uz
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Kanalga Telegram’da o‘tish

Ko'proq ko'rsatish
1 740
Obunachilar
+224 soatlar
+17 kunlar
-430 kunlar
Postlar arxiv
#ዜና | በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከ140 ሚሊዮን ብር በላይ የፈሰሰበት የዲጂታል መሠረተ ልማት ተመረቀ #DireTvአማርኛ | ሰኔ 8 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ ​በድሬዳዋ አስተዳደር በሚገኘው የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ @ቴክኒክ ኮሌጅ፣ በ"ትምህርት እና ክህሎት ለሥራ ዕድል ፈጠራ ፕሮጀክት" (EASE) አማካኝነት ከ140 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነቡ ዘመናዊ የዲጂታል መሠረተ ልማቶች በዛሬው ዕለት ተመርቀዋል። ​የኮሌጁን ተቋማዊ አሠራር ለማዘመንና የመማር-ማስተማር ሂደቱን ለማቀላጠፍ የተገነቡት እነዚህ መሠረተ ልማቶች ዘመናዊ ዳታ ሴንተር እና የውስጥ የኔትወርክ መሠረተ ልማት ግንባታ፣ የኢ-ለርኒንግ (e-Learning) ላብራቶሪ፣ ተቋሙን መረጃዎች ተደራሽ የሚያደርግ ዳይናሚክ ዌብሳይት ይዟል። ​በምርቃት ሥነ ሥርዓቱ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው፣ የፌደራል ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት ምክትል ዳይሬክተርና የEASE ፕሮጀክት አስተባባሪ ዶክተር ሀብቶም ገብረእግዚአብሔር፣ እንዲሁም የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ​አቶ ሮቤል ጌታው እንዳሉት "መንግሥት የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆችን @topfans ለማደራጀት በሚያደርገው ጥረት ውስጥ ይህ የዲጂታል መሠረተ ልማት ለኮሌጁ ማኅበረሰብ ፈጣንና አስተማማኝ የመረጃ ተደራሽነትን በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል።" ​የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ "ኢትዮጵያ በ2030 ዓ.ም የተቋማትን አገልግሎት ሙሉ በሙሉ በዲጂታል ሥርዓት ለማስተሳሰር የያዘችውን ብሔራዊ ዕቅድ ከግብ ለማድረስ ይህ ፕሮጀክት ትልቅ እርምጃ ነው። በሥራ ሂደት ውስጥ የሚታዩ ክፍተቶችን በመቅረፍም በቴክኖሎጂ የሰለጠነና በሙያ የጎለበተ የሰው ኃይል ለማፍራት ያስችላል።" ብለዋል። ​አዲሱ የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት የኮሌጁን የመማር ማስተማር ሂደት ከማቀላጠፉም በላይ፣ ለተማሪዎችና መምህራን ሰፊ የመረጃ ነፃነትና ቀልጣፋ አገልግሎት የሚፈጥር በመሆኑ የላቀ ተስፋ ተጥሎበታል። ​ ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት አማራጮች ያግኙ፡- በፌስቡክ -https://www.facebook.com/share/19wDiZAD7x/?mibextid=wwXIfr በቴሌግራም -https://t.me/EIPC2001 በቲክቶክ -https://www.tiktok.com/@ethioitaly2001?_t=ZM-90MxIrBN8qe&_r=1 በዌብሳይት - https://ethioitalypolytechniccollege.com/

ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በጀት አመቱ የ9 ወር የእቅድ አፈፃፀሪፖርት ለኮሌጁ ቦርድ ቀርቦ ተገመገመ፡፡ የተቋሙ የ9 ወራት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አማካኝነት ለቦርዱ የቀረበ ሲሆን በዚህም ኮሌጁ ባለፉት 9 ወራት ያከናወናቸውን ቁልፍ ተግባራት እንዲሁም የተመዘገቡ ውጤቶችን በማካተት ለቦርዱ ሪፖርት አቅርበው ገለፃ ያደረጉ ሲሆን አያይዘውም በቀጣይ በተቋሙ ሊከናወኑ በእቅድ የተያዙ ተግባራትን ለቦርድ አባላቱ በዝርዝር አመላክተዋል፡: በመድረኩ የቀረበውን አፈፃፀም ሪፖርት መነሻ በማድረግም የቦርድ አባላቱ ግብረ- መልሳቸውን የሰጡበት ሲሆን በተጨማሪም ኮሌጁ በቀጣይ በሚኖረው የስራ እንቅስቃሴ ላይ ምክረ-ሃሳባቸውን አስቀምጠዋል:: ቦርዱ በኮሌጁ በነበረው ቆይታ በEASE ፕሮጀክት ድጋፍ አማካኝነት በተቋሙ የተሰሩ የዳታ ማዕከል(Data Center) ፣ የኔትወርክ መሰረተ ልማት ዝርጋታንና የተገኙ ውጤቶች ተዘዋውረው ምልከታ አድርገዋል:: በተጨማሪም የኮሌጁን አለም አቀፋዊ ግንኙነት በማጠናከሩ ረገድ ጉልህ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ታምኖበት በEASE ፕሮጀክት ድጋፍ የሰራውን የተቋሙን ድህረ-ገፅ(Website) ቦርዱ በዝርዝር ከተመለከተ በኃላ እውቅና በመስጠት የኮሌጁን ዌብሳይት በይፋ አገልግሎት አስጀምሯል:: በመጨረሻም የኮሌጁ ቦርድ ሰብሳቢ እንዲሁም የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ እና የንግድ፣ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሀርቢ ቡህ በቀረበው አፈፃፀም ሪፖርትና በተከናወኑ የለውጥ ስራዎች ላይ ማጠቃለያ እንዲሁም የቀጣይ ስራ አቅጣጫና መመሪያን በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል፡፡ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ግንቦት 28/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

ለኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን ባለፉት ሳምንታት በOnline እና በተግባር ተደግፎ ሲሰጥ የቆየው የInnovative Pedagogy ስልጠና ተጠቀቀ:: ስልጠናው በመጀመርያ ዙር በኮሌጁ 20 ለሚሆኑ አሰልጣኝ መምህራን መሰጠቱ የተገለፀ ሲሆን ይህ የInnovative Pedagogy ስልጠና በፌደራል ስራና ክህሎት ሚኒስቴር አዘጋጅነት እንዲሁም በፌደራል TVET ኢንስቲትዩት ባለሞያዎች አማካኝነት ሲሰጥ የቆየ የ15 ቀን የOnline እና የ5 ቀን ተግባራዊ ስልጠናን ያካተተ እንደነበርም ተገልፇል:: ባለፉት ሳምንታት የInnovative Pedagogy ስልጠናውን ሲከታተሉ የቆዩት የኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራን እንደገለፁት ያገኙት ስልጠና ወቅቱን ያማከለና ዲጂታላይዜሽን ላይ ያተኮረ በመሆኑ የስልጠና አሰጣጥ ሂደታቸውን ምቹና ቀልጣፋ በማድረግ ከሰልጣኝ ተማሪዎች ጋር ያላቸውን ተግባቦት ወደ ላቀ ደረጃ ከማሻገሩም ባሻገር በዘርፉ የሚፈለገውን ውጤት ለማስመዝገብ የሚረዳ የማሰልጠኛ ስነ-ዘዴ እንደሆነም ሀሳባቸውን አካፍለዋል:: የInnovative Pedagogy ስልጠናውን በፕሮጀክቱ ትግበራ የትኩረት ዘርፍ በሆኑት የኮሌጁ የማኑፋክቸሪንግ፣ የኤሌክትሪክ እና የአውቶሞቲቭ ዲፓርትመንቶች ላይ ለሚገኙ 20 አሰልጣኝ መምህራን ሲሰጥ መቆየቱን የገለፁት በኮሌጁ የEASE ፕሮጀክት አስተባባሪ ኢ/ር ፋሲል ማዘንጊያ ሲሆኑ የዚህ ስልጠና አላማም የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኞች አለም የደረሰበትን የዲጂታልይዜሽን የስልጠና አሰጣጥ ስነ-ዘዴ ጋር አብረው እንዲጏዙ ለማስቻል እንደሆነ አስታውቀው ከዚህ ስልጠና በተጨማሪም ራስን በየጊዜው ማሻሻል እንደሚገባም ገልፀዋል:: በስልጠናው ማጠቃለያ የInnovative Pedagogy ስልጠናውን ወስደው ያጠናቀቁ አሰልጣኝ መምህራን በዲጂታላይዜሽን የስልጠና ስነ-ዘዴው በመታገዝ በቀጣይ ስልጠና የሚሰጡበትን የአሰራር ሂደት በመድረኩ ያቀረቡ ሲሆን በዚህ መነሻነትም ለቀጣይ የስልጠና ዘመን ከወዲሁ በቂ ዝግጅቶች ተደርገውበት ዲጂታል የማሰልጠኛ ስነ-ዘዴው ስራ ላይ እንደሚውልም ተገልፇል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ግንቦት 21/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

ለኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን ባለፉት ሳምንታት በOnline እና በተግባር ተደግፎ ሲሰጥ የቆየው የInnovative Pedagogy ስልጠና ተጠቀቀ:: ስልጠናው በመጀመርያ ዙር በኮሌጁ 20 ለሚሆኑ አሰልጣኝ መምህራን መሰጠቱ የተገለፀ ሲሆን ይህ የInnovative Pedagogy ስልጠና በፌደራል ስራና ክህሎት ሚኒስቴር አዘጋጅነት እንዲሁም በፌደራል TVET ኢንስቲትዩት ባለሞያዎች አማካኝነት ሲሰጥ የቆየ የ15 ቀን የOnline እና የ5 ቀን ተግባራዊ ስልጠናን ያካተተ እንደነበርም ተገልፇል:: ባለፉት ሳምንታት የInnovative Pedagogy ስልጠናውን ሲከታተሉ የቆዩት የኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራን እንደገለፁት ያገኙት ስልጠና ወቅቱን ያማከለና ዲጂታላይዜሽን ላይ ያተኮረ በመሆኑ የስልጠና አሰጣጥ ሂደታቸውን ምቹና ቀልጣፋ በማድረግ ከሰልጣኝ ተማሪዎች ጋር ያላቸውን ተግባቦት ወደ ላቀ ደረጃ ከማሻገሩም ባሻገር በዘርፉ የሚፈለገውን ውጤት ለማስመዝገብ የሚረዳ የማሰልጠኛ ስነ-ዘዴ እንደሆነም አስተያየታቸእን ሰጥተዋል:: የInnovative Pedagogy ስልጠናውን በፕሮጀክቱ ትግበራ የትኩረት አቅጣጫ በሆኑት የኮሌጁ የማኑፋክቸሪንግ፣ የኤሌክትሪክ እና የአውቶሞቲቭ ዲፖርትመንቶች ላይ ለሚገኙ የመጀመርያ ዙር 20 አሰልጣኝ መምህራን ሲሰጥ መቆየቱን የገለፁት በኮሌጁ የEASE ፕሮጀክት አስተባባሪ ኢ/ር ፋሲል ማዘንጊያ ሲሆኑ የዚህ ስልጠና አላማም የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኞች አለም የደረሰበትን የዲጂታልይዜሽን የስልጠና አሰጣጥ ስነ-ዘዴ ጋር አብረው እንዲጏዙ ለማስቻል እንደሆነ አስታውቀው ከዚህ ስልጠና በተጨማሪም ራስን በየጊዜው ማብቃት ተገቢ ተገቢ ነውም ብለዋል:: በስልጠናው ማጠቃለያ የInnovative Pedagogy ስልጠናውን ወስደው ያጠናቀቁ አሰልጣኝ መምህራን በዲጂታላይዜሽን የስልጠና ስነ-ዘዴው በመታገዝ በቀጣይ ስልጠና የሚሰጡበትን የአሰራር ሂደት በመድረኩ ያቀረቡ ሲሆን በዚህ መነሻነትም ለቀጣይ የስልጠና ዘመን ከወዲሁ በቂ ዝግጅቶች ተደርገውበት ዲጂታል የማሰልጠኛ ስነ-ዘዴው ስራ ላይ እንደሚውልም ተገልፇል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ግንቦት 21/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

ADRA Ethiopia ፕሮጀክት ከኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመተባበር ላለፉት አመታት ሲተገብር የቆየውን የVQEP/Green Energy TVET Project Phase II ፕሮጀክት አጠናቆ የማጠቃለያ መድረክ አካሄደ:: ፕሮጀክቱ ባለፉት አመታት በአስተዳደራችን ለመጀመርያ ጊዜ ከ130 በላይ ወጣቶችን አዲስና ተፈላጊ በሆነ የሙያ ዘርፍ(Solar PV Installation & Maintenance) ላይ አሰልጥኖ ወደ ስራ እንዲገቡ ያደረገ ፕሮጀክት መሆኑን ያስታወሱት የስራና ክህሎት ቢሮ ሀላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ሲሆኑ ፕሮጀክቱ በስልጥናው ዘርፍ ለፈጠረው አቅም ፣በከተማና በገጠር ላከናወነው የስራ እድል ፈጠራ እንዲሁም የSolar ኢነርጂን ተደራሽ በማድረግ የGreen TVTን በተግባር እንድናሳይ ላከናወናቸው ተግባራት በቢሮውና በአስተዳደሩ ስም ምስጋና እቅርበዋል:: ADRA Ethiopia በሀገሪቱ ብዙ ቦታዎች ላይ ይንቀሳቀስ የነበረ ቢሆንም ድሬዳዋን ተደራሽ ያደረገው በዚህ ፕሮጀክት መሆኑን ያስተወሱት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ ከዚህ በፊት ያልነበሩ እንቅስቃሴዎችና ብዙ በረከቶችንም ወደ ተቋማች ይዞልን የመጣ ፕሮጀክት ነው ያሉ ሲሆን በGreen Energy ላይ ግንባር ቀደም ሆነን እንድንሰራ ፈር የቀደደልን ልዩ ፕሮጀክት ነውም ብለዋል:: የኮሌጁ ዲን አክለውም ፕሮጀክቱ ያስቀመጠውን ግብ በመምታት ረገድ ጥሩ የሚባል አፈፃፀም እንደነበረው አስታውሰው ፕሮጀክት የራሱ የጊዜ ገደብ ያለው በመሆኑ ዛሬ ማጠቃለያ ብናደርግም በቀጣይ በጋራ የምንሰራቸው በርካታ ስራዎች በመኖራቸው እንደ ተቋም ደስተኞች ነንም ብለዋል:: የADRA Ethiopia ፕሮጀክት በ120 ሀገሮች ውስጥ ቢሮ ከፍቶ የሚቅሳቀስ ግብረ ሰናይ ድርጅት እንደሆነ ያስታወሱት የፕሮጀክቱ ዋና ዳይሬክቶር ዶ/ር ዘሪሁን አዋኖ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ ላለፉት 43 አመታትም በተለያዩ የሀገሪቷ ክፍሎች ላይ ሰው ተኮር ስራዎችን እየሰራ የሚገኝ ፕሮጀክት መሆኑን ገልፀው በውቢቷ ድሬዳዋ በነበረው የፕሮጀክቱ ሂደትና የተመዘገበው ውጤት እጅግ የሚያኮራና የአስተዳደሩንም ሆነ የኮሌጁን አመራሮች ቁርጠኝነት የተመለከቱበት እንደነበርም ገልፀዋል:: በማጠቃለያ መድረክ ላይ የADRA Ethiopia ፕሮጀክት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ያከናወናቸውን ቁልፍ ተግባራትና ያስመዘገባቸው አመርቂ ውጤቶች በፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ ሀብታሙ በየነ አማካኝነት ለባለድርሻ አካላት በዝርዝር የቀረበ ሲሆን በተጨማሪም በፕሮጀክቱ ሂደት ላይ በኮሌጁ ጥናት በማድረግ የመጣውን ለውጥ የሚገመግም ሰነድም በመድረኩ ቀርቦ ገለፃ ተደርጎበታል:: ADRA Ethiopia ከጀርመን የልማት ትብብር ተቋም(BMZ) እና በADRA Germany በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ከጥቅምት 2015 ዓ.ም ጀምሮ በድሬዳዋ አስተዳደር ከኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እና ከሌሎች ቁልፍ ባለ ድርሻ አካላት በመተባበር ሲተገበር የነበረው የVQEP/Green Energy TVET Project Phase II ፕሮጀክት በርካታ ስኬቶችን በማስመዝገብ በዛሬ እለት ፍፃሜውን አድርጏል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ግንቦት 20/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

እንኳን አደረሳችሁ!! ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አል አድሃ(አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልኩ በዓሉ የፍቅር፣ የደስታ እና የመተሳሰብ እንዲሆንላችሁ
+1
እንኳን አደረሳችሁ!! ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አል አድሃ(አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልኩ በዓሉ የፍቅር፣ የደስታ እና የመተሳሰብ እንዲሆንላችሁ ከወዲሁ እመኛለሁ:: አቶ ታደለ አሰፋ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን #ኢድ_ሙባረክ!!

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት በአጫጭር ስልጠና ማዕቀፍ የአምራች ኢንዱስትሪውን ፍላጎት ለመለየት የተዘጋጀ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ለባለድርሻ አካላት ቀርቦ ውይይት ተካሄደ:: አምራች ኢንዱስትሪው የሚጠይቀውን ብቁና የሰለጠን የሰው ሀይል በአጫጭር ስልጠና ማዕቀፍ አሰልጥኖ ለማቅረብ ታሳቢ ያደረገ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት በተቋም ደረጃ የተጠና ሲሆን ወጣቶች ጊዜው የሚጠይቀውን የአጫጭር ስልጠና ምርጫቸው ከማድረጋቸው ጋር ተያይዞ የአምራች ኢንዱስትሪውን የሙያ ፍላጎት መሰረት ያደረገ የአጫጭር ስልጠና ፕሮግራም ለመቅረፅ የጥናት ቡድኑ ከኢንዱስትሪ አድቫይዘሪግ ቦርድ አባላት ጋር በቅንጅት መስራቱም ተገልፇል:: በEASE ፕሮጀክት ትግበራ ትኩረት ተደርጎባቸው ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል ለኢንዱስትሪው ግብዓት የሚሆኑ ብቁ ባለሙያዎችን የማፍራቱን ሂደትን መደገፍ ዋነኛው መሆኑ የተገለፅ ሲሆን የፕሮጀክቱ ባለሙያዎች ከትምህርትና ስልጠና ዘርፉ ጋር በመቀናጀት ባዘጋጁት የኢንዱስትሪውን ፍላጎት መሰረት ያደርገ የአጫጭር ስልጠና ፕሮግራም ላይ አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል ሲያደርግም ቆይቷል:: በፍላጎት ዳሰሳ ጥናቱ መሰረት ውጤታማነታቸው ታምኖበት የተለዩ የአጫጭር ስልጠና ፕሮግራሞችን የጥናት ቡድኑ በዝርዝር ያቀረበ ሲሆን በተጨማሪም ለስልጠና ፕሮግራሞቹ እየተዘጋጁ ሚገኙት ማሰልጠኛ ሞጁሎች ላይም ለባለድርሻ አካላት ገለፃ አድርገዋል:: በመድረኩ በቀረቡት አጠቃላይ ሰነዶች መነሻነት ውይይት የተካሄደ ሲሆን ተሳታፊዎች በአጫጭር ስልጠና ማዕቀፍ የበቃ የሰው ሀይል ከማሟላት አኳያ በጥናቱ ያልተዳሰሱና ሊካተቱ ይገባል ያሏቸውን ጉዳዮች ለጥናት ቡድኑ አመላክተዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ግንቦት 18/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

ለኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን በInnovative Pedagogy ላይ ያተኮረ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል:: ለኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራን የተሰጠ የሚገኘው የInnovative Pedag
+9
ለኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን በInnovative Pedagogy ላይ ያተኮረ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል:: ለኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራን የተሰጠ የሚገኘው የInnovative Pedagogy ስልጠና በፌደራል ስራና ክህሎት ሚኒስቴር አዘጋጅነት ከፌደራል TVET ኢንስቲትዩት በመጡ የዘርፉ ባለሞያዎች እየተሰጠ የሚገኝ ሲሆን የስልጠናው ዋና ዓላማም የተለመደውን የማሰልጠኛ ስነ-ዘዴ ለማሻሻልና ጊዜው የደረሰበትን ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም ትምህርትና ስልጠናውን ለማዘመን ያለም ስልጠና እንደሆነም ተገልፇል:: ይህ በኮሌጁ ለ5 ቀናት የሚቆየው ስልጠናም ባለፉት 15 ቀናት አሰልጣኝ መምህራኑ በOnline ሲከታተሉት የነበረውን የ Innovative Pedagogy ስልጠና በተግባር የሚሰለጥኑበት እንደሆነው ተመላክቷል:: ስልጠናው በሀገሪቱ በሚገኙና የEASE ፕሮጀክት በሚተገበባቸው 24 ፖሊቴክኒኮች ላይ ለሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን አየተሰጠ እንደሚገኝም ተገልፇል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ግንቦት 11/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

ሀገር አቀፍ የካይዘን ውድድርን አስመልክቶ በኮሌጁ ምልከታ ተካሄደ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በካይዘን ፅንሰ-ሃሳብ መነሻነት እያከናወናቸው የሚገኙ ዘርፈ ብዙ ተግባራትና ወቅታዊ አፈፃፀም ላይ ከፌደራል በመጡ ባለሙያዎች በዛሬው እለት ግምገማ ተካሂዷል:: የሀገር አቀፍ የካይዘን ውድድር አካል በሆነውና ከፌደራል በመጡ ባለሙያዎች በተካሄደው ምዘና በኮሌጁ የስራ ቦታን ምቹ ከማድረግ ፤ ብክነትን ከመቀነስ፤ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትና ፍጥነትን ከማሻሻል አኳያ በተቀመጡ መመዘኛዎች የተከናወኑ ተግባራትንም ገምግሟል:: የምልከታ ቡድኑ በኮሌጁ የካይዘን ትግበራ አጠቃላይ የአፈፃፀም ሪፖርትን የተመለከት ሲሆን ከ8ቱ የውጤት አመላካች አኳያ የተገኙ ውጤቶችን በሪፖርቱ ተመልክተዋል:: በማስቀጠል ቡድኑ በተቋሙ የሚገኙ የስራ ክፍሎችና የስልጠና ወርክሾፖች ላይ የተከናወኑ የካይዘን ትግበራዎችን ከመመልከት በተጨማሪ የካይዘን ትግበራው ውጤታማነትና የተገኘውን ለውጥ የሚያመላክቱ ሰነዶችን በዝርዝር የገመገመ ሲሆን በኮሌጁ በትግበራ ወቅት የተገኙ ምርጥ ተሞክሮችንም መመልከት ችሏል:: "ዛሬን እናሻሽል፤ ብክነትን እንቀንስ፤ ጥራትና ፍጥነትን እንጨምር፤ ነገን እንገንባ"!! የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሚያዚያ 30/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ