uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 533 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 368-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 174-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 533 obunachiga ega bo‘ldi.

30 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 10 ga, so‘nggi 24 soatda esa -6 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 24.86% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 16.87% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 3 862 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 620 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 9 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
EEP Communication

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 01 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 533
Obunachilar
-624 soatlar
-207 kunlar
+1030 kunlar
Postlar arxiv
photo content
+2

በዞኑ የተደረገው የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ሥርጭት 97 በመቶ ተጠናቋል ……...///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በደቡብ ኦሞ ዞን በአየር ንብረት ለውጥ ለምግብ እጥረት ለተጋለጡ አራት ወረዳዎች ያደረገው የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ሥርጭት 97 በመቶ መከናወኑን በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የደቡብ ኦሞ ዞን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አስታወቀ። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስቸኳይ ጊዜ ሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍና ሥርጭት ኮሚቴ ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የደቡብ ኦሞ ዞን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጋር በሰብዓዊ እርዳታ ሥርጭቱ ላይ በጂንካ ከተማ ውይይት አካሒዷል። በውይይቱ ላይ የሰብዓዊ እርዳታ ሥርጭቱን አፈፃፀም አስመልክቶ ገለፃ ያደረጉት በማህበሩ የደቡብ ኦሞ ዞን የአደጋ ስጋትና ቅነሳ ቡድን መሪ ወ/ሮ ባህረወሰን ወ/አረጋይ እንደተናገሩት ድጋፉ በደቡብ ኦሞ ዞን በሐመር፣ ዳሰነች፣ ኛንጋቶም እና ሰላማጎ ወረዳዎች በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ የተከሰተውን የምግብ እጥረት በጊዜያዊነት ለመቅረፍ ያለመ ነው። በአራቱም ወረዳዎች በዕቅድ ከተለዩት 1 መቶ 54 ሺህ 512 ነዋሪዎች ውስጥ 1 መቶ 50 ሺህ 134ቱ የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፉ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። በወረዳዎቹ ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዞ የተከሰተውን የምግብ እጥረት በጊዜያዊነት ለመቅረፍ ከተመረጡት 68 ቀበሌዎች ውስጥ በ67 ቀበሌዎች የሰብዓዊ እርዳታ ሥርጭቱ መከናወኑን የገለፁት ቡድን መሪዋ ቀሪው አንድ ቀበሌ በፀጥታ ችግር ምክንያት ሳይካተት መቅረቱን ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በዞኑ ያደረገው የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ማህበራዊ ኃላፊነትን ከመወጣት አንፃር ውጤታማ ሥራ መስራቱንም ጠቅሰዋል። እንደ ወ/ሮ ባህረወሰን ገለፃ የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው የዞኑ አራት ወረዳ አርብቶ አደሮች 22 ሺህ 232 ነጥብ 5 ኩንታል በቆሎ፣ 149 ሺህ 723 ሊትር ዘይት፣ 22 ሺህ 264 ነጥብ 75 ኩንታል ባቄላ እንዲሁም 2 ሺህ 392 ነጥብ 73 አልሚ ምግቦች ተሰራጭቷል። የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ከዚህ በፊት የሰብዓዊ እርዳታ ሥራዎች ተደራሽ አድርጎ በማያውቅባቸው እንደ መርሲና ባጫ ቀበሌዎች ላይ መድረስ የቻለው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባደረገው የእርዳታ ድጋፍ አማካኝነት መሆኑንም ጨምረው ተናግረዋል። የተበታተነ የሥርጭት ጣቢያ መኖር፣ የመንገድ ተደራሽነት ማነስ፣ ዝርፊያ ማጋጠሙ፣ የፀጥታ ችግር እና የተመረጡ ተጠቃሚዎች አለመገኘት በሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ሥርጭቱ ወቅት ያጋጠሙ ችግሮች መሆናቸውን ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በዞኑ ላደረገው የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ምስጋናቸውን የገለፁት ወ/ሮ ባህረወሰን በቀጣይም በርካታ ሥራዎችን በጋራ ለመስራት ማህበራቸው ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጊዜያዊ የእርዳታ ድጋፍና ሥርጭት ኮሚቴ አባላት በተመረጡት ዞኖች ማህበሩ ላከናወነው የሰብዓዊነት ተግባር ምስጋና አቅርበዋል። በዞኖቹ የተከሰተውን የምግብ እጥረት ለመቅረፍ በተደረገው የሥርጭት ሥራ ላይ የነበሩትን የግልፀኝነት፣ ከስምምነት ማዕቀፉ ጋር ተያይዞም በአተገባበሩ ላይ የታዩ ችግሮችና የመረጃ ልውውጥ ክፍተቶች መታረም እንዳለባቸው አፅዕኖት ሰጥተው አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በደቡብ ኦሞ ዞን በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ ለተከሰተው የምግብ እጥረት ከሩብ ቢሊየን ብር በላይ የሚገመት የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ማድረጉን ከዚህ በፊት መዘገባችን ይታወሳል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 10 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ከ90 በመቶ በላይ የተቋሙ ቋሚ ይዞታዎች ህጋዊ የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር አግኝተዋል ……..///….. በመላ ሀገሪቱ ከሚገኙ የተቋሙ ቋሚ ንብረቶች መካከል ከ90 በመቶ በላይ የሚሆኑት ህጋዊ የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር እንዲያገኙ መደረጉን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፋሲሊቲ መምሪያ ገለፀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ከሊል ሺፋ እንደተናገሩት አብዛኛዎቹ የተቋሙ የኃይል ማመንጫዎች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ አልነበራቸውም፡፡ ባለፉት አራት ዓመታት በተከናወኑ ጠንካራ ሥራዎች ከ145 በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ህጋዊ የይዞታ ማረጋገጫ እንዲያገኙ ተደርጓል ብለዋል፡፡ አቶ ከሊል እንደገለፁት የተቋሙን ንብረት በዘመነ መንገድ መያዝ እና መጠቀም እንዲቻል በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሪፖርት ማድረጊያ ሥርዓት ወይም በእንግሊዝኛ ምዕፃሩ IFRS መሰረት የንብረት ምዝገባ ተከናውኗል፡፡ ከኢትየጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር ያልተጠናቀቁ የንብረት ክፍፍሎችን ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን የገለፁት ዳይሬክተሩ ንብረቶቹ ለሁለቱም ተቋማት ካላቸው ጠቀሜታ አንፃር እየተመዘኑ እንዲከፋፈል በተቋማቱ የበላይ አመራሮች አቅጣጫ መሰጠቱን አብራርተዋል፡፡ በሌላ በኩል በተቋሙ ገቢ እና የአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ጫና እያሳደረ የመጣውን የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ስርቆት ለመከላከል ከክልል እስከ ቀበሌ ባሉ መዋቅሮች በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 09 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2

በፕሮጀክቱ ላይ እየተፈፀመ ያለውን ስርቆት ለመከላከል በትብብር መስራት ይገባል ……...///……... ለአዋሽ- ወልዲያ - ሀራ ገበያ የባቡር ፕሮጀክት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ እየተገነባ ባለው የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ እየተፈፀመ ያለውን ስርቆት በጋራ ለመከላከል ህብረተሰቡና የፀጥታ አካላት በትብብር እንዲሰሩ ጥሪ ቀረበ፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ፕሮግራም-2 የፕሮጀክት አስተዳደር-1 ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮናስ አባዲ እንደገለፁት ለአዋሽ- ወልዲያ - ሀራ ገበያ የባቡር ፕሮጀክት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ እየተገነባ ባለው የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ እየተፈፀመ ያለውን ስርቆት ለመከላከል በትብብር መስራት ይገባል፡፡ ሥራ አስኪያጁ በፕሮጀክቱ ላይ እየተፈፀመ ያለውን ስርቆት መከላከል በሚቻልበት መንገድ እና እና በግንባታው ላይ እያሳደረ ስለሚገኘው ተፅዕኖ ከአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ዞን ሦስት ዋና አስተዳዳሪ ጋር ውይይት አካሂደዋል። ፕሮጀክቱ እንደተጀመረ ከካሳ ክፍያና ከአንዳንድ ግለሰቦች የግል ጥቅም ፍላጎት ጋር በተያያዘ የግንባታ ሥራውን የማስተጓጎል ሁኔታ ከመስተዋሉ ውጭ የስርቆት ወንጀሎች እንዳልነበሩ ነው አቶ ዮናስ ያስታወሱት። ከዚህ በፊት ተፈጥሮ የነበረውን ችግር ከአካባቢው የሀገር ሽማግሌዎች ጋር በመመካከር መፍታት እንደተቻለ የጠቆሙት አቶ ዮናስ እየተስፋፋ የመጣውን የስርቆት ወንጀል በዚሁ አግባብ እልባት ሊሰጠው እንደሚገባም ተናግረዋል። በፕሮጀክቱ ላይ የሚፈፀሙ ስርቆቶችን ለመከላከል የአካባቢው ማህበረሰብ ከፀጥታ አካላት፣ ከሥራ ተቋራጩና ከተቋሙ ጋር በትብብር ሊሰሩ እንደሚገባ የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ የዞኑ አስተዳደር የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን በስፋት ማከናወን እንዳለበትም አስገንዝበዋል። የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዶ አሊ በበኩላቸው ለህዝቡ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን ለማከናወን አቅጣጫ ተቀምጦ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራውን በአካባቢው ተሰሚነት ያላቸው የሀገር ሽማግሌዎች ከቀጣዩ እሁድ ጥቅምት 4 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ችግሩ በስፋት በሚስተዋልባቸው ቀበሌዎች በመዘዋወር ግንዛቤ እንዲሰጡ እንደሚደረግም አረጋግጠዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 10 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

የድሬዳዋ ቁጥር 1 የማከፋፈያ ጣቢያ ለከተማዋ የኃይል አቅርቦት ቁልፍ ድርሻ እያበረከተ ነው ……..///……… የድሬዳዋ ቁጥር 1 ማከፋፈያ ጣቢያ ለከተማዋ እና በከተማዋ ለሚገኙ ፋብሪካዎች እስከ 56 ሜጋ ዋት ኃይል በማቅረብ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የጣቢያው ኃላፊ አቶ ሚካኤል አልይ ገለፁ፡፡ ኃላፊው እንደተናገሩት በ1952 ዓ.ም. ተገንብቶ እስከ 26 ሜጋ ዋት ኃይል መጠን ሲያቀርብ የቆየው ማከፋፈያ ጣቢያው የአቅም ማሳደግ ሥራ ከተከናወነለት በኋላ እስከ 56 ሜጋ ዋት ኃይል ማስተናገድ ችሏል፡፡ ይህም የድሬዳዋ ከተማና በከተማዋ የሚገኙ ኢንዱስትሪዎችን የኃይል ፍላጎትን እንዲያሟላ አቅም መፍጠሩን ተናግረዋል፡፡ በኃይል ማስተላለፊያ መስመርና በማከፋፈያ ጣቢያ ኦፕሬሽን ዘርፍ የምስራቅ 1 ሪጅን የሰብስቴሽን ጥገና ባለሙያ ግርማ ደቻሳ በበኩላቸው እንደተናገሩት የድሬዳዋ ቁጥር 3 ማከፋፈያ ጣቢያ በ1987 ከተገነባና የድሬዳዋ ቁጥር 1 ማከፋፈያ ጣቢያ አቅም ማሳደግ ከተሰራለት ከ 2008 ዓ.ም. ጀምሮ በከተማዋ በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት የማስተናገድ አቅም ተፈጥሯል፡፡ የጣቢያው አቅም ማደግ የድሬዳዋ ከተማንና የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲን የኃይል ፍላጎት በመመለስ የምስራቅ ኢትዮጵያን የኤሌክትሪክ ኔትወርክ እንዲሻሻል ማድረጉንም ባለሙያው ገልፀዋል፡፡ 23 ሠራተኞች ያሉት የድሬዳዋ ቁጥር 1 የማከፋፈያ ጣቢያ 22 ሜጋ ዋት ኃይል ለናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ እንዲሁም 34 ሜጋ ዋት ኃይል ለድሬዳዋ ከተማ በማቅረብ ላይ ይገኛል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 08 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+3