1 751
订阅者
-124 小时
+37 天
+630 天
帖子存档
በዚህ ክረምት እረፍትዎን ወደ ገቢ ምንጭነት ይቀይሩ!
የዘመኑን ተፈላጊ ክህሎቶች በመማር እራስዎን ለስራ ገበያ ብቁ ማድረግ ይፈልጋሉ? እንግዲያውስ መልካም ዜና! የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከ A2B Creatives ጋር በመተባበር ለሁለት ወራት የሚቆይ አጠቃላይ የቪዲዮ ኤዲቲንግ እና ግራፊክስ ዲዛይን ስልጠና አዘጋጅቶላችኋል።
👉 የግራፊክስ ዲዛይን (Graphics Design): ማራኪ የሆኑ የብራንዲንግ ስራዎችን፣ ፍላየሮችን እና የማህበራዊ ሚዲያ ፖስተሮችን ፣ ሎጎዎችን መስራት (Adobe Photoshop,Canva ...)።
👉 የቪዲዮ ኤዲቲንግ (Video Editing): ለዩቲዩብ፣ ለቲክቶክ፣ ለፊልሞች እና ለድርጅቶች ማስታወቂያ የሚሆኑ ፕሮፌሽናል ቪዲዮዎችን ማቀናበር (Adobe Premiere Pro ...)።
ለመማር ምቹ እና ዘመናዊ የሆኑ መሰረተ-ልማቶች የተሟሉለት፦
🖥 Professional Computer Lab: ዘመናዊ የኮምፒውተር ላብራቶሪ።
🌐 Internet Access: ማቴሪያሎችን በነፃነት ለማውረድ የሚያስችል ፈጣን የኢንተርኔት አገልግሎት።
👨🏫 Experienced Instructor: በዘርፉ ሰፊ የገበያ እና የማስተማር ልምድ ባላቸው ባለሙያ አስተማሪዎች
https://docs.google.com/forms/d/18NF9YM3GTqrA6aMYC9koNvyKaI8CvBLzr40JbBGUd6o/viewform
📞 ለበለጠ መረጃ እና ለምዝገባ በሚከተሉት ስልክ ቁጥሮች ያግኙን፦
📱 0976315798
📱 0968377071የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አመራሮችና አባላትን ያካተተ ልዑካን ቡድን በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የመስክ የስራ ጉብኝት አደረገ፡፡
#EIPC ሰኔ 25/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አመራሮችና አባላትን የያዘው ልዑካን ቡድን የኮሌጁን አጠቃላይ የስራ እቅስቃሴ መቃኘት ሚያስችለውን የመስክና ስራ ጉብኝት በዛሬው እለት በኮሌጁ ማካሄድ ችሏል::
ልዑካን ቡድኑን ተቀብለው ያስተናገዱት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በንግግራቸው.. ሰልጥነው የበቁና በሙያቸው ሀገር የሚያሻግሩ አምራች ዜጎች መፍለቂያ ወደሆነው ኮሌጃችን እንኳን በደህና መጣችሁ ያሉ ሲሆን ተቋማችን ከድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ጋር በመቀናጀት አስተዳደሩ ላይ ለውጥ የሚያመጡ ተግባራትን የማከናወን ፍላጎት ያለው መሆኑን ገልፀው በቀጣይ በምጠይቁን ጉዳዮች በሙሉ ከተቋማችሁ ጋር በቅንጅት ለመስራት በኮሌጁ በኩል ሙሉ ዝግጁነት ያለ መሆኑንም ገልፀዋል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከምስረታው ጀምሮ አሁን እስከደረሰበት ደረጃ ያለውን አጠቃላይ የኮሌጁ እንቅስቃሴ በኮሌጁ ዲን አማካኝነት ለቡድኑ ገለፃ የተደረ ሲሆን በዚህም የISO 9001:2015 የጥራት አስተዳደር ስርዓት አውቅና ከማግኘት ባሻገር በትምህርትና ስልጠናው፣ በቴክኖሎጂ ልማትን ጨምሮ በዲጂታላይዜሽን አተገባበር የተከናወኑ የለውጥ ስራዎችና የተመዘገቡ ውጤቶችን በዝርዝር ለልዑካን ቡድኑ ገለፃ አድርገዋል፡፡
ቀደም ሲል በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ በቅንጅት የተሰሩ የተወሰኑ ስራዎች መኖራቸውን ያስታወሱት በኮሌጁ የቴ/ሽ/ኢ/ኤ/አ ስራ ሂደት ሀላፊና የኮሌጁ ም/ል ዲን አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ በቀጣይም የሁለቱን ተቋማት ግንኙነቶችን በማጠናከርና የጋራ መግባቢያ ስምምነቶችን በማድረግ በአጫጭር ስልጠናዎች፣ በቴክኒካል ጉዳዮች እንዲሁም በቴክኖሎጂ ልማቶች ላይ በጋራ እንሰራለንም ብለዋል::
በተጨማሪም የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መመሪያ አባላትን የያዘው ልዑክ በኮሌጁ የሚገኙ የስልጠና ወርክሾፖችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን በነበራቸው ጉብኝትም አጠቃላይ በኮሌጁ የስራ እንቅስቃሴ መደነቃቸውን ገልፀው በቀጣይ ስልጠናዎችን ጨምሮ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ከኮሌጁ ጋር ለመስራት ፅኑ ፍላጎት ያሳደረባቸው ጉብኝት እንደነበርም ገልፀዋል::
ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት አማራጮች ያግኙ፡-
በፌስቡክ -https://www.facebook.com/share/19wDiZAD7x/?mibextid=wwXIfr
በቴሌግራም -https://t.me/EIPC2001
በቲክቶክ -https://www.tiktok.com/@ethioitaly2001?_t=ZM-90MxIrBN8qe&_r=1
በዌብሳይት - https://ethioitalypolytechniccollege.com/
ለኮሌጁ ሰራተኞች በISO 9001:2015 QMS ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ::
#EIPC ሰኔ 25/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የISO 9001:2015 የጥራት አስተዳደር ስርዓት ትግበራን በተመለተ ለኮሌጁ አዲስ ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሂዷል::
በኮሌጁ የጥራት ደረጃን አስጠብቆ የአገልግሎት እርካታን በዘላቂነት የማረጋገጥ ሚናው የሁሉም ሰራተኛ እንደሆነ የገለፁት በኮሌጁ የቴ/ሽ/ኢ/ኤ/አ ሀላፊና የኮሌጁ ም/ል ዲን አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ በተቋሙ ከአመራር ጀምሮ በየደረጃው የሚገኝ በሁሉም ሰራተኛ በISO 9001:2015 QMS ትግበራ ተመሳሳይ ግብዛቤ እንዲኖር ለማስቻል ታልሞ ስልጠናው መዘጋጀቱንም ገልፀዋል::
በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ የኮሌጁን የISO 9001:2015 QMS አተገባበር ሂደትና የሰራተኛው ሚናን አስመልክቶ በኮሌጁ የISO Task Force ባለሙያዎች አማካኝነት ስልጠናውን በተሳካ ሁኔታ መስጠትም ተችሏል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አለም አቅፍ ተወዳዳርነቱን ለማረጋገጥ በቁጠኝነት ባከናወናቸው ተግባራት የISO 9001:2015 የጥራት አስተዳደር ስርዓት እውቅና የተሰጠው በምስራቅ ኢትዮጵያ ብቸኛው የመንግስት ፓሊቴክኒክ ኮሌጅ ሲሆን ትምህርትና ስልጠናውን ጨምሮ አጠቃላይ የደንበኞች አገልግሎቱን በጥራት እየሰጠ የሚገኝ ተቋምም ነው::
ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት አማራጮች ያግኙ፡-
በፌስቡክ -https://www.facebook.com/share/19wDiZAD7x/?mibextid=wwXIfr
በቴሌግራም -https://t.me/EIPC2001
በቲክቶክ -https://www.tiktok.com/@ethioitaly2001?_t=ZM-90MxIrBN8qe&_r=1
በዌብሳይት - https://ethioitalypolytechniccollege.com/
ለኮሌጁ ሰልጣኝ ተማሪዎች በISO 9001:2015 QMS ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ::
#EIPC ሰኔ 23/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የISO 9001:2015 የጥራት አስተዳደር ስርዓት ከትምህርትና ስልጠናው አኳያ የሚጨምረው ጥራት በተመለተ ለኮሌጁ ሰልጣኝ ተማሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሂዷል::
በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ የኮሌጁን የISO 9001:2015 QMS ትግበራ በማስቀጠሉ ሂደት ላይ የሰልጣኞች ሚናን አስመልክቶ በኮሌጁ የISO Task Force ባለሙያዎች ስልጠናውን ለሰልጣኞች በተሳካ ሁኔታ መስጠት ተችሏል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አለም አቅፍ ተወዳዳሪነቱን ለማረጋገጥ በቁጠኝነት ባከናወናቸው ተግባራት የISO 9001:2015 የጥራት አስተዳደር ስርዓት እውቅና የተሰጠው በምስራቅ ኢትዮጵያ ብቸኛው የመንግስት ፓሊቴክኒክ ኮሌጅ ሲሆን ትምህርትና ስልጠናውን ጨምሮ አጠቃላይ የደንበኞች አገልግሎቱን በጥራት እየሰጠ የሚገኝ ተቋምም ነው::
ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት አማራጮች ያግኙ፡-
በፌስቡክ -https://www.facebook.com/share/19wDiZAD7x/?mibextid=wwXIfr
በቴሌግራም -https://t.me/EIPC2001
በቲክቶክ -https://www.tiktok.com/@ethioitaly2001?_t=ZM-90MxIrBN8qe&_r=1
በዌብሳይት - https://ethioitalypolytechniccollege.com/
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት የአምራች ኢንዱስትሪው ፍላጎትን መነሻ አድርጎ በኮሌጁ የተዘጋጀው የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ማጠቃለያ መድረክ ተካሄደ::
#EIPC ሰኔ 19/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
በEASE ፕሮጀክት ድጋፍ በኮሌጁ በተዘጋጀው ጥናት በቴክኒክና ሙያ ስልጠና፣ በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት አሰጣጥ እንዲሁም በቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ እንዱስትሪውን ከመደገፍ አኳያ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን ለመፍታት ታልሞ በጥናት ቡድኑ የተዘጋጀ ሲሆን የኮሌጁ ኢንዱስትሪ እድቫይዘሪንግ ቦርድ አባላት በተገኙበት የማጠቃለያ ሪፓርት ቀርቧል::
ኮሌጁ ከኢንዱስሪዎች ጋር ያለውን ትስስር ውጤታማነት ለማረጋገጥ የጥናት ቡድኑ በአጭር ፣በመካከለኛና በረጅም ጊዜ የሚተገበሩ ዝርዝር ጉዳዮችን በዳሰሳ ጥናቱ ማስቀመጡን የገለፁት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ አክለውም በኮሌጁ የተካሄዱ ጥናቶችን ወደ ተግባር ለመቀየር ጊዜ ሳይወስድ ትግበራ ማስጀመር እንደሚገባም አሳስበው በትግበራው የተመዘገቡ ውጤቶችን በየጊዜው መገምገም እንደሚገባም ተናግረዋል::
የፍላጎት ዳሰሳ ጥናቱ በአስተዳደሩ በሚገኙና የትኩረት ዘርፍ በሆኑ ሶስት አምራች ኢንዱስትሪዎች ላይ መካሄዱን የገለፁት በኮሌጁ የEASE ፕሮጀክት አስተባባሪ ኢ/ር ፋሲል ማዘንጊያ ሲሆኑ በቀጣይ ተሞክሮችን በመቀመርና አቅምን በማጎልብት ወደ ሌሎች ኢንዱስትሪዎችም የማስፋት ተግባር እንደሚከናወን ገልፀዋል::
በዳሰሳ ጥናቱ ማጠቃለያ ላይ በቀረበው ሪፖርት ከኢንዱስትሪ ተወካዮችና ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት የተደረገ ሲሆን በቀጣይ የሚኖረው ትግበራ ውጤታማነትን ለማረጋገጥ አምራች ኢንዱስትሪዎች ሊያከናውኗቸው የሚገቡ ዝርዝር ጉዳዮችም በመድረኩ ተመላክተዋል::
ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት አማራጮች ያግኙ፡-
በፌስቡክ -https://www.facebook.com/share/19wDiZAD7x/?mibextid=wwXIfr
በቴሌግራም -https://t.me/EIPC2001
በቲክቶክ -https://www.tiktok.com/@ethioitaly2001?_t=ZM-90MxIrBN8qe&_r=1
በዌብሳይት - https://ethioitalypolytechniccollege.com/
Repost from Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
“የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ስኬት የሚለካው በተመራቂዎች ብዛት ብቻ አይደለም፣ በፈጠሩት ሥራ፤ በመሰረቱት ኢንተርፕራይዞች እና በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ባሳደሩት ተጽዕኖ ጭምር ነው”
ክቡር አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የመንግስት ተጠሪ እና የብልጽግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ስር የሚገኙ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጆች አሰልጣኝ መምህራንና ባለሙያዎች እንዲሁም የዲፓርትመንት ተጠሪዎችን አቅም ለማሳደግ የሚያስችል "የ21ኛው ክፍለ ዘመን የTVET ራዕይ: ከክህሎት ወደ ሀገራዊ ኢኮኖሚያዊ ትራንስፎርሜሽን" በሚል መሪ ሀሳብ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የመንግስት ተጠሪ እና የብልጽግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ክቡር አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል፡፡
የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ተቋማት እውቀትን ከክህሎት ጋር አሰናስለው እጀ- ወርቅ ባለሙያ እንዲሆኑ በማገዝ እረገድ የቴክኒክ ሙያ እና ትምህርት ስልጠና ጥራትን በማሻሻል ከዘመናዊ የዲጂታል የስራ ገበያ ጋር የተጣጣሙ የስራ ፈጠራ ክህሎቶችን በማዳበር ዘርፈ ብዙ ስራዎች መሰራታቸውን ገልጸው ይህም በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በዓለም የሥራ ገበያ ላይ ስኬታማ ለመሆን በራስ መተማመንን ያጎናፅፋል ብለዋል።
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው ነባሩን ትምህርትና ስልጠና ጥራት ባለው መልኩ በአዲስ መልክ ፖሊሲን በማሻሻል ጠንካራ ተቋማትን በመፍጠር ሂደት ወስጥ ውጤታማ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አንስተው ትውልድን በመቅረጽ እና ሀገርን በማሻገር በተቋም ግንባታ ቢሮው በሰው ሀይል በቴክኖሎጂ፣ በግብዓት አቅርቦት እንዲሁም ክህሎትን በብቃት የተላበሰ የሰው ሀይልን በመፍጠር ረገድ አመርቂ ስራዎች መሰራታቸውን የተናገሩ ሲሆን በቀረበውም ገለጻ ላይ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሰኔ 18/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
+4
#አሁን
#Happeningnow
በአስተዳደሩ ለሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራንና አጠቃላይ ማህበረሰብ "የ21ኛው ክፍለ ዘመን የTVET ራዕይ: ከክህሎት ወደ ሀገራዊ ኢኮኖሚያዊ ትራንስፎርሜሽን" በሚል መሪ ሀሳብ ሰነድ እየቀረበ ይገኛል።
ሰኔ 18/2018 ዓ.ም፤
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የEASE (Education and Skills for Employability) ፕሮጀክት ትግበራ አጠቃላይ አፈፃፀም ግምገማ ተካሄደ::
ሰኔ 17/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
የEASE ፕሮጀክት በኮሌጁ ትግበራ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ባለፋት ሁለት አመታት የነበረውን አጠቃላይ የፕሮጀክቱ አፈፃፀም ከአለም ባንክ እንዲሁም ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር የተወጣጡ የፕሮጀክቱ ሀላፊዎችን ያካተተ ልኡካን ቡድን የኮሌጁ አድቫይዘሪንግ ቦርድ በተገኘበት የፕሮጀክቱን አፈፃፀም ግምገማ አካሂዷል::
የፕሮጀክቱ ትግበራ አፈፃፀም ሪፖርት በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አማካኝነት ለልዑካን ቡድኑ የቀረበ ሲሆን በዚህም የEASE(Education and Skills for Employability ፕሮጀክት ትግበራ ትኩረት ከሚያደርግባቸው ስምንቱ Sub-Components አኳያ የተሰሩ ስራዎችን በዝርዝር አቅርበዋል::
በቀረበው ሪፖርት መሰረት በፕሮጀክቱ የሁለት አመት ቆይታ ከተከናወኑ ቁልፍ ተግባራት መካከል ….
- የአሰልጣኝ መምህራን እና ሰራተኞች አቅም ግንባታ...
- የወጣቶች ስራ ዕድል ፈጠራ...
- የኢንዱስትሪዎች ትስስርን የማጎልበት...
- በኮሌጁ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ማስፋፊያ ስራዎች...
- የICT መሰረተ ልማት ዝርጋታ...
- ኮሌጁን ኢንተርፕሩነር ለማድረግ የተሰሩ ስራዎች...
- ሴት ሰልጣኞች እና ሴት ሰራተኞችን በልዩ ሁኔታ የማብቃት የመደግፍ ስራ...
- እንዲሁም አካታችነት ላይ ሴቶችና አካል ጉዳተኞችን የመደገፍና የማቋቋም ስራዎች በኮሌጁ በEASE ፕሮጀክት ባለፉት ሁለት አመታት ከተከናወኑ ቁልፍ ተግባራት መካከል እንደሚጠቀሱ በሪፖርቱ ተመላክቷል::
የልኡካን ቡድኑ ከቀረበው የአፈፃፀም ሪፖርት ባሻገር በEASE ፕሮጀክት በኮሌጁ የተከናወኑ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን በተጨማሪም በኢንዱስትሪ ትስስር ላይ የተከናወኑ ውጤታማ ስራዎችንም እንዱስትሪዎች ላይ በአካል በመገኘት ምልከታም አድርገዋል::
ኮሌጁ በEASE ፕሮጀክት ባሳየው የላቀ አፈፃፀም መደነቃቸውን የገለፁት በዓለም ባንክ የEASE ፕሮጀክት የሥራ ቡድን መሪ የሆኑት አና ኦሌፊር (Anna Olefir) ሲሆኑ አክለውም ኮሌጁ አሁን ያለበት የአፈፃፀም ደረጃ አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባው በመግለፅ በቀጣይ ትኩረት ይሻሉ ያሏቸውንም ጉዳዮች አመላክተዋል::
በኢፌዲሪ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኢንስቲትዩት የሥልጠና እና አቅም ግንባታ ምክትል ዋና ዳይሬክተር እና በሀገር አቀፍ የEASE ፕሮጀክት ዋና አስተባባሪ ሀፍቶም ገ/እግዚአብሔር (ዶ/ር) በበኩላቸው የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የEASE (Education and Skills for Employability) ፕሮጀክት በኮሌጁ ትግበራውን ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ በሁሉም መመዘኛ የተሻለ አፈፃፀም እያሳየ የመጣ ተቋም መሆኑን አስታውሰው ለዚህ ውጤት መገኘት የኮሌጁ አመራሮች እንዲሁም በኮሌጁ የሚገኙ የፕሮጀክቱ አስተባባሪና ባለሙያዎች ያሳዩት ቁርጠኝነትና በቅንጅት የመስራት አቅም መሆኑንም ገልፀዋል::
የEASE ፕሮጀክት ከአለም ባንክ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ በሀገሪቱ በሚገኙ 24 ኮሌጆች በመተግበር ላይ የሚገኝ ፕሮጀክት ነው::
ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት አማራጮች ያግኙ፡-
በፌስቡክ -https://www.facebook.com/share/19wDiZAD7x/?mibextid=wwXIfr
በቴሌግራም -https://t.me/EIPC2001
በቲክቶክ -https://www.tiktok.com/@ethioitaly2001?_t=ZM-90MxIrBN8qe&_r=1
በዌብሳይት - https://ethioitalypolytechniccollege.com/
