uz
Feedback
ወርቃማ ምክሮች

ወርቃማ ምክሮች

Kanalga Telegram’da o‘tish

የተለየዩ አስተማሪ ታሪኮች ፣ወርቃማ ምክሮች የስኬታማ ሰዎች ልምድ፣ የተለያዩ መጣጥፎች የሚቀርቡበት ቻናል ነው ‼️ ☞https://t.me/eross_eross ▮Share and Join

Ko'proq ko'rsatish
2 765
Obunachilar
-224 soatlar
-177 kunlar
-6730 kunlar
Postlar arxiv
•.¸♡ ሁለት ግን አንድ ፣አንድ ግን ሁለት ♡¸.• አሏህ( ሱብሃነሁ ታአሏህ) ለሰው ልጅ ሁለት አይኖችን ሰጠ። ብዙዎች ግን የሚጠቀሙት አንድ ዓይናቸውን ነው ። አንድ ምላስና ሁለት ጆሮዎችንም ሰጣቸ
•.¸♡ ሁለት ግን አንድ ፣አንድ ግን ሁለት ♡¸.• አሏህ( ሱብሃነሁ ታአሏህ) ለሰው ልጅ ሁለት አይኖችን ሰጠ። ብዙዎች ግን የሚጠቀሙት አንድ ዓይናቸውን ነው ። አንድ ምላስና ሁለት ጆሮዎችንም ሰጣቸው ፤ ብዙዎች የሚጠቀሙት ግን ሁለት ምላሰ አንድ ጆሮ ነው።ሁለት እጅም ሰጣቸው ብዙዎች የሚጠቀሙት አንዱን ብቻ ነው። ሁለት እግርም ሰጣቸው ብዙዎች አንድ እግራቸውን ብቻ ነው ፋይዳ ላይ ያዋሉት ። እንዴት ለሚለው ምላሹ የሚከተለውን ነው _ብዙዎች በተሰጣቸው ዓይን ላይ እላይን እንጂ ትክክለኛ ትርጉምን ጠልቀው አይመለከቱም ። _ብዙ ከማዳመጥ ይልቅ ብዙ ያወራሉ ። _በእጃቸው በርካቶች ለመቀበል እንጂ ለመስጠት አልታደሉም ። _በእግራቸውም ወደ መጥፎ እንጂ ወደ መልካም ነገር በብዛት አይሄዱም። ለአንተም በርሱ እውቀት የሌለህን ነገር አትከተል ። መስሚያም ፣ማያም፣ልቦናም እነዚህ ሁሉ (በእለት ትንሣኤ በድርጊታቸው )ተጠያቂዎች ናቸው ። ❮አል _ኢስራእ:36❯ መልካም ቀን ተመኝሁ https://t.me/eross_eross

#ፈገግታም #ቁምነገርም አንድ ሰውዬ በውኃ ጉድጓድ አጠገብ ተቀምጣ ወደነበረች አንዲት ሴት ቀርቦ እንዲህ ሲል ጠየቃት፦“የሴቶች ብልህነት ምንድን ነው?” እሷም ይህንን ስትሰማ ከጉድጓዱ አጠገብ በመቆም የሰፈሯ ሰዎች እንዲሰሟት ጮክ ብላ ማልቀስ ጀመረች። ሰውዬው በመደናገጥ፡- “ፈርተሽኝ ነው? ለምን ፈራሽኝ እኔ እኮ ምንም ላደርግሽ አይደለም!።” እሷም፡- “የመንደሩ ሰዎች እንደሚመጡ ስላወቅክ እንጂ ልትጎዳኝና ልትገድለኝ ነበር” ሰውዬውም፦ “አንቺን ለመጉዳት ወደዚህ አልመጣሁም ነገር ግን ብልህነትሽን አይቻለሁና ጠየቅኩሽ። እና ካንቺ ጋር ለመነጋገር ያለኝ ፍላጎት ከመጥፎ እምነት የመነጨ አይደለም ምክንያቱም ቆንጆ ሴት ነሽ” ልጅቷ የሰውዬውን ንግግር ስትሰማ። ከጉርጓዱ አጠገብ የነበረውን የውሃ ባልዲ በማንሳት በራሷ ላይ አፈሰሰችው። ሰውዬው በልጅቷ ተግባር ተደንቆ ጠየቃት፡-“ለምንድነው ይህን ያደረግሽው?” ንግግሩን ሳይጨርስ ጩኸቱን የሰሙት የመንደሩ ሰዎች በአጠገባቸው ተሰበሰቡ። ልጅቷም የፈጠነ፡- “ጉርጓድ ውስጥ ወድቄ ነበር እና ይህ ሰውዬ ነው ያዳነኝ” አለቻቸው። ሰዎቹም በደሰታ እንደጀግና አመስግነው ሸለሙት። ከሄዱ በኋላ ጠየቃት፦“ከተግባርሽ በስተጀርባ ያለው ጥበብ ምንድን ነው?” እሳም መለሰች:- ሴቶች እንደዚህ ናቸው። ከጎዳሀት ትገድልሀለች!፤ ብታስደስታት ግን የበለጠ ደስ ታሰኝሃለች። copied ወንዶች ጠንቀቅ በሉ👇 👉@eross_eross

ትዳሬ ለምን ዘገየ!? አውቃለሁ፤ አንዳንድ ጊዜ የጥበቃው ሰዓት ሲረዝም፣ በዙሪያሽ ያሉ እኩዮችሽ የራሳቸውን ጎጆ ሲቀልሱ ስታይ፣ ልብሽ ውስጥ የሚፈጠረውን ስሜት አላህ ያውቃል። ነገር ግን አንድ ነገር ልንገርሽ፤ የዘገየው ነገር ሁሉ የቀረ አይደለም፤ የዘገየው አላህ ባንቺ ልክ፣ ለልብሽ በሚመጥንና ለአኺራሽ በሚበጅ መልኩ እያሰናዳው ስለሆነ ነው። ይፍጠንም ይዘግይ፤ እርግጠኛ ነኝ ያሰብሽው ዓይነት፣ በሱጁድ ወርደሽ ያለቀስሽለት ዓይነት፣ «ጌታዬ ሆይ እንዲህ ያለውን ስጠኝ» ብለሽ የተመኘሽው ዓይነት አጋር አላህ ይሰጥሻል። የጌታሽ ካዝና አይጎድልም፤ ጊዜው ሲደርስ "ሁን" ይለዋል፤ ይሆናል። ውድ እህቴ... ዐይንሽን ከአላህ ላይ አትንቀይ። የልብሽን መልሕቅ በረብሽ ላይ ጣይው።  የዘገየው ባንቺ ላይ ካለው ክፋት ሳይሆን፣ ለአንቺ ካለው የእዝነት ጥበብ የተነሳ ነው። ስለዚህ መልካም ጥርጣሬሽን ንፋስ አይግባው። «ለምን ዘገየ?» የሚለው የሸይጧን ሹክሹክታ ኢማንሽን፣ ተወኩልሽንና ያቂንሽን  እንዲፈታተነው አትፍቀጂ። ያ የለመንሽው ዱዓ አየር ላይ አልቀረም፤ አላህ እየሰማሽ ነው።  አሁንም በፊት እንደምታስቢው፣ በፊት እንደምትመኚው አድርገሽ አስቢ። ተስፋሽን አዳብሪ። አላህ ነገ በተባረከ ትዳር፣ የዲን መሰረት ባለው ቤተሰብ፣ በሱና በደመቀች ጎጆ እንደሚክስሽ አስቢ። የአላህ ውሳኔ ሁሌም ከምኞታችን በላይ ውብ ነው። ትዕግስትሽ ጣፋጭ ነው፤ ፍሬውም ያማረ ይሆናል። አንቺ ብቻ ከደጃፉ አትጥፊ፤ ዱዓሽን አታቋርጪ። ያሰብሽውን፣ የተመኘሽውን፣ ለዱኒያም ለአኺራሽም የሚሆነውን የልብ ወዳጅ አላህ በቅርቡ ያምጣልሽ። አላህ የልብሽን መሻት ያሳካ፤ ሷሊህ የሆኑ ልጆች አባት ከሆነ ምርጥ ባሪያው ጋር ያጣምርሽ። አሚን! @eross_eross

  የህይወት እይታ ባህሪህን እወቅ በመንገድ ላይ ሲጓዝ የነበረ አንድ ሰውዬ መርዛማ የሆነ እባብ በእሳት ሲቃጠል ተመለከተና ከእሳቱ ውስጥ ሊያወጣው ወሰነ። ከእሳቱ ውስጥ ሊያወጣ ሲያነሳው እባቡ እጁ ላይ ነደፈው። ሰውዬው በድንጋጤ እባቡን ወረወረው እባቡም ተመልሶ እሳቱ ውስጥ ወደቀ። ሰውዬውም በድጋሚ ሁለት እንጨቶችን ተጠቅሞ ከእሳቱ አወጣው። እናም የእባቡ ሕይወት ተረፈ። ቆሞ ድርጊቱን ይመለከት የነበረ አንድ ሰው ወደ ሰውየው ቀርቦ "ይህ እባብ በመርዙ ነድፎህ ሳለ ድጋሚ ልታድነው የምትሞከረው ለምንድነው?" ብሎ ጠየቀው። ሰውየውም "የእባቡ ባህሪ መንደፍ ነው የእኔ ደሞ ማትረፍ ነው። ሁለታችንም ያለንን ነው ያንፀባረቅነው። ለሱ ክፉ ባህሪ ብዬ የኔን መልካም ባህሪ መለወጥ የለብኝም" ብሎ መለሰ። ክፉ ነገር በክፉ ሊመለስ አይገባም። መጥፎ ሰዎች በዙሪያህ ቢኖሩም፣ የቱንም ያህል ክፋት ቢሰሩብህ አንተ የራስህን መልካም ብህሪ አንፀባርቅ እንጂ በነሱ ውስጥ አትዋት።አንድ ቀን ከዚህ ስራቸው ታድናቸዋለህ። ሀል ጊዜም እራስህን ሁን!!!! የእውነት የሰውኛ ባህሪያችን ምንድነው?እየሆንን ያለውስ.? @eross_eross

ስለ ንፅህና ስናወራ… እድፍ ውስጥ የነበርን  እንደሆነ የምታስቡ… ስለ መለያየት ስንፅፍ…  ክህደት ተፈፅሞብን የእንባ ዓለማችንን እያስተጋባን የሚመስላችሁ… ስለ ፍቅር ስናስረዳ… ልባችን በፆታዊ ፍቅር የተነደፈ እንደሆነ የምትደመድሙ… ይህንንም አንብቡልኝ…  እዚህ የተፃፈ ሁሉ አልተኖረም… የተኖረው ሁሉም አይፃፍም እሺ… ያየነውንም ፣ የሰማነውንም በአንድ ሜዳ ለማጋራት ያህል ነው…  ከዚህ ውጪ ታድያ ምን እንፃፍላችሁ??… 👉t.me/eross_eross

🔺ቀሲዳ *☝️ أتُعلنُ حرباً أيا مُسلماً ..* *🎙️ نشيد عن المعاصي* 👉@eross_eross

የፍቅር ጥግ ስለ ፍቅር ከተነገረው ትልቁ አቡበክር ምን አስለቀሰህ ተባለ እርሱም፡- የአላህን መልእክተኛን እያለቀሱ አየሁ እኔም አለቀስኩ https://t.me/eross_eross
የፍቅር ጥግ ስለ ፍቅር ከተነገረው ትልቁ አቡበክር ምን አስለቀሰህ ተባለ እርሱም፡- የአላህን መልእክተኛን እያለቀሱ አየሁ እኔም አለቀስኩ https://t.me/eross_eross

↬የምትወደውን ሰው ማጣት ህመም አለው በጣም! ከዚሁ ሱራ ውስጥ ከምናገኛቸው ነገሮችመካከል  የዩሱፍ አባት በሱፍ ሀዘን ግሎ ሳይጨርስ ሌላ ዱብዳ ለሁለተኛ ጊዜ ሌላ የልጅ ማጣት መጣበት  ካአለው አሏህ ላይ ተወኩልም ጋ አሏህ ካሳወቀው ጥበብም ጋ  ስሞታው ወዳአሏህ ከመመለሱጋ ከወዳጅ ቹ መለያየት ሀዘኑ በጣም ጥልቅ ስለሆነ የአይን ብርሃን እስከማጣት ደረሰ … ( وتَوَلَّىٰ عَنْهُمْ وَقَالَ يَٰٓأَسَفَىٰ عَلَىٰ يُوسُفَ وَٱبْيَضَّتْ عَيْنَاهُ مِنَ ٱلْحُزْنِ فَهُوَ كَظِيمٌۭ ) " ከእነሱም ዘወር አለና ኣ«በዩሱፍ ላይ ዋ ሐዘኔ!» አለ ፡፡ ዓይኖቹም ከሐዘን (ለቅሶ) የተነሳ ነጡ ፡፡ እርሱም በትካዜ የተሞላ ነው ፡፡"  ዩሱፍ 84 አዎን የምትወደውን ሰው ስታጣ ህመም አለው!!!!! 👉@eross_eross

Ovozli xabar01:39

ሸይኽ_ሷሊህ_አልፈውዛን ሐፊዞሁሏህ እንዲህ ይላሉ : - «አግብተህ፣ ነፍስህን (ከዝሙት) መጠበቅህ፣ ሴቲቱንም እንዲሁ መጠበቅህ እና ዝርያዎችንም መተካትህ ትርፍ ዒባዳዎችን ለመፈፀም ለብቻህ ከመገለልህ
ሸይኽ_ሷሊህ_አልፈውዛን ሐፊዞሁሏህ እንዲህ ይላሉ : - «አግብተህ፣ ነፍስህን (ከዝሙት) መጠበቅህ፣ ሴቲቱንም እንዲሁ መጠበቅህ እና ዝርያዎችንም መተካትህ ትርፍ ዒባዳዎችን ለመፈፀም ለብቻህ ከመገለልህ የበለጠ ነው። @eross_eross

የዛሬው ጠቅላላ እውቀት 💥 ስለ መውሊድ ትክክል ያልሆነው የቱ ነው።
Anonymous voting

፣ والله ከባድ ገፍላ ላይ እኮ ነው ያለነው ውዶች ጨልሞብናል ማለት ይቻላል ያረበና መጨረሻችን አሳምርልን https://t.me/eross_eross

•.,¸¸,.•´¯ ስለ ቀልበችን ክፍል ❻ ¯•.,¸¸,.•´ ❹ ቀልቡን ወጂል ፦ ለሰራችው መልካም ስራ አሏህ ተቀብሎኝ ይሆን በማለት የምትሰጋ ቀልብ ፦ (አሏህ ሱብሃነሁ ታዕሏህ) እንዲህ ይለናል ፦ እ
•.,¸¸,.•´¯ ስለ ቀልበችን ክፍል ❻ ¯•.,¸¸,.•´ ❹ ቀልቡን ወጂል ፦ ለሰራችው መልካም ስራ አሏህ ተቀብሎኝ ይሆን በማለት የምትሰጋ ቀልብ ፦ (አሏህ ሱብሃነሁ ታዕሏህ) እንዲህ ይለናል ፦ እንዚያ ከሰጠናቸው (ሲሳይ)የሚመጸውቱ ሲሆኑ (ቀልባቸው)ልባቸው (አይቀበለንምይሆን በማለት) የሚፈሩ ናቸው እንሱም ወደ ጌታቸው ተመላሾች ናቸው ። (አል _ሙእሚኑን:60) አማኞች ሆነው ንፁህ ቀለብ ያላቸው ሰዎች ጌታቸው ያዘዛቸውን አምልኮት በሚገባ ከፈጸሙ በኋላ ይህ አምልኮዬ ጌታዬ እንደሚፈልገው ሆኖ ይቀበለኝ ይሆን ??? የሚል ስጋት ያድርባቸዋል እንጂ እንደ እኔ ማን ለጌታው ተገዢ ፣ታዣዥ አለ በማለት አይመፃደቁም ። ይህ ተግባር ደግሞ የቀልብ ንጹህነትንና የኢማን ጥንካሬን ያንጸባርቃል ። _________________________ {[ይቀጥላል }} ኢባዳችሁ ተቀባይነት ያለው ምሸት አሏህ ያድርግልን ያረብ https://t.me/eross_eross

🤩ባለ ተሰጥኦዎች የታላቹ🤩 አሰላሙ አለይኩም እንዴት ናቹ ውድ የተከበራቹ የቻናል ሜምበሮች ዛሬ አዲስ ነገር ይዘንላቹ መተናል የግጥም ውድድር ልናደርግ ነው ሽልማቱም የሚሆነው አንደኛ ለወጣ......150 ብር ካርድ 🤩 ሁለትኛ ለወጣ.....100 ብር ካርድ🤩 ሶስተኛ ለወጣ..... 50 ብር ካርድ 🤩 ግጥሙ <ስለ ቁርዓን አጠር መጠን ያለ >ብቻ እና ብቻ መሆን አለበት። አሸናፊው የሚሆነው በላይክ ብዛት ይሆናል። ውድድሩ ለሶስት ቀን የሚቆይ ሲሆን ከአሁን  ሰአት ጀምሮ  እስከ ሶስት ቀን መላክ ትችላላቹ😊 ማስጠንቀቂያ ❗️ copy right ማረግ በፍፁም ያተከለከለ ነው።ባለ ትክክለኛ ተስጥኦዎች ብቻ ይወዳደሩ። ውድድሩ የሚሆነው ወርቃማ ምክሮች ቻናል ላይ ነው። ግጥሙን በዚ ይላኩ 👉@eross_63 መልካም እድል ሼር አርጉ @eross_eross

#አኩራፊ_ሰው_ብዙ_ነገር_ያመልጠዋል ባል እና ሚስቱ በመሀላቸው ግጭት ተፈጥሮ አይነጋገሩም፡፡ ሁለቱም በረጅም ትዝታ ተውጠዋል፡፡ መጀመሪያ ማውራት ሽንፈት መስሎ ስለታያቸው ሳይነጋገሩ መተኛ ሰዓታቸው ደረሰ፡፡ ድንገት ግን ባል የሆነ ነገር ትዝ አለው፡፡ ነገ በጠዋት የስራ ስብሰባ ለመታደም ወደ ሌላ ሀገር ለመሄድ በረራ አለው፡፡ ሁሌ ደሞ ወደ ስራ ሲሄድ እንቅልፋም በመሆኑ የምትቀሰቅሰው ሚስቱ ናት፡፡ እናም የነገው ስበሰባ እንዳያመልጠው ለሚስቱ "11 ሰዓት ቀስቅሽኝ" ብሎ በአፉ መናገር ሞት መስሎ ታየው፡፡ እና ወረቀት ላይ "ነገ የስራ ስብሰባ ስላለበኝ ወደ ሌላ ሀገር እበራለው፡፡ አደራ 11 ሰዓት ቀስቅሽኝ" ብሎ በወረቀት ፅፎ እሷ የምታየው ቦታ አስቀምጦላት ምንም ቃል ሳይተነፍስ ተኛ፡፡ ጠዋት ሰውየው ከእንቅልፉ ሲነቃ ከጠዋቱ 3ሰዓት ሆኖ በረራውም ስብሰባውም አምልጦታል፡፡ "እንዴት እንደዛ አስጠንቅቄ ነግሪያት አትቀሰቅሰኝም?" ብሎ በጣም ተበሳጨ፡፡ ከአልጋው ለመነሳት ሲሞክር አንድ ወረቀት ኮመዲኖ ላይ ተቀምጦ አየ፡፡ "11 ሰዓት ሆኗል ተነስ ስብሰባ እንዳያመልጥህ" የሚል ፁፍ ተፅፎበታል፡፡ ✍️ማነው ስህተት የሰራው? ማነው ልክ? ወዳጄ ሴትን ልጅ በተንኮልም ሆነ በፍቅር ልትበልጣት አትችልም፡፡ ዝምታ ደሞ መቼም መፍትሔ ሁኖ አያውቅም፡፡ https://t.me/eross_eross

ይህ ዘመን የፊትና ነው። አንድ ሰው ወደ መጥፎ ነገር ባይሄድ እንኮን መጥፎ ነገር ወደሱ መምጣቱ አይቀርም በስልካችንም በወሬም በተለያዩ ነገር። ብዙ ሰው እያየሁ ነው በሶሻል ሚዲያው ላይ ሰዎች በተፈ
ይህ ዘመን የፊትና ነው። አንድ ሰው ወደ መጥፎ ነገር ባይሄድ እንኮን መጥፎ ነገር ወደሱ መምጣቱ አይቀርም በስልካችንም በወሬም በተለያዩ ነገር። ብዙ ሰው እያየሁ ነው በሶሻል ሚዲያው ላይ ሰዎች በተፈተኑበት ላይ በየኮመንቱ እየገባን እኔ ኮሜንት ላነብ ነው የመጣሁት እንላለን ፣ ብዙ ያልተገቡ ቦታው ለኛ የማይመጥነን ቦታ ላይ እየገባን ማንቆሸሽ አቢድ አቢድ ያደርገናል። ይህ ለነፍሳችን ካሰብን ሰዎች በተፈተኑበት ስላልተፈተንን አላህን አመስግነን ብናልፍ የተሻለ ነው። ልባችን በአላህ እጅ ነው እንደፈለገ ይገለባብጠዋል። እናም ይህን ዱኣ ማድረግም አንርሳ ​"يا مقلب القلوب ثبت قلبي على دينك" (ያ ሙቀልበል ቁሉብ ሰቢት ቀልቢ አላ ዲኒክ)ያ ሙቀልበል ቁሉብ፦ "አንተ ልቦችን ገለባባጭ የሆንክ ጌታ ሆይ" ​ሰቢት ቀልቢ አላ ዲኒክ፦ "ልቤን በሃይማኖትህ (በቀጥተኛው መንገድ) ላይ አጽናልኝ"👇👇 👉@eross_eross

አታመንታ! ቁጭ ብለህ እንዲህ ባደርግ እንዲህ ቢሆን አትበል! አድርገው! ወደ ተግባር ግባ! ወዳጄ ባህሩ ላይ ማፍጠጥ አያሻግርህም ተነስተህ ጀልባውን መቅዘፍ አለብህ። ከአልጋህ ተነስ፣ ለዲንህ ስራ፣ መፅሀፉን አንብብ፣ በጊዜህ ወደ ስራህ ግባ ፤ ወዳጄ የተግባር ሰው ካልሆንክ በሀሳብ መንሳፈፍ ነው ስራህ! ዳይ ተነስ! @eross_eross

~ ምናልባትም "እድል"… በምናገኛቸው ውብ ነገሮች አይለካም… ባልደረሱብን መጥፎ ነገሮች እንጂ… ጤናህን አቅልለህ አትመልከት… ለመተንፈስ ሌላ መሳሪያ ሚፈልጉ፣ መመልከት የማይችሉና አልጋ ላይ አመታት
~ ምናልባትም "እድል"… በምናገኛቸው ውብ ነገሮች አይለካም… ባልደረሱብን  መጥፎ ነገሮች እንጂ… ጤናህን አቅልለህ አትመልከት… ለመተንፈስ ሌላ መሳሪያ ሚፈልጉ፣ መመልከት የማይችሉና አልጋ ላይ አመታትን ያሳለፉ ፍጡራንም አሉ። … ምንም ባይኖርህም… እጅግ ትልቅ ፀጋ ላይ ነህ…አመስግን። 👉@eross_eross

1- ሶላት ግዴታ አይደለም የሚል አቋም ያለው 2- ሶላትን ሙሉ በሙሉ የተወ 3- ሶላት ካልሰገድክ ትገደላለህ ቢባልም ከመስገድ አሻፈረኝ ያለ ይሄ ሰው ከሀዲ ለመሆኑ ምንም ጥርጥር የለውም። ሸይኽ ሙሀመድ ዐሊ አደም አል #ኢትዮቢይ