es
Feedback
ወርቃማ ንግግሮች

ወርቃማ ንግግሮች

Ir al canal en Telegram

የተለየዩ አስተማሪ ታሪኮች ፣ወርቃማ ምክሮች የስኬታማ ሰዎች ልምድ፣ የተለያዩ መጣጥፎች የሚቀርቡበት ቻናል ነው ‼️ ☞https://t.me/eross_eross ▮Share and Join

Mostrar más
2 922
Suscriptores
-224 horas
-127 días
-4630 días
Archivo de publicaciones
የቂያማ ቀን የሚሰጥህ መፅሀፍ ደራሲው አንተ ነህ 🌱 @TewhedandSuna

ይህን አስደናቂ ፅሁፍ አንብበው ሼር ማድረግ አይዘንጉ!!! ° ✍🖊 ሙዓዊያ እና ዐሊይ ረዲየላሁ ዐንሁም አጅማኢን በተጋጩ ግዜ የሮሙ ንጉስ እንዲህ ሲል ደብዳቤ ፃፈ። 🍂 "ከሮም ንጉሰ ነገስት ለ ሙስሊሞች መሪ ሙዐዊያ አቡ ሱፍያን!! ባንተ እና በዐሊይ መካከል የተከሰተውን ግጭት ሰምተናል።ስለዚህም ለሙስሊሞች መሪ አንተ መሆን እንዳለብህም ስለምናምን አንተ ፍቃድህ ከሆነ የዐሊይን ጭንቅላት ቀንጥሶ የሚያመጣልህን ወታደር ልላክልህ።" 👉 ይህ ደብዳቤ ሙዐዊያ ጋር እንደደረሰም ሙዓዊያም ➖ "ከሙዓዊያ ለሮም መሪ!!! ሁለት ወንድማማቾች ስለተጣሉ አንተ ምን አገባህ? አፍህን የማትዘጋ ከሆነ ጅማሬው እኔ ጋ የሆነ እና ፍፃሜው አንተ ጋ የሆነ ሰራዊት ልኬ አንገትህን በማስቀንጠስ ለዐሊይ በስጦታ መልኩ አበረክትለታለሁ።" #ይህ_ትክክለኛ_ሙስሊሞች_ሳለን_ነው ___________________ 🍁 ካሊድ ኢብን ወሊድ ለፐርሺያው ንጉሰ ነገስት እንዲህ ሲል ደብዳቤ ፃፈለት "ስለም ትድናለህ። እንቢ ያልክ እንደሆን ግን፤ እናንተ ህይወትን የምትወዱትን ያህል ሞትን የሚወዱ ሰራዊቶችን ይዤልህ እመጣለሁ።" ንጉሱ ይህን ደብዳቤ ካነበበ በኋላ የቻይናውን ንጉስ የጦር እርዳታ ሊለምነው ደብዳቤ ፃፈለት። ➖ የቻይናውም ንጉስ እንዲህ ሲል ደብዳቤ መልሶ ላከለት። "ንጉስ ሆይ! ተራራን እንኳን ለመናድ ካሰቡ ምንም ከማያግዳቸው ወታደሮች ጋር ለመጋፈጥ አቅሙ ስለሌለኝ ጥያቄህን መፈፀም አልችልም።" #ምን_ያህል_ሀያላን_እንደነበርን_ተመልከቱ ___________________ 🍃 በደውለቱል ዑስማኒያ የአገዛዝ ዘመን የሙስሊም ወታደሮች የጦር መርከቦቻቸውን ይዘው በአውሮፓ ደሴቶች ሲያልፉ በአከባቢው ያሉ አብያተ ክርስትያናት በሙሉ ሙስሊሞች መጥተው ፈትህ እንዳያደርጉ በመፍራት ከበሮ ከመምታት እና ምንም አይነት ድምፅ ከማሰማት ይቆጠቡ ነበር። #ያኔ_ጀግና_ሳለን ___________________ 🍁 በደውለቱል ኡስማኒያ የአገዛዝ ዘመን በያንዳንዴ ቤት ደጅ ላይ ሁለት የበር ማንኳኩያዎች ይኖራሉ። አንዱ ትልቅ ሲሆን አንዱ ትንሽ ነው። በትልቀኛው ከተንኳኳ አንኳኪው ወንድ ነው'ና በሩን ሊከፍት ሚመጣው ወንድ ይሆናል። ነገር ግን በትንሸኛዋ ከተንኳኳ አንኳኪዋ ሴት መሆኗ ስለሚታወቅ ሴት ትከፍትላታለች። ➖ በዚያ ምርጥ ዘመን አንድ ቤት ውስጥ ሰው ከታመመ ደጅ ላይ ቀይ አበባ ይንጠለጠል ነበር። ያን አበባ የተመለከቱ ሰዎች ሁሉ እዝያ ቤት በሽተኛ መኖሩን ስለሚያውቁ በበሩ ሲያልፉ ድምፃቸውን ዝቅ ያደርጉ ነበር። #ሹፍ_ምን_እንመስል_እንደነበር!!! ____________________ 🍁 ግዜው ሰላሁዲን አል አዩቢ በይተል መቅዲስን ባስመለሰበት ግዜ ነበር። እና ጦርነቱ ነገውን ሊጀመር ማታ ላይ የጦር መሪው ሰላሁዲን የወታደሮቹን ድንኳን እየዞረ ሲያዳምጥ፤ ግማሹ ለይል ይሰግዳል፣ ሌላው ቁርአን ይቀራል፣ የተቀሩት ደግሞ ይዘክራሉ። ➖ ግን ድንገት በሆነ ድንኳን አጠገብ ሲያልፍ በድንኳኑ ውስጥ ያሉት ሁሉም ተኝተው ነበር። ይህን ግዜ፦"በዚህች ድንኳን አዳሪዎች ምክንያት ልንሸነፍ እንችላለን" ብሎ አለፈ። ___________________ 🍂 ቀደምት ዑለማኦች በሶስት ነገራት አደራ ይባባሉ ነበር። 1፦ሰውዬው በሱ እና በአላህ መካከል ያለውን ግንኙነት ካሳመረ፤ በሱ እና በሌሎች መካከል ያለው ግንኙነት ያምርለታል። 2፦ሰውዬው ሚስጥራዊ ተግባሩን ካሳመረ አላህ ይፋዊ ተግባሩን ያሳምርለታል። 3፦ሰውዬው የአኪራው ጉዳይ ካስጨነቀው አላህ የዱንያውንም የአኪራውንም ጉዳይ ያግራራለታል። ____________________ #ትልቁ_ኪሳራ_ማለት_ይህ_ነው ጀነት ስፋቷ የምድርን እና የሰማያትን ያህል ሁና ላንተ በሷ ቦታ ሳይኖርህ ሲቀር...ትልቅ ኪሳራ ነው። በእለታዊ ፕሮግራምህ ውስጥ ቁርአንን መቅራት ካልተካተተ ወላሂ ትልቅ ኪሳራ ነው። ▼ ሼር https://t.me/eross_eross

an_najm_swr_lnjm_qari_ibrahim_abdella_ekpqfo8wsgy_f97a3aba.m4a7.03 MB

~ ፍቅር እና ደስታ ሕይወታችንን የገነቡ ቁርጭራጨ ነገሮች በርካታ ናቸው፡፡ የሰበሩን አጋጣሚዎች ፣ ከፍ ያደረጉን እና መስመር በማስያዝ የቀረፁን ሁነቶች ፣ የወሰንናቸው ወይም ሳንወስን የተውናቸው ውሳኔዎች፣ ወደ ህይወታችን የገቡና የወጡ እስከመጨረሻው ድረስም እንድንቀየር ያደረጉን ሰዎች፣ የወደድናቸው፣ የጎዱን ወይም የተዉን ሰዎች እነኚህ ሁሉ በሕይወታችን ግንባታ ዉስጥ ሚና አላቸው፡፡ አንዳንድ ጊዜ እነኚህን ቁርጭራጮች አናስተውልም፤ ወይም ብናስተውልም ልብ አንላቸዉም፣ ትኩረት አንሰጣቸዉም፡፡ ጊዜ ሄዶ፣ ነገሮች አልፈው መለስ ብለን ስናያቸው ብቻ ድንገት መላ ሕይወታችን በእንቆቅልሽ መልኩ የተቀረፀ መስሎ ይታየናል፡፡ በእርግጥ እነኚህን የሕይወት እንቆቅልሾች አትፍሯቸው፡፡ የህይወታችን አካል መሆናቸዉንም ዉደዱ። በርግጠኝነት ፍጹም በሆነ መልኩ ይስማማችኋል። የሚያስፈልጓችሁ ናቸው፡፡ ለምን አትሉኝም? የሠራችሁ እና በዚህ መልኩ የቀረፃችሁ ቀራፂ ፍፁም የሆነ አምላክ ነውና፡፡ አሳዛኙ ነገርህ ... ዉስጥህን ባሳዘነህና ምቾት በነሳህ ነገር ዉስጥ ምቾት የምታገኝ መሆኑን መርሳትህ ነው፡፡ ምክንያቱም ይህ የታወቀ ጉዳይ ነው፡፡ ህመም ሰላም ነው፤ አደጋ የለውም፡፡ (ከሰላም ወደ ችግር ከመግባት ይልቅ ከችግር ወደ ሰላም መምጣቱ ይመረጣል፡፡ ህመምና ችግር ላይ የነበረ ሰው ሁኔታው ወደ ጤና እና ድሎት ቢሸጋገር አተረፈ እንጂ አልተጎዳም፡፡ ያጣው ነገር የለምና፡፡ ተቃራኒው በሆነ ጊዜ ግን ጉዳቱ ከባድ ነው የሚሆነው፡፡ ለዚህም ነው ህመም ሰላም ነው፤ ጤና ግን አደጋ አለው የተባለው፡፡) ፍቅር ፣ ደስታና ነፃነት ግን አደጋ አላቸው፡፡ ምክንያቱም በሆነ ጊዜ ሊታጡ ይችላሉና፡፡ ስለለመድናቸዉም ባጣናቸው ጊዜ እንጎዳለን፡፡ ስለሆነም በደስታ ዉስጥ ከሚጠብቅህ አደጋ ይልቅ በእስር ውስጥ የሚገኘዉን ደህንነት ምረጥ፡፡ ይህን የምትመርጠውም ሁሌም የሚታወቅና የተለመደ ነገር ስለሆነ ነው፡፡ እንደዉም ላንተ ምንም ካለመሰማት ከመደንዘዝ ስሜት ይልቅ ከባዱ ህመም ነው የሚሻልህ፡፡ በዉስጡ ሰላምን ታገኝ ዘንድ፡፡ ይህ እንግዲህ ራስን የመጉዳት ትርጉሙ ነው፡፡ ስሜቱን ለመረዳት ሲባል ቆርጦ መጣል፡፡ ምክንያቱም ምንም ካለመስማትና ከመደንዘዝ ይልቅ የሆነ ነገር መስማት ይሻላልና፡፡ ራስህን መጉዳት አቁም፡፡ አላህ የሆነ ነገር ሰጥቶህ ከተቀበልከው በኋላ አመስግናለሁ አትበል፡፡ ይህ ማመስገን ሳይሆን አለማመስገን ነው፡፡ ነገር ግን አላህ የሆነ ነገር ሰጥቶህ ለመቀበል ፍቃደኛ ካልሆንክ ትልቁ አለማመስገን የሚባለው ይህ ነው፡፡ ምስጋና ቢስነት፡፡ በሆነ ነገር ላይ ፍፁም በሆነ መልኩ ሙሉ ትኩረት ከማድረግና በነገሮች ላይ ጥገኛ ከመሆን ተጠንቀቅ፡፡ እነዚያ ነገሮች ጥሩ ከሆኑ በነርሱ ላይ ትኩረት ማድረግህ እንድትኩራራና እንድትንጠባረር ያደርግሃል፡፡ መጥፎ ነገሮችን ደግሞ አግዝፈህ የተመለከትካቸው እንደሆነ ተስፋ እንድትቆርጥ ያደርጉሃል፡፡ አሳንሰህ የተመለከትካቸው እንደሆነ ደግሞ ከልክ ባለፈ ሁኔታ ችላ እንድትል ያደርጉሃል፡፡ ስለሆነም ሚዛናዊነትህን ጠብቅ:: ከዚያ ይልቅ በአላህ ላይ ትኩረት አድርግ፡፡ እሱ ባንተ ላይ ያለው ፍፁም የሆነ መብት በመልካም ሥራህ እንዳትመፃደቅ ያደርግሀል፡፡ በሠራኸው ኃጢአት እርሱ ላንተ ያለው ፍፁም የሆነ እዝነት ደግሞ ምክንያት ተስፋ እንዳትቆርጥ ያደርግሃል፡፡ ባንተ ላይ ያለውን ፍፁም ኃያልነት ስታውቅ ደግሞ ኃጢአትን ትንሽ ናት ብለህ እንዳትዳፈር ያደርግሃል፡፡ ~ በነኚህ ሦስት መርሆች መካከል ኑር፡፡ 👉@eross_eross

የአደም ልጅ ሆይ! በእናትህ ሆድ ውስጥ አኖርኩህ፤ ከማሕፀን እንዳትበረግግም ቅርፊቶችን ከፊትህ ጋረድኳቸው። የምግቦች ጠረን እንዳይረብሽህም ፊትህን ከናትህ ሆድ ወደ ጀርባዋ አዞርኩልህ። ከናትህ ሆድ ውስጥም ሁለት መደገፍያዎችን አበጀሁልህ። ለቀኝህ መደገፍያ ጉበቷን አድርጌ ለግራህ ጣፍያዋን አበጀሁልህ። መቆምንም መቀመጥንም ከእናትህ ሆድ ውስጥ ሁነሁ ገራሁህ፤ ታድያ ይሄን ከእኔ ሌላ እሚችል አለ? የመውጫህ ግዜ ሲደርስማ! መልዓኩን ልኬ ከክንፎቹ በአንዱ ላባ ቀስ አድርጎ እንዲያስወጣህ አደረግኩ። ሚያኝክ ጥርስ የለህ፣ እሚጨብጥ እጅ የለህ፣ እሚሮጥ እግር የለህ...ከእናትህ ደረት ስር በሁለት ቱቦዎች የሚፈሱ ንፁህ ወተቶችን በክረምት ሙቅ በበጋ ቀዝቃዛ አድርጌ አመነጨሁልኽ። ወላጆችህ ሳትጠግብ እንዳይጠግቡ፣ ሳትተኛ እንዳይተኙ የሚያደርግ ፍቅርህን ዘራሁባቸው። ጡንቻዎችህ ፈርጥመው ጉልበትህ የመጣ ግዜማ፤ በአመፅ ዘመትክብኝ። ጭራሽ እኔን አታፍረኝምም። ይህም ሁኖ! ስትጠራኝ እመልስሃለሁ፣ ስትለምነኝ እሰጥሀለሁ፣ ተፀፅተህ ወደኔ ብትመጣ እቀበልሃለሁ። 👉@eross_eross

ከቀረብህ የቀረልህ ይበልጣል!! በህይወት አውድ፣ በህይወት መንገድ ወደንም ሆነ ሳንወደ፣ መርጠንም ሆነ ሳንመርጥ ብዙ ነገርን እየጣልን፣ እየቀነስንና እየተውን የምንጓዝበት ግዜ ይኖራል። ከሁሉም ከሁሉም ከዕጃችን ጭብጥ አምልጦን የወጣ መመለሻውም የከበደ ሀሳብን ብቻ ያስታቀፈን ከቃል በላይ የሆነ ነገር ቀርቶብን፣ አምልጦንም ይሆናል። ነገር ግን አሁንም ለራሳችን እኛ እራሳችን ቀርተናል። አዎ! ምናልባትም አንዳንዴ የምንጥለውና የምንተውው በቅፅበታዊ ሁኔታ ባልታሰበ አጋጣሚ ሊሆን ይችላል። ከዚህም በዘለለ የነገሮች መደራረብ፣ የምርጫ መዛባት፣ ለሰው ብለን በይሉኝታ፣ የሚገባንን በሚገባ መምረጥ ባለመቻል፣ እነዲሁም ከሚያስፈልገን የምንፈልገው ላይ ማተኮራችንና ሌሎችም ምልከታወችና ተግባራት በተናጥልም ሆነ በጋራ ለተውናቸውና ለጣልናቸው ብሎም ላመለጡን ነገሮች ምክንያት ይሆኑን ይሆናል። አዎ! ይሄ የህይወት አንድ ገፅ ነው። ነገር ግን ምንም አይደለም ጀግናዬ...! Its Okay! ሁሌም ቢሆን ከቀረብህ ነገር የቀረልህ ይበልጣልና። አዎ! ጀግናዬ....! ምክንያቱም የቀረብህ ለግዜው እጅህ ላይ የለም የቀረለህ ግን በእጅህ ነው። በእርሱም ተጠቅመህ አይደለም የቀረብህን ቀርቶ ከዛም በበለጠና በተሻለ ሌላ ግዙፍና ወሳኝ ነገር የራስህ ለማድረግና ለማሳካት በሚገባ ትችላለህና። ሰናይ ምሽት ይሁንልን!! https://t.me/eross_eross

🌱 ደማቅ የዳዕዋ መድረክ ! •በኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር •በኡስታዝ ሰዓድ ጅላሉ 🗓 እሁድ ግንቦት 2/2018 🕒 ከጠዋቱ 3:30 ጀምሮ 🕌 ሙስዓብ መስጂድ 📍 አድራሻ - አለም ባንክ • ለሴቶች በ
🌱 ደማቅ  የዳዕዋ መድረክ ! •በኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር  •በኡስታዝ ሰዓድ ጅላሉ 🗓  እሁድ ግንቦት 2/2018      🕒 ከጠዋቱ 3:30  ጀምሮ 🕌 ሙስዓብ መስጂድ 📍 አድራሻ - አለም ባንክለሴቶች በቂ ቦታ አለ ! Map location - https://maps.app.goo.gl/QBQTbrq6figoZ38w5?g_st=atg

እሷ ትዳርን ትሻለች ከዛም አልፎ አግብታ ጓጆ መስርታ የሞቀ ህይወትን ታልማለች።  አንተ ግን ፍቅር ትላለህ ወዳ ይመስልሀል እንዴ ብቸኝነትን ጌጧ አድርጋ የተቀመጠችው? ልንገርህ ሁሉንም ብዬ ባልደመድምልህም ብዙ ሴትኮ ''አጓጉል ጥንድነትን ሽሽት'' እንጂ ''ከራሷ ጋር እንድትቆም ያደረጋት #ከፍቅር_ጋር_ቂመኛና ደመኛ ሆና አይደለም ከትዳር በፊት ግኑኝነት ሀይማኖቷ ስለ ከለከላት እንጂ..!ወዳ ይመስልሀል እንዴ!? እድሜዋ እየጨመረ ጊዜዋ እየበረረ ልቧ እየተሸበረ ብቸኛ የሆነችው #ታማኝ_ወንድ በማጣት ነው የውስጥ ስሜቷን እና ፍላጎቷን ሳታደምጥ ለውሳኔ አትቸኩል! ደግሞ በብዙ እህቶች የልብ ስብራት ግንባር ቀደም ተጠያቂወች እኛው ወንዶች ነን ..ከትዳር በፊት ለኛም አስፈላጊ እንዳልሆኑ እያወቅን ስሰበሩን ስያገቡ የኛን ጥፋት ወደእነርሱ እያጣበቅን ስህተታችንን ለማድበስበስ አንሞክር:: https://t.me/eross_eross

እስቲ በዚህ ቻናል ላይ የሚፖሰቱት ፖስቶች አብባችሁ እየተጠቀማችሁ ነው መልሶቻችሁ አው ከሆነ በዚህ ግለፁልን ተጠቅመነበታል ምትሉ ብቻ 👍✅

ዛሬ ጁሙዓ ነው በነቢዩ ላይ ሰለዋት እናብዛ صلى الله عليه وسلم ከጁመዓ ሱና 1⃣🌽ገላን መታጠብ 2⃣🌽 ሽቶ መቀባት 3⃣🌽ሲዋክ መጠቀም 4⃣🌽 ጥሩ ልብስ መልበስ 5⃣🌽ሱረቱል   ካህፍን መቅራት 6⃣🌽 ለጁመዓ ሶላት መሄድ 7⃣🌽በነብዩ ﷺ ላይ ሰለዋትን ማብዛት ✍.....ጆይን👇👇👇 🌹@eross_eross

በችግሮች ውስጥ ብሩህ ተስፋዎች አሉ። ቁም ነገሩ ችግሮቹን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ብሩህ የሆነውን ተስፋ ለማየት የሚያስችለንን ጥበብ መካኑ ላይ ነው። . . . ከስኒው ላይ የተደፋውን ቡና የ
በችግሮች ውስጥ ብሩህ ተስፋዎች አሉ። ቁም ነገሩ ችግሮቹን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ብሩህ የሆነውን ተስፋ ለማየት የሚያስችለንን ጥበብ መካኑ ላይ ነው። . . . ከስኒው ላይ የተደፋውን ቡና የሚያሳየውን ፎቶ በአመልካችና በአውራጣታችሁ ከግራና ቀኝ በመለጠጥ ሰፋ አድርጋችሁ (Zoom In) ተመልከቱ። . . . ምን አያችሁ ??? ወገን እንዲህ ነው ከችግሮች ውስጥ ብሩህ ተስፋዎች የሚፈልቁት። https://t.me/eross_eross . .

በአስቸጋሪ የህይወት አውሎ ንፋስ ስትላጋ ... ባንዣበበ የመከራ ደመና ሰትከበብ ... ሁሉም ነገር ከቁጥጥርህ ውጭ ወጥቶ በተቃራኒው አቅጣጫ ሲጓዝ … መሬት ከስፋቷ ጋር ስትጠብህ ... ይጠቅሙኛል ብለህ የተመካህባቸው ፍጡራን ለራሳቸው መሆን ተስኗቸው ሲርዱ ... በፍርሃት ውቅያኖስ ሰጥመህ ግራ ስትጋባ … ሐብትህ የተጋረጠብህን ብርቱ ፈተና መከላከል አቅቶት ከወረቀት ያለፈ ፋይዳ መስጠት ሳይችል ሲቀር … በተግባር የተፈተነው ዕውቀትህ ከገባህበት ማጥ ሊያወጣህ ሰንፎ ንድፈ ሃሳብ ሆኖ ሲተን …. ያኔ አይዞህ አትፍራ! ... አንድ ጥሪ ብቻ ተጣራ … ያ አላህ በል ! … ደግመህ ጥራው! ... ህይወትህን እያመሰቃቀለ የሚገኘውን የመከራ አውሎ ንፋስ “ሁን” በሚለው የትዕዛዝ ቃሉ ሊያሰክነው የሚችል አዛኝ አምላክ አለህና << ያ አላህ >> በለው … ካረገዙ ደመናዎች ሊንቧቧ ያለውን መዓት በጠራ ሰማይ ለውጦ አድማሱ የሰላም አየር እንዲሸተው ማድረግ የሚችል ፈጣሪ አለህና አሁንም << ያ አላህ በለው >> ... ከስፋቷ ጋር የጠበበችህን መሬት ለጥጦ ልብህን በማረጋጋት ላልታ ልትበጠስ ያለችውን የተስፋ ክር በመቀጠል ህይወትን የሚያደምቅ ፈጣሪ ያለህ ፍጡር ነህና << ያ አላህ በለው>> ... ደግመህ ተጣራማ ! … ጥሪህን ቀጥል! ወገኔ አትሰልች … ምላሹ ከረዘመ ችግሩ ያንተ እንጂ የፈጣሪህ እንዳልሆነ ተገንዝበህ የጥሪህን ስልት በማሻሻል ልመናህን ቀጥል። ዘዴውን ካወቅክበት መልሱ ፈጣን ነው። የመዓቱ አውሎ ንፋስ በ “ሁን” ቃሉ ፀጥ ይላል። ያንዣበበው የመከራ ደመና ይበተናል። የጠበበው ምድር ይሰፋል። ፅልመት በብርሃን ይተካል። በስጋት የታጠሩ ልቦች በደህንነት ይሞላሉ። አየሩ በሰላም ናርዶስ ይታጠናል። በረሃብ ጠኔ የሚያቃትቱ ወና አንጀቶች በጥጋብ ይሞላሉ። በሀሴት የደመቁ ህፃናት አየሩን ይቆጣጠሩታል። የአዕዋፋት ህብረ ዝማሬ ይነግሳል። ሰላም በሁሉም ጎጆ የሚዘልቅ ቤተኛ ይሆናል። . . . . አንተ ለመጣራት ያብቃህ እንጂ እርሱ ሁሌም እዝነትና ርህራሄ በተሞላበት ሁኔታ እንዲህ ይልሃል ፡- وَإِذَا سَأَلَكَ عِبَادِي عَنِّي فَإِنِّي قَرِيبٌ أُجِيبُ دَعْوَةَ الدَّاعِ إِذَا دَعَانِ فَلْيَسْتَجِيبُواْ لِي وَلْيُؤْمِنُواْ بِي لَعَلَّهُمْ يَرْشُدُونَ ( ሙሃመድ ሆይ ! ) ባሮቼ ስለ እኔ በጠየቁህ ጊዜ ተከታዩን መልዕክቴን አስተላልፍላቸው)፡- “ እኔ ቅርብ ነኝ። የለማኝን ፀሎት በለመነኝ ጊዜ እቀበለዋለሁ። ስለዚህ እነርሱም ጥሪየን ይቀበሉ። በኔ ይመኑም። ቅኑን ጎዳና ይከተሉ ዘንድ። ” . . . ከላይ የሰፈረው አንቀፅ በውስጡ ያቀፋቸውን መስፈርቶች ልብ ይሏል። የጥሪው ምላሽ የረዘመው እነዚህ ቅድመ ሁኔታዎች ባለመሟላታቸው እንጂ ጥሪውን የሚሰማ አካል ጠፍቶ አይደለም። አንዳንዴ የምትሻውን ነገር አለማግኘትህ በራሱ በጎ ምላሽ ሊሆን እንደሚችል አስብ። ስለዚህ ጥሪው ይሰማል። ለጥሪውም ምላሽ ተዘጋጅቷል። ግና ጥሪውን የሚያሰማው ፍጡር ያለ መማሪያ ቁሳቁስ ባዶ እጁን ትምህርት ቤት እንደሚጓዘው አይነት ተማሪ እንዳይሆን ..... ስንቅ ይዘህ ተጣራ ! ..... https://t.me/eross_eross

photo content

አንድ ጊዜ አንድ አባት ልጃቸውን ‹‹ተነስ ተማር ተለወጥ ተንቀሳቀስ ሂድ›› ሲሉት ልጁም ‹‹አባዬ መማሩን እማራለሁ ግን ምን እየበላሁ ልማር?›› ሲላቸው እሳቸውም ‹‹እስከዛሬ ምን እየበላህ ደነቆርክ?›› አሉት አሉ፡፡ አስተውል ለረዥም ጊዜ አንድ ቦታ የተኛ ውሀ ይሸታል! አንተም ሸተህ እንዳትደርቅ ተጠንቀቅ፤ ተንቀሳቀስ፤ በድሮ ታሪክህ አንድ ቦታ አትተኛ፤ ቀስት ካልተወረወረ አይመታም፤ ነብርም ካላባረረ አይዝም። እራስን ለውጦ በዚህ በድንቅ በሆነችው አለም ላይ ተስማምቶ ለመኖር ስታስብ በቅድሚያ ያንተ የመለወጥ ፍላጎት ከምንም በላይ አስፈላጊ ነው፡፡ አስተውል ድመት አይጥ እንድትይዝ ተብሎ ችቦ የሚያበራላት የለም፡፡ ስለሚርባት በጨለማም ቢሆን ታግላ አይጧን ይዛ መመገብ አለባት። አለዛ በየሰው ጓዳ መልከስከስና መለቃቀም ይሆናል ስራዋ፡፡ የሰው ልጅም እንዲሁ ነው እራሱን ለውጦ በትክክል ማሰብ ካልቻለ በስተቀር በትላንት ታሪኩ ወይ በነገ ምኞቱ ቢኖር ኪሳራ ፣ ኖረው በሚሞቱ ሰዎች መቅናትና ሌሎች ሃሳብ ስር መልከስከስ ይመጣል፡፡ አንተም እንዲሳካ የምትፈልገው ሃሳብ ካለህ ሃሳብህን አክብረው፤ ውደደው፤ ከልብህ ፈልገው። አስተውል የምትፈልገው ነገር የፈለከውን ያህል ትልቅ ነው፤ አስተውል ዛሬ አለማችን ላይ ያሉ ትልልቅ ግኝቶች በሙሉ የአንድ ሰው ተራ ሃሳብ ነበሩ! ግን ሃሳባቸውን አክብረውት መስዋእት ከፍለውለት ሀሳባቸውን አለም እንዲያከብረው አደረጉ። ለዚህም የለውጥ ጉዞ ያንተ ፍላጎት ከምንም በላይ አስፈላጊ ነው፡፡ ይህ እንዴት ይሆናል? አልለወጥም አትበል። ከዚህ ከ‹‹አልለወጥም›› ‹‹አይሆንም›› ሃሳብ ካልወጣህ የሚቀየር ነገር የለም፤ ምክንያቱም በጨለማ ሁሉም ቀለም ጥቁር ነው፡፡ ብዙዎች ሳይለወጡ ሞት ቀደማቸው፤ ስኬታቸውን ይዘው መቃብር ወረዱ። https://t.me/eross_eross

🔥የአይሁድ አመሰራረት እና አኗኗር 🔥አይሁዶች…… 💫መነሻቸው የት ነው? 💫አመሰራረታቸው እንዴት ነበር? 💫ከቀደምት ነብያቶች የነበራቸው ሁኔታ ምን ይመስላል? 💫ቀደምት ህዝቦች እንዴት ነበር የሚኗኗሯቸው? 💫በዐረብ ደሴት ላይ እንዴት ሰፈሩ? 💫ከነብያችንﷺ ጋ የነበራቸው ሁኔታ ምን ይመስል ነበር? 💫እኛስ ከእነርሱ ምን እንጠብቅ?             በሚል አጠቃላይ የአይሁድ አመሰራረትና አኗኗር ቁርኣን ሓዲስ ዋቢ በማድረግ የተዘጋጀ ሙሓደራ   🪑በኡስታዝ አቡ ቀታዳ ዐብደላህ ቢን ሙዘሚል    /አላህ ይጠብቀው/ https://t.me/eross_eross

አንድ እለት… ረቢእ ኢብን ሀይሰም (አላህ ይዘንለትና) እየሰገደ እያለ በዐይኖቹ ስር በሃያ ሺህ ዲርሃም የገዛውን ፈረስ ሌባ ፈትቶ ወሰደበት። እርሱ ግን ሶላቱን አቋርጦ ሌባውን በመያዝ ፈንታ ተረጋግቶ ሶላቱን መጨረስን ነበር የመረጠው። ከዚያ በኃላ የሆነውን ሁሉ ሰምተው ሊያጽናኑት ወደርሱ ለመጡ ጓደኞች እንዲህ አላቸው " ሌባውን ፈረሱን ሲወስድብኝ አይቻለሁ። ይሁን እንጂ በጊዜው ከዚህች አለም አላፊ መጠቃቀሚያ በላቀ ደስታ ላይ ነበርኩ። ስለሆነም ያንን ደስታዮን ሰውቼ ሌባውን ልይዘው አልፈቀድኩም።" በዚህ ጊዜ ባልንጀሮቹ ሌባውን መራገም ጀመሩ። እርሱ ግን "ተረጋጉ ማንም በደል አልፈፀመብኝም። ሌባው የበደለው የራሱን ነፍስ ነው። ራሱን በድሎ ለታላቅ ኪሳራ የተዳረገውን ሰው እኛ እርግማን በማውረድ የበለጠ ልንበድለው አይገባም" በማለት እንዳይራገሙ ከለከላቸው። 💚 https://t.me/eross_eross

#የምሽት ስንቅ ለቀልብዎ           አድራሻችን ቴሌግራም     𝐂𝐡𝐚𝐧𝐧𝐞𝐥👉🏿@eross_eross       𝐠𝐫up👉🏿@tewhiddd    Add ያድርጉ 𝐓𝐞𝐥𝐞𝐠𝐫𝐚𝐦