uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 695 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 017-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 152-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 695 obunachiga ega bo‘ldi.

31 Avgust, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 142 ga, so‘nggi 24 soatda esa 2 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 30.85% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 16.42% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 4 842 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 578 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 10 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
EEP Communication

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 01 Sentabr, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 695
Obunachilar
+224 soatlar
+237 kun
+14230 kun
Postlar arxiv
ስርቆት የፈጸመው ግለሰብ በ10 ዓመት ከ6 ወር ጽኑ እስራት ተቀጣ …..///…. በጌዶ - ገፈርሳ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ ስርቆት የፈጸመ ግለሰብ በ10 ዓመት
+1
ስርቆት የፈጸመው ግለሰብ በ10 ዓመት ከ6 ወር ጽኑ እስራት ተቀጣ …..///…. በጌዶ - ገፈርሳ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ ስርቆት የፈጸመ ግለሰብ በ10 ዓመት ከ6 ወር በሆነ ጽኑ እስራት እንዲቀጣ መወሰኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ አንድ ሪጅን አስታወቀ፡፡ በሪጅኑ የትራንስሚሽንና ኦፒጂ ደብሊው መስመር ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ በፍቃዱ በቀለ እንዳስታወቁት የጌዶ -ገፈርሳ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር በተደጋጋሚ ሥርቆት ከሚፈጸምባቸው መስመሮች መካከል አንዱ ነው፡፡ ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.eep.com.et/?amh-news=ስርቆት-የፈጸመው-ግለሰብ-በ10-ዓመት-ከ6-ወር-ጽ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ታህሳስ 3 ቀን 2018 ዓ.ም

#LinkedIn 𝗕𝘂𝗶𝗹𝗱𝗶𝗻𝗴 𝘁𝗵𝗲 𝗙𝘂𝘁𝘂𝗿𝗲: 𝗘𝗘𝗣 𝗦𝘁𝗿𝗲𝗻𝗴𝘁𝗵𝗲𝗻𝘀 𝗦𝘂𝗯𝘀𝘁𝗮𝘁𝗶𝗼𝗻 𝗗𝗲𝘃𝗲𝗹𝗼𝗽𝗺𝗲𝗻𝘁 𝗮𝗻𝗱 𝗚𝗿𝗶𝗱 𝗥𝗲𝗹𝗶𝗮𝗯𝗶𝗹𝗶𝘁𝘆 Ethiopian Electric Power (EEP) continues to demonstrate strong end-to-end capabilities in the development of 𝗘𝘁𝗵𝗶𝗼𝗽𝗶𝗮’𝘀 𝘁𝗿𝗮𝗻𝘀𝗺𝗶𝘀𝘀𝗶𝗼𝗻 𝗶𝗻𝗳𝗿𝗮𝘀𝘁𝗿𝘂𝗰𝘁𝘂𝗿𝗲, from project initiation and detailed design to construction, operation, and long-term maintenance Read More on LinkedIn 👇 https://surl.li/exnnla 💡 "Clean Energy for a Better Life!" Facebook | Telegram | Twitter | YouTube | TikTok | Website | LinkedIn

ፕሮጀክቱን በተያዘው በጀት ዓመት አጠናቆ አገልግሎት እንዲሰጥ ለማድረግ እየተሰራ ነው ‎…....///…….. ‌‎የደሴ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የግንባታ ሥራን በተያዘው በጀት ዓመ
+7
ፕሮጀክቱን በተያዘው በጀት ዓመት አጠናቆ አገልግሎት እንዲሰጥ ለማድረግ እየተሰራ ነው ‎…....///…….. ‌‎የደሴ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የግንባታ ሥራን በተያዘው በጀት ዓመት አጠናቆ አገልግሎት ለማስጀመር ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ። ‎ ‎ሥራ አስኪያጁ አቶ አብዲ ኪያር እንዳስታወቁት የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈፃፀም 32 በመቶ ደርሷል። ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.eep.com.et/?amh-news=ፕሮጀክቱን-በተያዘው-በጀት-ዓመት-አጠናቆ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ታህሳስ 02 ቀን 2018 ዓ.ም

በጣቢያው ትራንስፎርመር ላይ የተከናወነው የጥገና ሥራ የተቋሙን ባለሙያዎች አቅም ያሳየ ነው ‎…....///…... ‌‎በኮምቦልቻ አንድ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፊያ ጣቢያ ትራንስፎርመር ላይ
+7
በጣቢያው ትራንስፎርመር ላይ የተከናወነው የጥገና ሥራ የተቋሙን ባለሙያዎች አቅም ያሳየ ነው ‎…....///…... ‌‎በኮምቦልቻ አንድ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፊያ ጣቢያ ትራንስፎርመር ላይ የተከናወነው የጥገና ሥራ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለሙያዎችን አቅም ያሳየ መሆኑን የሰሜን ምስራቅ 1 ሪጅን አስታወቀ። ‎ ‎በሪጅኑ የኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ ዳይሬክተር ተወካይ አቶ ደስታዬ ስጦታው እንደገለፁት የጥገና ሥራው የተከናወነው ጣቢያው ካሉት ሁለት ትራንስፎርመሮች መካከል በአንደኛው ላይ የእሳት አደጋ በማጋጠሙ ምክንያት ነው። ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.eep.com.et/?amh-news=በጣቢያው-ትራንስፎርመር-ላይ-የተከናወነ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ታህሳስ 01 ቀን 2018 ዓ.ም

የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ያስፈልጋል ……///…… ከጾታ ጥቃት ነፃ የሆነ ማህበረሰብ ለመገንባት ሁሉም የመፍትሔ አካል በመሆን የኃላፊነት ደርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ፡
+8
የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ያስፈልጋል ……///…… ከጾታ ጥቃት ነፃ የሆነ ማህበረሰብ ለመገንባት ሁሉም የመፍትሔ አካል በመሆን የኃላፊነት ደርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ፡፡ ዓለም አቀፍ የፀረ ፆታ ጥቃት ቀን “ጥቃትን የማይታገስ ማህበረሰብ ለትውልድ ግንባታ" በሚል መሪ ቃል በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና መስሪያ ቤት ተከብሮ ውሏል። ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.eep.com.et/?amh-news=የሴቶችን-ሁለንተናዊ-ተሳትፎና-ተጠቃሚነ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም

የአይ ኤም ኤፍ ምክትል ዳይሬክተር የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን ጎበኙ …….///……. የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት አይ ኤም ኤፍ ምክትል ዳይሬክተር ኒጌል ክላርክ 1800 ሜጋ ዋት የማመንጨት
+6
የአይ ኤም ኤፍ ምክትል ዳይሬክተር የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን ጎበኙ …….///……. የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት አይ ኤም ኤፍ ምክትል ዳይሬክተር ኒጌል ክላርክ 1800 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለውን የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ጎበኙ፡፡ ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.eep.com.et/?amh-news=የአይ-ኤም-ኤፍ-ምክትል-ዳይሬክተር-የኮይሻ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም

#photonews የኢፌዲሪ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት እና የኢፌዲሪ ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲዔታዎችን ጨምሮ በፓን አፍሪካኒዝም እንቅስቃሴ ላይ ግንባር ቀደም ከነበሩ ቀደምት የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች ልጆችና የልጅ ልጆች እንዲሁም ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተውጣጡ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ያደረጉት ጉብኝት በምስል!! 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” ህዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+9

photo content
+9

photo content
+9

#photonews የኢፌዲሪ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት እና የኢፌዲሪ ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲዔታዎችን ጨምሮ በፓን አፍሪካኒዝም እንቅስቃሴ ላይ ግንባር ቀደም ከነበሩ ቀደምት የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች ልጆችና የልጅ ልጆች እንዲሁም ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተውጣጡ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ያደረጉት ጉብኝት በምስል!! 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” ህዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም

ግድቡ በኢትዮጵያ የቱሪዝም ሀብቶች ላይ ትልቅ እሴት የሚጨምር ነው -የቱሪዝም ሚኒስቴር …....///…….. ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ኢትዮጵያ እስካሁን ከነበሯት የቱሪዝም ሀብቶች ላይ ትልቅ እሴት የሚጨምር መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስትር ዲኤታ አስታወቁ። ሚኒስትር ዲኤታው እንደገና አበበ (ዶ/ር ) እንዳስታወቁት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ የሠንደቅ ዓላማ ፕሮጀክት እና ኢትዮጵያውያን ፅናታቸውን ያሳዩበት እንደ አፍሪካ ደግሞ ከአድዋ በኋላ ለፓን አፍሪካ ንቅናቄ ያዋጣነው ትልቅ ሀብት ነው። የህዳሴ ግድብ በቱሪዝም እሳቤ ውስጥ የሚመጡ ሁለት ነገሮችን ያሟላ መሆኑን የጠቀሱት ሚኒስትር ዲኤታው  የመጀመሪያው  ተጨባጭ የሆነና በአካል የሚታይ ሲሆን  ሁለተኛው የሚነገርለት ታሪክ ያለው መሆኑን ገልጸዋል። እንደ ሚኒስትር ዲኤታው ገለጻ  የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የፈጠረው ንጋት ሀይቅን ጨምሮ የሌሎች ደሴቶች አካላዊ ዕይታ ለኢትዮጵያ ቱሪዝም ፍሰት ትልቅ ተስፋ ይዞ መጥቷል። በተጨማሪም ግድቡን  በራሳችን ሀብት እና ልጆች  በብዙ ጫና ውስጥ ሆነን ማጠናቀቃችን ኢትዮጵያዊያን መሥራት እንደምንችል ለዓለም ያሳየንበት በመሆኑ ትርክቱ በራሱ ትልቅ የቱሪዝም መስህብ መሆኑን አስረድተዋል። ግድቡ ከቱሪዝም ባሻገር ኢንቨስትመንትን በመሳብ  ለኢትዮጵያ ብዙ ሀብት ሊያመጣ የሚችል በመሆኑ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ይህን ታሳቢ ያደረገ የሮድ ማፕ ጥናት እያከናወኑ መሆኑን ጠቁመዋል። ቱሪዝሙን ለማሳደግ በህዳሴ ግድቡ ላይ ለሚደረጉ ኢንቨስትመንቶች ሚኒስትር መስሪያ ቤታቸው ልዩ ትኩረት እንደሚሰጥም ነው ያመለከቱት። አስጎብኚ ድርጅቶች ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ሂደው በማየትና በፓኬጃቸው ውስጥ በማካተት ለዓለም ህዝብ እንዲያስተዋውቁ መንግስት ምቹ ሁኔታዎችን እንደሚፈጥር ሚኒስትር ዲኤታው አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ በርካታ የቱሪዝም ሀብቶች ያሏት ሰፊ ሃገር በመሆኗ የውጭና የሀገር ውስጥ ባለሀብቶችም ግድቡን በመጎብኘት ሀሳብ እንዲወስዱና ኢንቨስት እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+3

ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብን የገነባችው ካላት የመልማት ፍላጎት እንጂ ሌሎችን ለመጉዳት አይደለም - የኢፌዴሪ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት …....///…..... ኢትዮጵያ ታላቁ የህዳሴ ግድብን የገነባችው ካላት የመልማት ፍላጎት እና የኤሌክትሪክ ኃይልን ለህዝቦቿ ተደራሽ ለማድረግ እንጂ ሌሎችን ለመጉዳት አለመሆኑን መገንዘብ  እንደሚያስፈልግ የኢፌዴሪ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዲኤታ ገለጹ። በሚኒስትር ዲኤታው ተስፋሁን ጎበዛይ የተመራ እና በአፍሪካ ፖለቲካ እና የነጻነት ትግል ውስጥ ትልቅ ድርሻ የነበራቸው የአፍሪካ የቀድሞ መሪዎች ልጆችን ያካተተ የልዑካን ቡድን ትናንት በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ጉብኝት አካሂዷል። ሚኒስትር ዴታው በጉብኝቱ ላይ እንደገለጹት የግድቡን እውነታ በቦታው ተገኝተው  ያላዩ  አካላት ግድቡን በሚመለከት የሚያነሷቸው ጥያቄዎች በመረጃ መዛባት የተቃኙ ስለነበሩ ይህን በማረም እውነታውን ማስረዳት ያስፈልጋል። ጉብኝቱ በፓን አፍሪካ እንቅስቃሴ እና በአፍሪካ አንድነት ድርጅት ምስረታ እንዲሁም በአህጉሪቱ ታሪክና ፖለቲካ ትልቅ ስም ያላቸው መሪዎች ልጆች የተሳተፉበት መሆኑ አባቶቻቸው ሲመኙት የነበረውን አፍሪካ ትልልቅ ጉዳዮችን አቅዶ የመፈጸም እና ፕሮጀክቶችን ሰርቶ የማጠናቀቅ ህልም ምን እንደሚመስል ግድቡን አይተው እንዲረዱ ለማስቻል ያለመ መሆኑን ሚኒስትር ዲኤታው ገልጸዋል። በተጨማሪም  ጉብኝቱ ከአፍሪካ የመጡ የህዝብና የንግድ ሚዲያ ኃላፊዎችም  ግድቡን በተመለከተ ከአሁን በፊት በተለያዩ መንገዶች ሲሰሯቸው ከነበሩ ዘገባዎች በተሻለ ቦታው ላይ በመገኘት እውነታውን የበለጠ በዓይናቸው አይተው እንዲረዱና እንዲገልጹ ያስችላል ብለዋል። ስለሆነም ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ውሃ ኤሌክትሪክ አመንጭቶ እንደሚፈስ፣ ለታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ጥቅም እንጂ ጉዳት እንደሌለው እንዲሁም ኢትዮጵያ ይህን ግድብ የሠራቸው ካላት የመልማት ፍላጎት እና የኃይል ጥማት እንጂ ሌሎችን ለመጉዳት እንዳልሆነ ተገንዝበው በሚያገኙት አጋጣሚ ሁሉ እውነታውን እንዲያሳውቁ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ በፓን አፍሪካኒዝም እንቅስቃሴ በተለያዩ ትውልዶች ገላጭ የሆኑ አስተዋፅኦዎችን ስታበረክት እንደነበር የጠቀሱት ሚኒስትር ዲኤታው ለዚህም አድዋ ጥቁር ማሸነፍ እንደሚችል ለአፍሪካውያን በማሳየት የፓን አፍሪካኒዝም እንቅስቃሴ እንዲጀመር በር የከፈተ እንደነበር አስታውሰዋል። የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ እና በከተማ ልማትና በግብርና የተከናወኑና በመከናወን ላይ የሚገኙ ሥራዎችም  አፍሪካውያን መፈጸምና ማሳካት ይችላሉ የሚለውን የማስረጽ ሞዴል ተደርጎ እንደሚወሰድ አብራርተዋል። ኢትዮጵያ ያከናወነቻቸው ሥራዎችና የተገኙ ውጤቶችን በማስተዋወቅ አፍሪካውያን እንዲገነዘቡት ለማስቻል እንዲሁም በቀጣይ በጋራ በሚከናወኑ ጉዳዮች ላይም አብሮ ለመሥራት ጉብኝቱ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 28 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+8

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የአዲሱ ትውልድ ፓን አፍካኒዝም ነው - የቀድሞ የአፍሪካ የነጻነት ታጋዮች ልጆች .......///........ ኢትዮጵያ ገንብታ ያጠናቀቀችው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ቀደምት አፍሪካውያን አባቶቻችን ሲመኙት የነበረውን ርዕይ እውን ያደረገ፣ አፍሪካን ዳግም ወደ አንድነት የሚያመጣ የአዲሱ ትውልድ ፓን አፍሪካኒዝም መሆኑን የቀድሞ የአፍሪካ የነጻነት ታጋዮች ልጆች  ገለጹ። በአፍሪካ ታዋቂ የሆኑ የነጻነት ታጋዮችና ተፅዕኖ ፈጣሪ መሪዎች ልጆች ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ኃይል ማመንጫ ጣቢያን ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ ላይ አስተያየታቸውን የሰጡት ጎብኝዎቹ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከኢትዮጵያ አልፎ ለአፍሪካውያን ትልቅ የመቻል ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል። የቀድሞው የጋና የነጻነት ታጋይ የክዋሚ ንክሩማ ልጅ ሳሚያ ንኩርማ አፍሪካውያን በኢኮኖሚ፣ በፖለቲካ እና በማህበራዊ ጉዳዮች አንድ ሆነው ማየት የአባታቸው የዘወትር ህልም እንደነበር አስታውሰዋል። ስለሆነም ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አፍሪካውያን በሁሉም ዘርፎች ቢጀምሩም ማጠናቀቅ አይችሉም የሚለውን የተሳሳተ ትርክት መለወጥ የሚችል ከኢትዮጵያም አልፎ ለመላው ጥቁር ህዝቦች ኩራት መሆኑን አብራርተዋል። የቀድሞ የታንዛኒያ ፕሬዚዳንት ጁሊየስ ኔሬሬ ልጅ ማዳርካ ኔሬሬ በበኩላቸው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ በታንዛኒያ እና በኢትዮጵያ መካከል የተፈረመውን የኃይል ሽያጭ ስምምነት እውን በማድረግ በቀጣናው የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነትን ለማስፋት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ገልጸዋል። የህዳሴ ግድብ የኤሌክትሪክ ኃይል ከማመንጨት ባሻገር የፓን አፍሪካኒዝምን እሳቤ በአዲሱ ትውልድ ውስጥ ለማስረጽ እና  የፓን አፍሪካን አባቶችን ሌጋሲ ለማስቀጠል ትልቅ መነሳሳት እንደሚፈጥር ተናግረዋል። ከደቡብ አፍሪካ የመጡት እና የቀድሞው የአፍሪካ ናሽናል ኮንግረስ ፓርቲ ፕሬዚዳንት ኦሊቨር ታምቦ ልጅ ኖማቴምባ ታምቦ ኢትዮጵያ ህዝቦቿን አስተባብራ በራሷ የፋይናንስ አቅም ይህን ታላቅ ግድብ ገንብታ ማጠናቀቋ የሚደነቅ መሆኑን ጠቅሰዋል። ይህ ጥንካሬና ፅናት ለሌሎች አፍሪካውያንም ትልቅ መነሳሳት ይፈጥራል የሚል እምነት እንዳላቸው ተናግረዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ኢትዮጵያውያን ብዙ  ውስብስብ ችግሮችን በመፍታት ፅናታቸውን ለዓለም ህዝብ ያስመሰከሩበት እንደሆነ ማረጋገጣቸውን ጎብኝዎቹ መስክረዋል። ኢትዮጵያ ቀደም ሲል ለፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ የነበራትን አስተዋጽኦ እንደሚያውቁ አስታውሰው በቀጣይም  አፍሪካን አንድ የማድረግ የአባቶቻቸውን ሌጋሲ እውን ለማድረግ ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። በጉብኝቱ ታዋቂው የጋና የነጻነት ታጋይ ኩዋሚ ንኩሩማ ልጅ ሳሚያ ንኩሩማ እና የቀድሞ የታንዛኒያ የነጻነት ቀንዲልና  ፕሬዚዳንት የነበሩት የጁሊየስ ኔሬሬ ልጅ ማዳርካ ኔሬሬ ልጅን ጨምሮ የቀድሞ የሊቢያ መሪ መሃመድ ጋዳፊ፣ የቀድሞ የዛምቢያ ፕሬዚዳንት ኬኔት ካውንዳ፣ የፓትሪስ ሉምባ እና ሌሎች የአፍሪካ ተፅዕኖ ፈጣሪ መሪዎች ልጆች ተሳትፈዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 27 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9

የሚዲያ ባለሙያዎች የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጎበኙ ...///..... በኢፌዴሪ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዲኤታ የተመራ የሚዲያ ባለሙያዎች ልዑካን ቡድን በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ጎብኝት እያካሄዱ ነው። ሚኒስትር ዲኤታው አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ የጉብኝቱን  ዋና ዓላማ አስመልክተው እንደገለጹት ሚዲያዎች ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ማመንጫ ጣቢያ ነባራዊ እውነታን እንዲረዱና ትክክለኛ መረጃ እንዲያጋሩ ለማስቻል ነው። በጉብኝቱ ዲሴንደንት በሚል ማህበር የተቋቋሙ  የቀድሞ ታዋቂ የአፍሪካ መሪዎች ልጆች  በጉብኝቱ ላይ የተገኙ መሆኑን የጠቆሙት ሚኒስትር ዲኤታው ይህም አባቶቻቸው ሲመኙት የነበረውን አፍሪካውያን ጀምሮ የመጨረስ ህልም በህዳሴ ግድቡ የተሳካ መሆኑን እንዲመለከቱ ታስቦ መሆኑን አስረድተዋል። ታዋቂው የጋና የነጻነት ታጋይ ክዋሚ ንኩርማ ልጅ ሳሚያ ንኩሩማን ጨምሮ የኬኔት ካውንዳ፣ የጁሌስ ኔሬሬ  እና ሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች መሪዎች ልጆች እንዲሁም የተለያዩ የሃገር ውስጥና የውጭ ሃገር ሚዲያዎች በጉብኝቱ ላይ ተሳትፈዋል። በተጨማሪም ከቱሪዝም ሚኒስትር፣  እና ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኃይል የተውጣጡ አመራርና ሠራተኞች በጉብኝቱ ታድመዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ህዳር 27 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+9