና በዛሬው እለት ፍፃሜውን ማግኘቱን ተከትሎ ስልጠናውን ወስደው ላጠናቀቁ ተሳታፊዎች የእውቅና ሰርተፊኬናየመፅሀፍ ስጦታ የቴክኒክና ሙያ ትምርትና ስልጠና ኤንጀንሲ ሀላፊ ከሆኑት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ  እጅ ተረክበዋል።       በተጨማሪም የኤጀንሲ ሀላፊዋ በቀጣይ ትኩረት ሊሰጣቸው በሚገቡ ወሳኝ ጉዳዮች ላይ ከተሳታፊዎች ጋር የመከሩና  አቅጣጫዎችን ያስቀመጡ ሲሆን ስልጠናውም በዚህ መልኩ ተጠናቋል። የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን ህዳር 2/2015 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በተቋሙ ለሚገኙ የማኔጅመንት አባላትና የፑል አመራሮች Mind Set ላይ ያተኮረ የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት ጀመረ።           ስልጠናው በንግግር የመክፈቻ ንግግር ያስጀመሩትት በስራና ክህሎት ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ እንደገለፁት ይህን ስልጠና ከሚወስዱ ሰልጣኞች ብዙ እንደሚጠበቅ ገልፀው  ሰልጣኞች ስልጠናውን በጥብቅ ዲሲፒሊን ወስደው በቀጣይ በስራቸው የሚገኙ ሰራተኞችንና ሌሎችንም የማሰልጠን ተግባር ላይ እንዲሳተፉ አፅኖት ሰተው ተነናግረዋል።           በዛሬው እለት የተጀመረው ይህ ስልጠና  በኮሌጁ ዲኖች መሰጠት የጀመረ ሲሆን ስልጠናውም ለቀጣይ ሶስት ቀናት የሚቀጥል ይሆናል። የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን ጥቅምት 29/2015 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር በስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ስር የሚገኘው የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የአይሲቲ ትምህርትና ስልጠና ክፍል ለአስተዳደሩ አልፎም ለአገር አርአያ የሚሆን በዛሬው ዕለት በተዘጋጀ ፕሮግራም የስልጠና ክፍሉ ለአሰልጣኝ መምህራን ኦፊስ የሚገለገልበትን ስፍራ በካይዘን በማደራጀት ጽዱ እና ውብ አድርጎ የኮሌጁ ማኔጅመንትና የአካዳሚክ ኮሚሽን አባላት በተገኙበት አስመርቋል፡፡ በዚህም ፕሮግራም ላይ የትምህርትና ስልጠና ክፍሉ ኃላፊ አቶ አቤል ፋንታሁን ስለተሰራው ስራ ገለጻ ያደረጉ ሲሆን በዋናነት በትምህርትና ስልጠና ክፍሉ በሚገኙ አሰልጠኝ መምህራን መካከል በተፈጠረው መቀባበልና መልካም ተግባቦት ይህ ስራ ተሰርቶ እንዲህ ባለ ሁኔታ እዲጠናቀቅ እንዳደረገውና ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የአሰልጣኝ መምህራኑን እውቀትና ጉልበት እንዲሁም በኮሌጁ የሚገኙ ሌሎች ትምህርት ክፍሎችና በአጠቃላይ የኮሌጁን የውስጥ አቅም በመጠቀም መሰራቱን እና በቀጣይም በዋናነት በዲጂታላይዜሽን አቅጣጫ በኮሌጁ ውስጥ ያለውን ተሞክሮ በማስፋት እንደ አስተዳደር ተጨባጭ ስራዎችን ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በበኩላቸው ኮሌጁ ለሪፎርም ስራዎች ትኩረት ሰጥቶ እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝ አስታውሰው በተለየ መልኩ የትምህርት ክፍሎች የካይዘን ትግበራ ላይ መሆናቸውንና ጥሩ አፈጻጸም እየስመዘገቡ ከሚገኙትም የአይሲቲ ትምህርትና ስልጠና ክፍል ተጠቃሽ መሆኑን አንስተው ይህን አርአያ የሚሆን ስራ ሌሎችም ትምህርትና ስልጠና ክፍሎች እንዲከተሉ በማሳሰብ ኮሌጁ ለውጥን የሚያስቡና የሚሰሩ እጆችን እንደሚያበረታ ተናግረዋል፡፡ የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን ጥቅምት 28/2015 ዓ.ም ድሬዳዋ

በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከድሬዳዋ ደወሌ ምድር ባቡር ድርጅት ጋር በጋራ በመስራት የእውቀትና የቴክኖሎጂ ሽግግር ማደረግ በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረሙ። ከመቶ ሀያ አምስት አመት በላይ እድሜ ያለዉ የድሬዳዋ ደወሌ ምድር ባቡር ድርጅት በውስጡ በርካታ እምቅ እውቀት ያላቸው ባለሙያዎች እንዲሁም ከፍተኛ ማሽነሪ ዎችና ወርክ ሾፖች የያዘ ነው:: ይህን የድርጅቱን አቅም ለመጠቀም እና በካይዘን ትግበራ ዙሪያ ድርጅቱ ያለበትን ክፍተት ለመሙላት የኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በጋራ ለመስራት በማለም ከድርጅቱ ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል:: በፊርማ ስነ ስርአቱ ላይ የኮሌጁ ኃላፊ አቶ ታደለ አሰፋ እንዳሉት ስምምነቱ በድርጅቱ ውስጥ ያለውን የካበተ እውቀት ለመጠቀም እና የእውቀት ሽግግር ለማደረግ ጉልህ ሚና አለው ብለዋል። በተጨማሪም ኮሌጅ በካይዘን ትግበራ ላይ  ያለዉን ተሞክሮ ለድርጅቱ በሚጠቅም መልኩ እንደሚያሰለጥን ገልፀዋል። ግንኙነቱን ለማስጀመር ኤሌክትሪካል ዲፓርትመት መመረጡን የገለጹት አቶ ታደለ በቀጣይ ወደ ሌሎች ዲፓርትመንቶች እንደሚሰፋ አስረድተዋል:: የድሬዳዋ ደወሌ ምድር ባቡር ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ አየለ ወ/ዮሐንስ ተቋሙ ከ1911 ጀምሮ የተገነቡ በርካታ ወርክ ሾፖች እንዳሉት ተናግረዋል። እነዚህን እምቅ አቅሞች ድርጅቱ ለወጣቶች የማስተላለፍ አላማ እንዳለው ተናግረዋል። የተፈረመውን ስምምነት ተግባዊ ለማድረግ በርብርብ እንደሚሰራም አቶ አየለ ገልፀዋል። በኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህርት ህይወት እሸቱ በበኩላቸው ኮሌጁ የካይዘን እቅዶችን በማውጣት ወደ ስራ መግባቱን ገልፀው ድርጅቱም ለኮሌጁ መምህራን እና ተማሪዎች የተግባር እውቀት ከፍተኛ እንገዛ  እንደሚያደርግ ያላቸውን እምነት ተናግረዋል።