uz
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Kanalga Telegram’da o‘tish

Ko'proq ko'rsatish
1 743
Obunachilar
+224 soatlar
+37 kunlar
-130 kunlar
Postlar arxiv
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2015 ዓ.ም የበጀት አመት እቅድ ላይ ከተቋሙ ሰራተኞች ጋር ተወያየ።        በእለቱ በነበረው መድረክ በቅድሚ የስራ ሂደቶች እንዲሁም የዋና ስራ ሂደቶች የ2014 ዓ.ም አፈፃፀም ሪፖርታቸውን ለተቋሙ ሰራተኞች ያቀረቡ ሲሆን በመቀጠልም የሁሉም የስራ ሂደቶች በቅደም ተከተል የ2015 ዓ.ም እቅዶቻቸውን ለመድረኩ አቅርበዋል።       መድረኩ ቀጥሎም የቀረቡት እቅዶች ላይ ከተሳታፊዎች በርከት ያሉ ሀሳብና አስተያየት ተሰቶባቸው ሰፋ ያለ ውይይት የተደረገበት ሲሆን በመጨረሻም የዋና ስራ ሂደቶችና የክፍል ተጠሪዎች ከኮሌጁ ዲን ጋር የ2015 ዓ.ም እቅዳቸውን በፊርማ ርክክብ አድርገዋል። የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን። ጥቅምት 25 2015 ዓ.ም

በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በ02 ቀበሌ የሚገኘውን  የወ/ሮ ይመኙሻል ዳኜ የፈራረሰ ቤት በ1 ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ባማረ መልኩ በአዲስ በመገንባት አስረከበ።        በርክክብ ስነ-ስርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ እንደገለፁት እንደዚህ አይነት በጎ ተግባራት ላይ መሳተፍና ከአቅመ ደካሞች ጎን መቆም በምንም የማይተካ የህሊና እርካታ የሚያስገኝ መሆኑን ገልፀው ይህ የተቸገሩትን የመደገፍ ስራ ጅምር መሆኑንና በቀጣይ ለምንሰራቸው በጎ ተግባራት ጥሩ ተሞክሮ የወሰድንበት ነው ሲሉም አክለዋል። አያይዘውም ኮሌጁ ቤቱን ሰርቶ ከማስረከብ በተጨማሪ የተለያዩ የቤት እቃዎችን(ቁም ሳጥን፣ ቲቪ) ድጋፍ ማድረጉን ገልፀው እዚህ በጎ ስራ ላይ የተሳተፉት የኮሌጁ ሰራተኞችና ተባባሪ አካላትንም አመስግነዋል።       የ02 ቀበሌ ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር አቤል ምስራቅ በበኩላቸው ስራዎችን መጀመር ቀላል እንደሆነና በዚህ መልኩ ስራዎችን አጠናቆ ፍፃሜውን ማየት ትልቅ ብርታት የሚጠይቅ ተግባር መሆኑን በመግለፅ ይህም የፓርቲያችን ዋና መገለጫውም ነው ብለዋል።     በመጨረሻም የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው እንደዚህ ያሉ በጎ ተግባራት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ቢሯቸው ሁሌም የበኩሉን ድጋፍ  እንደሚያደርግ በመግለፅ በአዲስ መልክ ተገንቡቶ የተጠናቀቀውን የቤት ቁልፍ ለወ/ሮ ይመኙሻል ዳኜ ያስረከቡ ሲሆን በኢትዮ-ጣሊያን ኮሌጅ በኩል የተገኘ የአስቤዛ ድጋፍም በእለቱ ድጋፍ ተደርጓል።      ከርክክብ ስነ-ስርዓቱ በኋላ የተሰማቸውን የገለፁት ወ/ሮ ይመኙሻል ዳኜ  በበኩላቸው በፊት የነበሩበት ቤት በጣም ከማርጀቱ በተጨማሪ ዝናብ በዘነበ ቁጥር ቤት ውስጥ ውሃ ገብቶ እየተኛ እንቅልፍ ይነሳቸው እንደነበር አስታውሰው አሁን ላይ ያን ሁሉ ስቃይ ያለፍኩት በእናንተ ነው በማለት ሁሉንም በማመስገን የማይጠገብ ምርቃታቸውን መርቀዋል።  የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኬሽን ጥቅምት 17/2015 ዓ.ም

የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊቴክኒክ ኮሌጅ ውጤትን መሰረት ያደረገ ውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና አተገባበርን አስመልክቶ ከ ኮሌጁ መምህራን ጋር ተወያየ። በመድረኩ የ2014 ዓ.ም ውጤትን መሰረት ያደረገ ትምርህትና ስልጠና አተገባበር የነበረበትን ክፍተት እንዲሁም ጠንካራ ጎኖቹ የተገመገሙ ሲሆን በቀጣይም የነበሩ ችግሮችን በመቅረፍና የተገኙ መልካም ውጤቶች በማጠናከር በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሚፈለገው ጥራት ትምህርትና ስልጠናውን ለማከናወን በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከመምህራን ጋር ሰፋ ያለ ውይይት ተካሂዷል። የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ጥቅምት 15 2015 ዓ.ም

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሰራተኞች ለኢትዮጵያ እቆማለሁ፤ ድምጼን አሰማለሁ በሚል መሪ ቃል በተደረገ ሀገራዊ የድጋፍ ሰልፍ ላይ ድምጻቸውን አሰሙ። የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ህዝብ ግንኙነት ጥቅምት 12/2015 ዓ.ም ድሬዳዋ

በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተለያየ የትምህርትና ስልጠና መስክ ያሰለጠናቸውን ሰልጣኝ ተማሪዎችን  አስመረቀ። በምረቃ ስነስርዓቱም ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር፣ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና  ንግድ፣ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሀርቢ ቡህ እና የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እንዲሁም የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ተገኝተው ለተመራቂ ሰልጣኝ ተማሪዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልክት አስተላልፈዋል። ኮሌጁ ከተቋቋመ ከ2001 እስከ 2015 ዓ.ም በ9 ዲፓርትመንቶች ማለትም በአውቶቲቭ፣ በአሌክትሪክ፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በአይ.ሲ.ቲ፣ በኮንስትራክሽን፣ በሆቴል፣ በሰርቬይ፣ በፈርኒቸር እና በቢዝነስ  ከደረጃ 1 እስከ ደረጃ 5 አጠቃላይ በመደበኛ ስልጠና 16,461 አንዲሁም በአጫጭር ስልጠና ሙያ መስኮች ከ20,000 በላይ ሰልጣኞች አሰልጥኗል፤ በተጨማሪም በሳተላይት ዲግሪ መርሃ-ግብር ከ300 በላይ ሰልጣኞች በመደበኛና በኤክስቴንሽን መርሃ ግብር ተቀብሎ እንያሰለጠ ይገኛል፡፡ በዛሬው ዕለት የተመረቁ ሰልጣኝ ተማሪዎች ብዛት ወንድ-246 እና ሴት-297 በድምሩ 543 ሲሆኑ የዘንድሮ ምረቃ ስነስርዓት ልዩ የሚያደርገው ጉዳይ በዘርፍ አዲሱ ፖሊሲ መሰረት ከፍተኛ አካዳሚክ ውጤት ያላቸው ሰልጣኝ ተማሪዎች ተሸላሚ መሆናቸው ነው፡፡