EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 555 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 397,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 165 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 555 名订阅者。
根据 21 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 10,过去 24 小时变化为 1,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.74%。内容发布后 24 小时内通常能获得 14.94% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 003 次浏览,首日通常累积 2 323 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 22 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 555
订阅者
+124 小时
+87 天
+1030 天
帖子存档
15 555
የተቋሙ አመራርና ሠራተኞች የአድዋ መታሰቢያ ሙዚየምን ጎበኙ
.......///........
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅን አስመልክቶ ባዘጋጀው የምስጋና መርሀ ግብር ላይ ለመታደም የተገኙ አመራሮችና ሠራተኞች የአድዋ መታሰቢያ ሙዚየምን ጎበኝተዋል።
በተቋሙ የትራንሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አንዱዓለም ሲዓ በጉብኝቱ ወቅት እንደገለጹት የአድዋ ድል ሀገርን ለማጽናት ሲባል ለነጻነት የተከፈለ የደም ዋጋና የጽናት ተምሳሌት የሆነ የጥቁር ህዝቦች ቀንዲል ነው።
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ደግሞ ኢትዮጵያውያን ለሁሉን አቀፍ ዕድገት በአንድነትና በትብብር በመቆም የገነቡት የጽናት ተምሳሌት ፕሮጀክት ነው።
አድዋ ሀገርን ለማጽናት የተደረገ ተጋድሎ ሲሆን ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ደግሞ በኢነርጂ ዘርፉ ራስን ከመቻል ባሻገር ለጎረቤት ሀገራት ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ለማጠናከር የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።
ሠራተኞች በበኩላቸው ዳግማዊ አድዋ በሆነው ታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ላይ የተለያየ ድርሻ ያላቸው አመራርና ሠራተኞች የአድዋን መታሠቢያ መጎብኘታቸው ልዩ ስሜት እንደፈጠረባቸው ተናግረዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መስከረም 27 ቀን 2018 ዓ.ም
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መስከረም 27 ቀን 2018 ዓ.ም
15 555
የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ክቡር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ በሕዝብ ተወካዮች እና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች የ2018 ዓ.ም የሥራ ዘመን የጋራ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ የኃይል ዘርፉን በተመለከተ ካነሷቸው ነጥቦች መካከል
….///….
📌 በአዲሱ ዓመት መባቻ የበርካታ ዓመታት የቁጭታችንና የጥረታችን ውጤት የሆነውን የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ያስመረቅንበት ይህ ዘመን በታሪካችን ውስጥ በጉልህ የሚወሳ አዲስ ምዕራፍ ነው፡፡
📌 በ2018 የኃይል ተደራሽነትን ለማሳደግ መንግስት ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል፡፡
📌 የሕብረተሰቡን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት የሚያስችሉ የታዳሽ ኃይል ፕሮጀክቶች በቀጣይ ዓመታት በበቂ ይገነባሉ፡፡
📌 ለውጭ ንግድ(ኤክስፖርት) የሚበቃ የኤሌክትሪክ አቅርቦት በማሳደግ ለቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትስስር መሰረት ይጣላል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም
15 555
+4
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ
....///....
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልኢንቫሮሜንታሊስት I (ዲ1)' ሶሾሎጂስት I (ዲ1) እናኦኮፔሽናል ኸልዝ እና ሴፍቲ ኦፊሰር I (ዲ1) የስራ መደቦች ላይ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር በነሀሴ 01 ቀን 2017 ዓ.ም የውጭ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወቃል፡፡
በዚሁ መሰረት ከላይ ስማችሁ የተገለጸ አመልካቾችሰኞ ጥቅምት 03 ቀን 2018 ዓ.ም ጠዋት 2፡30 ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ ብረታ ብረት ፊት ለፊት በሚገኘው በዋናው መ/ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ የጽሁፍ ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 28 ቀን 2017 ዓ.ም
15 555
ተቋማቱን ውጤታማ ለማድረግ የዩኒቨርሲቲ ኢንዱስትሪ ትስስርን ማጠናከር ይገባል
….///…..
ብቃት ያለው ባለሙያ በማፍራት ተቋማቱን ውጤታማ ለማድረግ የዩኒቨርሲቲና ኢንዱስትሪ ትስስሩን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የጅማ ዩኒቨርሲቲ የሥራ ኃላፊዎች ተናግረዋል።
የሥራ ኃላፊዎቹ በሁለቱ ተቋማት መካከል ያለው የትብብር ሥራ ተጠናክሮ በሚቀጥልበት ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሂደዋል።
የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጀማል አባፊጣ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት የተቋማትን ውጤታማነት ለማረጋገጥ የዩኒቨርሲቲና የኢንዱስትሪ ግንኙነትን በማጠናከር በትብብር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።
ዩኒቨርሲቲው በኃይል ልማት ዘርፉ ላይ የራሱን አስተዋፅኦ ለማበርከት ከተቋሙ ጋር አሁን ካለው የትብብር ሥራ በተጨማሪ በሌሎች የተለያዩ የሥራ መስኮች ላይ በጋራ የመስራት ፍላጎት እንዳለው ጠቁመዋል።
በኃይል ልማት ዘርፉ ወቅቱን የዋጀ የስልጠናና የትምህርት ሥርዓት ለመዘርጋት ተቋማቱ ከፕሮግራም ቀረፃ ጀምሮ በጋራ መስራት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።
በዩኒቨርሲቲው የአስተዳደር እና ልማት ምክትል ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ገመቺስ ፊሌ ዩኒቨርስቲያቸው በውሃ ምህንድስና፣ በግድብ ክትትልና ደህንነት፣ በአካባቢያዊ ተፅዕኖ ግምገማ ጥናት፣ በአቅም ግንባታና ስልጠና፣ በማህበረሰብ ልማትና ግንኙነት እንዲሁም በቴክኖሎጂና ፈጠራ ጉዳዮች ለይ ከተቋሙ ጋር በትብብር የመስራት ፍላጎት እንዳለው አብራርተዋል።
በተጨማሪም አካባቢን መልሶ በማቋቋም፣ ከዘርፋ ጋር በተገናኙ ፖሊሲዎች ቀረፃና አስተዳደር ፣ በሥራ ፈጠራና ኢኖቬሽን ማዕከል /ልህቀት/ማቋቋም፣ በሥራ ላይ ልምምድና የተማሪዎች የፕሮጀክት ሥራ፣ በአውደ ጥናት፣ ኮንፈረንስ እና መሰል ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት ፍላጎት እንዳለውም ምክትል ፕሬዚዳንቱ ገልፀዋል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጄነሬሽን ቢዝነስ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ወ/ኪዳን ሁለቱ ተቋማት በትብብር የሚሰሩባቸው በርካታ ጉዳዮች እንዳሉ ገልፀው ትብብሩ ተቋሙ የያዘውን ሀገራዊና ቀጣናዊ ዕቅድ ለማሳካት ሚናው የጎላ ነው ብለዋል። የሁለቱን ተቋማት ባለሙያዎች ለማብቃት የዩኒቨርሲቲ ኢንዱስትሪ ትስስሩን በተግባር ማጠናከር እንደሚገባና ለዚህም ተቋሙ ዝግጁ መሆኑን አንስተዋል።
በተቋሙ የኮርፖሬት ፋይናንስና ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ በበኩላቸው ተቋሙ ከዩኒቨርሲቲው ጋር አብሮ ለመስራት ፈቃደኛ መሆኑን አረጋግጠው ይሁንና ትብብሩ ቀጣይነት ያለው እንዲሆን፤ ከቀረቡ ሀሳቦች መካከል በጋራ ሊሰራባቸው የሚገቡ ጉዳዮች በተቋሙ በዝርዝር ተለይተው እንደሚቀርቡ አስታውቀዋል።
ከዚህ በፊት ከተለያዩ ተቋማት ጋር በተለዩ ጉዳዮች በትብብር ለመስራት ዕቅድ ቢያዝም ስምምነቶች ከወረቀት ውጭ በተጠናከረ መልኩ በአግባቡ ባለመተግበራቸው የሚፈለገው ውጤት እንዳይመጣ አድርጎታል ያሉት ደግሞ የኮይሻ ማመንጫ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ አቶ መብራቱ ተሾመ ናቸው።
ስለሆነም የትብብር ሥራው ውጤታማ እንዲሆን ሁለቱ ተቋማት በጋራ የሚሰሩባቸውን ጉዳዮች በግልፅ በማስቀመጥ ተግባራዊነቱ ክትትል የሚደረግበት የጋራ ሥርዓት መዘርጋት ይኖርባቸዋል ብለዋል።
የኢትዮ ፓወር አካዳሚ ዳይሬክተር ወንድወሰን ካሳ (ዶ/ር) ተቋሙ በዘርፋ ብቁ ባለሙያዎችን ለማፍራት የሚያስችለውን ኢንስቲትዩት ለማቋቋም እየሰራ ነው ብለዋል።
ባለሙያዎቹ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚሆኑበትን የብቃት ማረጋገጫ እንዲያገኙ የሚያስችል የትምህርት ፕሮግራም እንዲከፈት ተቋሙ ፍላጎት እንዳለው የተናገሩት ዳይሬክተሩ ይህ ወደተግባር እንድለወጥ የትብብር ሥራው ወሳኝ ስለመሆኑም አስታውቀዋል።
ሁለቱ ተቋማት በትብብር የመስራት ፍላጎትቻውን ለማጠናከር የያዙትን ዕቅድ ተግባራዊ ለማድረግሥራውን የሚከታተሉ የሥራ ኃላፊዎችን መድበዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም
15 555
ከተረዳዳንና ከተባበርን የማይሳካ ነገር እንደማይኖር በኮይሻ አካባቢ የተገኘው ውጤት ማሳያ ነው
...............//..........
ከተረዳዳንና ከተባበርን የማይሳካ ነገር እንደማይኖር በጎፋ ዞን መለኮዛ ወረዳና አካባቢው የተገነቡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ማሳያ ናቸው ሲሉ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ ገለፁ።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና ዊ ቢውልድ ኩባንያ የጋራ ትብብር በጎፋ ዞን መለኮዛ ወረዳ ባንካ ቀበሌ ባንካ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ላይ የተገነቡ የመማሪያ ክፍሎች በዛሬው እለት ተመርቀዋል።
ምርቃቱ ላይ የተገኙት የጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ እንደተናገሩት አካባቢው የበርካታ ተፈጥሮ ፀጋዎች ባለቤት ቢሆንም ባለው የመሰረተ ልማት እጥረት ምክንያት ጥቅም ላይ ሳይውል ቆይቷል።
ይሁንና የኮይሻ ፕሮጀክት በአካባቢው ከመጣ በኋላ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የዊ ቢውልድ ኩባንያ ባከናወኗቸው የመሠረተ ልማት ግንባታዎች የአካባቢው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እየተነቃቃ ይገኛል ብለዋል።
በዛሬው እለት ለምረቃ የበቁ የመማሪያ ክፍሎች በአካባቢው ያለውን የትምህርት ተደራሽነት በማስፋት በእውቀት የታነፀ ትውልድ ለመፍጠር ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወቱም ተናግረዋል።
እንደ ዋና አስተዳዳሪው ገለፃ ፕሮጀክቱ ከመሰረተ ልማት ግንባታ ሥራዎች ባለፈ በዞኑ በሚከሰቱ የተፈጥሮ አደጋዎች ላይ ሰብዓዊ ድጋፎችን በማድረግ የማህበረሰብ አለኝታነቱን እያሳየ ይገኛል። ተቋማቱ እያደረጉ ላሉት ሁሉን አቀፍ ድጋፍም አመስግነዋል።
"ከተባበርንና በጋራ ከቆምን ሀገር መለወጥ እንደምንችል በአካባቢው ከተገኘው ውጤት ተገንዝበናል" ያሉት ኢንጂነር ዳግማዊ ሀገሪቱ ያላትን ፀጋ ጥቅም ላይ ለማዋል ሁሉም በአንድነትና በትብብር መስራት እንደሚጠበቅበትም አስገንዝበዋል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮይሻ ፕሮጀክት የአካባቢያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ግዛቸው ደሳለኝ ፕሮጀክቱ በአካባቢው መተግበር ከጀመረ ወዲህ ከ1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ የጤና፣ የውሃ፣ የመንገድ፣ የትምህርት ወዘተ መሰረተ ልማቶችን በመገንባት የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን አስታውሰዋል።
በጅማ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ በቆዩ የፕሮጀክቱ ሠራተኞች እየተመራ ለምረቃ የበቁት የትምህርት መማሪያ ክፍሎች ተቋሙ ለማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎች የሰጠውን ትኩረት የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል።
በትምህርት ቤቱ ላይ ለተገነቡ አራት የመማሪያ ክፍሎች እና አንድ የአስተዳደር ቢሮ 17 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር ወጭ መደረጉን ጠቁመዋል።
የተማሪዎቹ አስተባባሪ አቶ ኤሊያስ ኤካ በበኩላቸው ተማሪዎች በአካባቢው ያለውን የትምህርት ተደራሽነት እጥረት ከግንዛቤ በማስገባት የትምህርቱ አካል የሆነውን የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራ በትምህርት ዘርፍ ላይ ማድረጋቸውን ገልፀዋል።
ለመማሪያ ክፋሎቹ ግንባታ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና የኮይሻ ፕሮጀክት ሥራ ተቋራጩ ዊ ቢውልድ ኩባንያ በገንዘብ፣ በጥሬ ዕቃ እና በሰው ሀይል ድጋፍ ማድረጋቸውን ጠቁመው ለተደረገላቸው ድጋፍም ተቋማቱን አመስግነዋል።
በዕለቱ ለትምህርት ቤቱ ግንባታ አስተዋፅኦ ላደረጉ አካላት እውቅና ተሰጥቷል።
በምረቃ ሥነ- ሥርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተወካይና የጄነሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ወ/ኪዳን እና የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጀማል አባፊጣ(ዶ/ር) ጨምሮ የተቋሙ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የዩኒቨርሲቲው የሴኔት አባላት፣ የአካባቢው የመስተዳደር አካላት፣ የአካባቢው የሀገር ሽማግሌዎችና የትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ አካላት ተገኝተዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መስከረም 25 ቀን 2018 ዓ.ም
15 555
ተመራቂዎች ያገኙትን ዕውቀት ከልምዳቸው ጋር አቀናጅተው በአግባቡ ሥራ ላይ ማዋል ይጠበቅባቸዋል- ኢንጅነር ኤፍሬም ወ/ኪዳን
ሠራተኞች በትምህርት ቆይታቸው ያገኙትን ዕውቀት ወደ ተግባር በመለወጥ ሀገራዊ ግደታቸውን በአግባቡ መወጣት እንደሚጠበቅባቸው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጄነሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አሳሰቡ።
ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚው ኢንጂነር ኤፍሬም ወ/ ኪዳን ለተመራቂ የኮይሻ ፕሮጀክት ሠራተኞች የእንኳን ደሥ አላችሁ መልዕክት ባስተላለፉበት ወቅት እንደገለጹት ተቋሙ የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል የመሆን ራዕዩንና የያዘውን የስትራቴጂክ ዕቅድ ለማሳካት ብቃት ያለው የሰው ኃይል ያስፈልጋል።
በዚህም ተቋሙ ከአጫጭር ስልጠናዎች በተጨማሪ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመተባበር የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችንና የፕሮጀክት ሠራተኞችን አቅም ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶት እየሰራ ይገኛል ብለዋል።
የጅማ ዩኒቨርሲቲ በተቋሙ የሰው ኃይል ልማት ላይ የበኩሉን አሻራ እያሳረፈ ከሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መካከል አንዱ መሆኑን አስታውሰው በአሁኑ ወቅትም ተቋሙ ከዩኒቨርሲቲው ጋር ያለውን ትበብር በማጠናከር የኮይሻ ፕሮጀክት ሠራተኞች ከመደበኛ ሥራቸው ጎን ለጎን የሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን በሥራ ቦታቸው ላይ ሆነው እንዲከታተሉ በማድረግ ማስመረቅ ተችሏል ብለዋል።
የትምህርት መርሃ ግብሩ የሥራ ልምድን ከንድፈ-ሀሳብ ባጣመረ መልኩ በመሠጠቱ ለተቋሙ ብቃት ያለው ሠራተኛ በማፍራት በኩል ከፍተኛ ሚና እንዳለው የተናገሩት ኢንጂነር ኤፍሬም ተማሪዎች ከፕሮጀክቱ ጋር ተያያዥነት ባላቸው ጉዳዮች ላይ የሰሩዋቸው የመመረቂያ ጽሑፎች ለተቋሙ በግብዓትነት እንደሚያገለግሉም አስታውቀዋል ።
ዩኒቨርስቲው የተቋሙን ሠራተኞች አቅም ለማሳደግ እያደረገ ላውን ጥረት እና የዛሬ ተመራቂዎች ለስኬት እንዲበቁ ላበረከተው አስተዋፅኦ አመስግነው ተቋሙ በቀጣይ በሰው ኃይል ልማትና በሌሎች መስኮች ከዩኒቨርስቲው ጋር የሚኖረውን ትብብር አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ኢንጂነር ኤፍሬም አረጋግጠዋል።
በቀጣይ በተለያዩ የሥራ ቦታዎች ያሉ ሠራተኞችን አቅም በማሳደግ ብቁ የሰው ኃይል ለማፍራት የትምህርት እድሉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
ተመራቂዎቹ በትምህርት ቆይታቸው ያገኙትን
ዕውቀት ከልምዳቸው ጋር በማቀናጀት በፕሮጀክቱ ቆይታም ሆነ ወደፊት በሚሰማሩበት የሥራ መስክ የተጣለባቸውን ኃላፊነት በአግባቡ እንዲወጡ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው አሳስበዋል።
የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጀማል አባፊጣ (ዶ/ር) በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው "በማህበረሰብ ውስጥ ነን" በሚል መርሁ የማህበረሰብ አገልግሎቶቹን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልፀው ለፕሮጀክቱ ሠራተኞች የተሰጠው የትምህርት ፕሮግራም ዩኒቨርሲቲው የማህበረሰቡ መሆኑን በተግባር ማረጋገጥ የተቻለበት ነው ብለዋል።
ኮይሻ ፕሮጀክት የሀገራችን የማንሰራራት ያረጋግጣሉ ብሎ ዩኒቨርሲቲው ከለያቸው ፕሮጀክቶች አንዱ በመሆኑ የሠራተኞቹን አቅም ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
በዚህም የፕሮጀክቱን ሠራተኞች ከሥራቸው ጎን ለጎን በሥራ ቦታቸው ላይ ሄዶ በማስተማር ማስመረቅ መቻሉን አስረድተው በዘርፉ ብቃት ያለው ባለሙያ ለማፍራት ዩኒቨርሲቲው ከተቋሙ ጋር ያለውን ትብብር አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
ከተመራቂ ሠራተኞች መካከል ኤሊያስ ኤካ እና ተወዳጅ በቀለ እንደተናገሩት ትምህርቱ በመደበኛ ሥራቸው ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ሳያሳድርባቸው አጠናቀው በመመረቃቸው ደስታቸውን ገልፀዋል፡፡
በትምህርት ቆይታቸው ለሥራቸው ግብዓት የሚሆኑ ተጨማሪ እውቀቶችን እንዳገኙ የገለፁት ተመራቂዎቹ የተከታተሉት የትምህርት መስከ በሥራቸው ላይ ውጤታማ እንዲሆኑ እንደሚረዳቸውም አስረድተዋል፡፡
በሥራ ቦታቸው ላይ ሆነው ትምህርቱን እንዲከታተሉ ተቋሙና ፕሮጀክቱ ላደረጉላቸው ድጋፎች አመስግነው የተጣለባቸውን ኃላፊነት በአግባቡ ለመወጣት በቁርጠኝነት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መስከረም 25 ቀን 2018 ዓ.ም
15 555
የተቋሙ የሥራ ኃላፊዎች የኮይሻ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን ጎበኙ
.......///.......
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ፕሮጀክትን የሥራ እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል።
የሥራ ኃላፊዎቹ የዋናውን ግድብና የኃይል ማመንጫ ቤቱን የግንባታ ሥራ እንዲሁም የግንባታ ግብዓት ማምረቻ ወርክ ሾፖችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
በጉብኝቱ ፕሮጀክቱ የደረሰበትን ደረጃና የአሰራር ሂደት፣ ፕሮጀክቱ እያከናወነ ስላለው የማህበራዊ አገልግሎት ሥራዎች እንዲሁም ግንባታውን በተያዘለት መርሃ ግብር ለማጠናቀቅ በቀጣይ መከናወን ስለሚኖርባቸው ሥራዎች የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ መብራቱ ተሾመ ለሥራ ኃላፊዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ሥራ አስኪያጁ በማብራሪያቸው ፕሮጀክቱ በፋይናንስና ችግር ምክንያት ተጓቶ የነበረ ቢሆንም በተቋሙና በመንግስት በተወሰዱ እርምጃዎች አሁን የግንባታ ሥራው በጥሩ ሂደት ላይ ይገኛል ብለዋል።
በዚህም በአሁኑ ወቅት የዋናው ግድብ የጥቅጥቅ ኮንክሪት ሙሌት 70 በመቶ፣ የማመንጫ ቤቱ የመጀመሪያ ደረጃ የአርማታ ኮንክሪት 68 በመቶ እንዲሁም የግድቡ የውሃ ማስተንፈሻ የስትራክቸራል ኮንክሪት ሥራ 30 በመቶ ላይ መድረሱን አብራርተዋል።
ግድቡ ሲጠናቀቅ ከሚኖረው 201 ሜትር ከፍታ አሁን ላይ በአማካኝ ከ120 ሜትር በላይ መድረሱን የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈፃፀም ደግሞ 72 በመቶ ላይ ደርሷል ነው ያሉት።
በቀጣይ በኤሌክትሮ ሜካኒካልና ሀይድሮሊክ ስቲል ስትራክቸር ገጠማ ሥራዎች ላይ ትኩረት ተደርጎ እንደሚሰራና ይህም የከፍተኛ አመራሩን የቅርብ ክትትልና ድጋፍ እንደሚጠይቅ አስገንዝበዋል።
እንደ አቶ መብራቱ ገለፃ ጉብኝቱ የተቋሙ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ፕሮጀክቱ የደረሰበትን ደረጃ ተመልክተው በቀጣይ ለሚከናወኑ ሥራዎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ እና ለችግሮቹ አፍጣኝ እርምጃዎችን እንዲሰጡ ያስችላል።
ከጅማ እስከ ጭዳ ባለው መንገድ ላይ የሚስተዋለው ችግር በፕሮጀክቱ ዕቃዎች ማጓጓዝ ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ በመሆኑ ከፍተኛ ሥራ አመራሩ ችግሩ እንዲቀረፍ እያከናወነ ያለውን ሥራ አጠናክሮ እንዲቀጥልም አሳስበዋል።
በጉብኝቱ ላይ የተሳተፉት የጄነሬሽን ቢዝነስ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ወ/ ኪዳን እና የኮርፖሬት ፋይናንስና ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ የፋይናንስ ችግር ገጥሞት እንደነበር በማስታወስ የግንባታ ሥራውን ለማስቀጠል ተቋሙ አሁን ላይ አብዛኛውን ክፍያዎች በራሱ እየሸፈነ ስለመሆኑም ገልፀዋል።
የመስክ ምልከታው የፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ የደረሰበትን ደረጃና ያጋጠሙ ችግሮችን በጋራ ለይቶ ለችግሮቹ ወቅታዊ መፍትሔ በመስጠት የፕሮጀክቱን አፈፃፀም ለማሻሻል እንደሚያግዝ ተናግረዋል።
ከዚህ በተጨማሪም ጉብኝቱ በቀጣይ መከናወን ስለሚኖርባቸው ሥራዎች አቅጣጫ ለማስቀመጥ የሚያስችል ሲሆን ምልከታው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መስከረም 25 ቀን 2018 ዓ.ም
15 555
በተለያዩ የትምህርት መስኮች ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ የፕሮጀክቱ ሠራተኞች የምረቃ ሥነ -ሥርዓት እየተካሄደ ነው
የጅማ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና ከዊ ቢውልድ ኩባንያ ጋር በመተባበር በሁለተኛ ዲግሪ ያስተማራቸውን 37 የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሠራተኞችን በዛሬው ዕለት እያስመረቀ ነው፡፡
በምረቃ ሥነ -ሥርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተወካይና በተቋሙ የጄኔሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ወ/ኪዳን እና የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጀማል አባፊጣን(ዶ/ር) ጨምሮ ሌሎች የተቋሙ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የዩኒቨርሲቲው የሴኔት አባላት፣ የኮንታና ጎፋ ዞኖች ዋና አስተዳሪዎችና ሌሎች የአካባቢው የመስተዳድር አካላት የፕሮጀክቱ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች፣ የተመራቂ ቤተሰቦች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ተቋሙ በኃይል ማመንጫ ጣቢያ እና በፕሮጀክቶች ላይ የሚገኙ ሠራተኞች በየአካባቢያቸው ከሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመተባበር ከመደበኛ ሥራቸው ጎን ለጎን በሥራ ቦታቸው ላይ ሆነው የትምህርት ዕድል የሚያገኙበትን ምቹ ሁኔታ እየፈጠረ ሲሆን በዛሬው ዕለት የሚመረቁ የኮይሻ ፕሮጀክት ሠራተኞችም የዚሁ ተጠቃሚ ናቸው።
ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ለፕሮጀክቱ ሠራተኞች የተሰጠው የትምህርት እድል በኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የተመቻቸ ስለመሆኑም ተገልጿል።
ከተመራቂዎች መካከል አስሩ በኮንስትራክሽን ኢንጂነሪንግና ማኔጅመንት፣ 14 በፕሮጀክት ማኔጅመንት እና ፋይናንስ እንዲሁም 13 በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን የትምህርት መስክ የተከታተሉ ናቸው። ከዚህ ውስጥ 33 ወንድና ሦስቱ ሴቶች ናቸው።
ሠራተኞች በሥራ ቦታቸው ላይ ሆነው ትምህርታቸውን መከታተላቸው በሥራ ቦታዎች ላይ የሠው ኃይል እጥረት እንዳያጋጥም ያግዛል።
ከሠራተኞች ምርቃት በተጨማሪ በተመራቂ ሠራተኞች አስተባባሪነት የተገነባ ትምህርት ቤት ምርቃት እንዲሁም የኃይል ልማት ዘርፉን ለማሳደግ በተቋሙና በዩኒቨርሲቲው መካከል ያለው የትብብር ሥራ ተጠናክሮ በሚቀጥልበት መንገድ ላይ ውይይት ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መስከረም 25 ቀን 2018 ዓ.ም
15 555
ኬንያ ከውጭ ከምትገዛው ኤሌክትሪክ 83 በመቶውን የምትገዛው ከኢትዮጵያ ነው
….…///….…
ኬንያ ከውጭ ከምትገዛው አጠቃላይ የኃይል አቅርቦቷ ውስጥ 83 በመቶው ከኢትዮጵያ የተገኘ መሆኑን ካፒታል ኤፍ ኤም የተሰኘው የሀገሪቱ ሬዲዮ ገለጸ፡፡
የመረጃ ምንጩ የሀገሪቱን የኢነርጂና ነዳጅ ተቆጣጣሪ ባለሥልጣን ጠቅሶ እንደዘገበው ኬንያ እስከ ሰኔ ወር 2017 ዓ.ም. ድረስ ከውጭ ካስገባችው ጠቅላላ የኤሌክትሪክ ኃይል 83 በመቶው ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተገኘ ነው፡፡
ኬንያ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር በፈጠረችው የኃይል ትስስር ከዚህ ቀደም ሀገራዊ የኤሌክትሪከ ፍላጎቷን ለማሟላት ለነዳጅ እና ለሌሎች አማራጭ የኃይል ምንጮች የምታወጣውን ከፍተኛ ወጪ አስቀርቶላታል ፡፡
በዚህም ኬንያ በዓመት 10 ሚሊየን ዶላር ገደማ ማዳን መቻሏን ሬዲየው አስታውቋል፡፡
የኬንያው ቢዝነስ ዴይሊ አፍሪካ ጋዜጣ በበኩሉ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት በኬንያ ሊፈጠር የሚችለውን የኃይል ቀውስ በመከላከል ረገድ ወሳኝ መሆኑን በመጥቀስ “ኢትዮጵያ ኬንያን ከመብራት መጥፋትና ከፈረቃ ታድጋለች” ሲል ዘግቧል፡፡
ኢትዮጵያ እና ኬንያ ቀደም ሲል በተፈራረሙት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ስምምነት መሰረት ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ በቀን በከፍተኛ ጭነት ሰዓት 200 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለኬንያ እያቀረበች ትገኛለች፡፡
ኢትዮጵያ ቀጣናውን በኃይል ትስስር ለማጠናከር በያዘችው ዕቅድ መሰረት ከኬኒያ በተጨማሪ በአሁኑ ወቅት ከጂቡቲ፣ ሱዳን እና ታንዛኒያ ጋር የኤሌክትሪክ ኃይል ትስስር ፈጥራለች፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መስከረም 21 ቀን 2018 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
