uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 698 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 062-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 174-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 698 obunachiga ega bo‘ldi.

01 Sentabr, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 139 ga, so‘nggi 24 soatda esa 1 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 28.75% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 16.42% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 4 513 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 578 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 10 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
EEP Communication

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 02 Sentabr, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 698
Obunachilar
+124 soatlar
+277 kun
+13930 kun
Postlar arxiv
በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ ስርቆት የፈፀሙ አካላት በፅኑ እስራት ተቀጡ ….///…. ከእንጦጦ ፓርክ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር የኤሌክትሪክ ገመዶችን በመቁረጥ የሰረቁ ተከሳሾች እስከ 23 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት መቀጣታቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገለፀ፡፡ መልካሙ ማቴዎስ፣ ቢኒያም ካሳሁን፣ ደረጄ ተሰማ፣ ቶፊቅ ዓለሙ፣ አማኑኤል አቡ፣ አስመላሽ ትዕግስቱ እና ዓለሙ ተመስገን የተባሉ ተከሳሾች የወንጀል ድርጊቱን የፈፀሙት ጥቅምት 4 ቀን 2016 ዓ.ም በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ልዩ ቦታው እንጦጦ ፓርክ ውስጥ ነው። ተከሳሾች አባሪ ተባባሪ በመሆን ለእንጦጦ ፓርክ አገልግሎት እንዲውል የተዘረጋ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ገመድ ቆርጠው በኮድ1 ላዳ ተሽከርካሪ ጭነው ለመውሰድ ሲሉ በቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ ሲካሄድባቸው ቆይቷል፡፡ የጉለሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ያጠናቀረውን የምርመራ መዝገብ አቃቤህግ  ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ልዩ ልዩ የወንጀል ጉዳዮች ችሎት አቅርቧል፡፡ ፖሊስ በምርመራ መዝገቡ ተከሳሾቹ በተለያዩ ጊዜያት በሌሊት እንጦጦ ፓርክ ግቢ ውስጥ በመግባት የተዘረጉ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ገመዶችን እየቆረጡ በተሽከርካሪ በመጫን ሰርቀው በመውሰድና ሸጠው በመከፋፈል ተግባር መሰማራታቸውን ገልጿል፡፡ ፍርድ ቤቱም እንደ ወንጀሉ አፈፃፀምና ተሳትፏቸው መጠን ተከሳሾችን ያስተምራል፣ ሌሎች ወንጀል ፈፃሚዎችን ያስጠነቅቃል ሲል ከ6 ዓመት ከ9 ወር እስከ 23 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እንዲቀጡ የፍርድ ውሳኔ ሰጥቶባቸዋል። የመረጃ ምንጫችን የአዲስ አበባ ፖሊስ ነው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 28 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ኃይል ሳይቋረጥ ሲከናወን የቆየው የኮንዳክተር ገመድ ቅየራ ሥራ ሙሉ በሙሉ ተጠናቀቀ ….//…. በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ተከስቶ በነበረው የፀጥታ ችግር ሳቢያ ጉዳት የደረሰበትን የኮምቦልቻ- አላማጣ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ ሁለተኛ ሰርኪዩት መስመር ኃይል ሳይቋረጥ በአዲስ የኮንዳክተር ገመድ የመቀየር ሥራ ሙሉ በመሉ መጠናቀቁን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የትራንስሚሽን ቢዝነስ አስታወቀ። በትራንስሚሽን ቢዝነስ የፕሮጀክት ማኔጂመንት 1 ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ ሙሉ ብርሃን እንዳስታወቁት 114 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው ከኮምቦልቻ- አላማጣ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ሁለተኛ ሰርኪዩት የኮንዳክተር ሽቦ ዝርጋታ ሥራ ተጠናቆ በዛሬው ዕለት አገልግሎት መስጠት ጀምሯል። የመስመሩ መጠናቀቅ በኮምቦልቻ እና አላማጣ እንዲሁም አጎራባች ከተሞች በኤሌክትሪክ መቋረጥ ሳቢያ ሊፈጠር የሚችለውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግር ለማስቀረት የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ብለዋል፡፡ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታው ከ2013 ዓ.ም በፊት ተጠናቆ ለፍተሻና ሙከራ ሥራ ዝግጁ እንደነበር ያስታወሱት ሥራ አስኪያጁ በወቅቱ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በነበረው ጦርነት ምክንያት መስመሩ መጎዳቱን ገልፀዋል፡፡ እንደ አቶ አሸናፊ ገለፃ ከዚህ በፊት ከለገጣፎ- ኮምቦልቻ 61 ኪሎ ሜትር የኃይል ማሰተላለፊያ መስመር የኮንዳክተር ገመድ ቅየራ ሥራ ተጠናቆ ለህብረተሰቡ ያልተቆራረጠ ኃይል ማቅረብ መጀመሩንም አስታውሰዋል። ከለገጣፎ- ኮምቦልቻ በተከናወነው የኮንዳክተር ገመድ ቅየራ ሥራ ከመስመሩ ኃይል ለሚያገኙ አካባቢዎች እና ለለሚ ሲሚንቶ ፋብሪካ እንዲሁም ለደብረ-ብርሃን ኢንዱስትሪ ዞን አስተማማኝ ኤሌክትሪክ ለማቅረብ ማስቻሉንም ነው የጠቀሱት። በአንድ ዓመት ውስጥ የተጠናቀቀው የኮንዳክተር ገመድ ቅየራ ሥራ የግሪድ ሥርዓቱን ከማረጋጋት ባሻገር ተጨማሪ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ማስቻሉንም ነው ያስረዱት። የመስመር ዝርጋታ ሥራውን ኃይል ሳይቋረጥ ማከናወን መቻሉ ለተቋሙ ትልቅ እምርታ መሆኑን ያብራሩት አቶ አሸናፊ ሥራው በተቋሙ የኮንስትራክሽን ማኔጂመንት መምሪያ ሠራተኞች አቅም በስኬት በመጠናቀቁ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ‎ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 27 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

ሠራተኛው ለተቋማዊ ስኬት በእኔነት ስሜት ሊሰራ ይገባል  -  ዶ/ር አብርሃም በላይ ‎....//.... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኛ ለተቋማዊ ስኬት በእኔነት ስሜት ሊሰራ እንደሚገባ የተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አሳሰቡ። ‎ ‎የቦርድ ሰብሳቢው ዶ/ር አብርሃም በላይ እንደገለጹት በሀገሪቱ እያደገ ላለው የኃይል ፍላጎት ምላሽ ለመስጠት ተጨማሪ የኃይል መሰረተ ልማቶችን በከፍተኛ ፍጥነትና አቅም መገንባት ያስፈልጋል። ‎ ‌‎ሀገሪቱ ኃይል ለማመንጨት ያላትን እምቅ አቅም በጥናት ላይ ተመስርቶ ወደ ተግባር በመለወጥ የኃይል አማራጮችን ለማስፋት እና ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ ተቋሙ ጊዜን ቀድሞ ሊሰራ ይገባል ብለዋል፡፡ ዶ/ር አብርሃም እንደገለፁት የመነጨውን ኃይል ወደ ተጠቃሚው ለማድረስ አስተማማኝ የግሪድ መሰረተ ልማት ከመዘርጋት ጀምሮ ነባሮቹን በማሻሻልና በማዘመን ላይ ትኩረት ተሰጥቶ መሰራት እንዳለበት አንስተዋል። ‎ ‎ለዚህም ተቋሙ የሚያስተዳድረውን ከፍተኛ ሀብት በአግባቡ በመጠቀም የተሰጠውን ሀገራዊ ተልዕኮ ለመወጣት አሰራሮቹን ማዘመንና የክትትልና ቁጥጥር ሥራውን ማጠናከር እንዳለበትም ተናግረዋል፡፡ መንግስት የተቋሙን የፋይናንስ ቁመና ለማሻሻል የሚያስችሉ በርካታ እርምጃዎችን መውሰዱን በማስታወስ ቀጣይነት ያለው ለውጥ በማምጣት ተቋሙን ውጤታማ ለማድረግ በመንግስት በሚወሰዱ እርምጃዎች ሳይዘናጉ አቅዶ መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች የሚቀርበው ኃይል በአሰራር የተደገፈ ባለመሆኑ በአቅርቦቱ ላይ የተለያዩ ችግሮች እንደነበሩበት የተናገሩት ዶ/ር አብረሃም ችግሮቹን የአሰራር ሥርዓት በመዘርጋት መፍትሔ እስኪሰጠው ድረስ ተጨማሪ የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶችን ማስተናገድ መታገዱን ገልፀዋል። በዚህም የዳታ ማይኒንግ የኃይል አቅርቦትን ተጠያቂነትና ግልፅነት ባለው መልኩ በማድረግ ሀገሪቱ በአግባቡ ገቢ እንድታገኝ ለማስቻል በጥናት ላይ የተመሰረተ የአሰራር ሥርዓት ለመዘርጋት እየተሰራ እንደሆነም አስታውቀዋል። ከፕሮጀክቶች አፈፃፀም፣ የተቋሙን ገፅታ ከመገንባትና ሥራዎቹን ከማስተዋወቅ፣ ከሴቶች ተሳትፎ እና ተቋማዊ አቅምን ከመገንባት አንፃር ያሉ ክፍተቶችን በፍጥነት ማረም እንደሚገባም አቅጣጫ ሰጥተዋል፡፡ በሠራተኞች የተነሱ ጥያቄዎችንና ትኩረት እንዲሰጣቸው የቀረቡ ጉዳዮችን በዕቅድ አካቶ መስራት እንደሚገባ የገለፁት ዶ/ር አብርሃም ሠራተኛውን ሊያሰራ የሚችል አደረጃጀት እና ምቹ የሥራ ሁኔታ መኖሩን ለማረጋገጥ የሥራ አመራር ቦርዱ የሚያደርገውን ሁሉን አቀፍ ድጋፍና ክትትል አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡ የተቋሙ የሥራ መሪና ሠራተኛም ራሱን በእውቀትና በሥነ-ምግባር በማሳደግ፣ ሀገርንና ተቋምን በማስቀደም በእኔነት ስሜት በኃይል ዘርፉ ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉ ዘመን ተሻጋሪ ሥራዎች ሊያከናውን እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡‎ ‎ ‎የሠራተኛ ማህበር ተወካይና የቦርድ አባል የሆኑት አቶ ተሾመ በላይ በበኩላቸው የሠራተኛውን መብትና ጥቅም፣ የሙያ ደህንነትና ጤንነት እንዲሁም የሥራ ዋስትና እንዲረጋገጥ እና የኢንዱስትሪ ሠላም እንዲሰፍን ቦርዱ በትኩረት እየሰራ መሆኑን አንስተዋል፡፡ ተቋሙ ለሀገር ሁለንተናዊ እድገት የሚጫወተውን አውንታዊ ሚና ከግምት በማስገባት ሠራተኛው በሙሉ አቅሙ መስራት አለበት ያሉት አቶ ተሾመ የሠራተኛውን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት በዕቅድ ተይዘው እየተከናወኑ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

‎ተቋሙን ውጤታማ ለማድረግ የሚስተዋሉ ችግሮች በአፋጣኝ እንዲፈቱ ሠራተኞች ጠየቁ ‎.....///.... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተሰጠውን ተልዕኮ በስኬት ለመወጣት ከአሰራር እና ከሠራተኞች ተጠቃሚነት ጋር በተያያዘ የሚስተዋሉ ችግሮች በአፋጣኝ እንዲፈቱ የተቋሙ ሠራተኞች ጠይቀዋል። ‎ ‎የተቋሙ ሥራ አመራር ቦርድ በተቋሙ የ2017 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸምና በ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ  ሠራተኞች ጋር ውይይት ያደረገ ሲሆን ከተቋማዊ አሰራርና ከሠራተኞች ተጠቃሚነትና ደህንነት ጋር የተያያዙ ጥያቄዎች ተነስተዋል። ‎ ‎በዚህም ከዳታ ማይኒግ የኃይል አቅርቦትና የአሰራር ሥርዓት፣ የሴቶችን ተሳትፎ ከማረጋገጥ፣ ከወጪ ቅነሳ፣  ከግዥ ሥርዓት፣  ከፕሮጀክት አፈጻጸም፣ ተጠያቂነትን ከማስፈን፣ ከተቋሙ የሥራ ቦታዎች የይዞታ ማረጋገጫ፣ ከማከፋፈያ ጣቢያዎች አቅም ማሳደግና ትራንስፎርመር አቅርቦት ጋር የተያያዙ ጥያቄዎች ቀርበዋል። ‎ ‎በተጨማሪም ከደመወዝና ጥቅማ ጥቅም፣ ከሥራ ላይ ደህንነት፣ በተቋሙ እየተከናወነ ካለው የለውጥ  ሥራና አደረጃጀት አተገባበር፣ ከሠራተኛ ተጠቃሚነት እና ከሥራ ላይ ደህንነት ጋር የተያያዙ ጥያቄዎች በተሳታፊዎች ተነስተዋል። ‎ ‎ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ የሰጡት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጅነር አሸብር ባልቻ ለተቋሙ ቀጣይነት ላለው ዕድገትና መሻሻል መሰል መድረኮች አስፈላጊ ናቸው ብለዋል። ‎ ‎ተቋሙ ከአሁን ቀደም የነበረውን አሰራር ለማቀላጠፍና ወጭ ቆጣቢ በሆነ መልኩ ሥራዎችን ለመፈጸም ከአደረጃጀት ጀምሮ የተለያዩ የለውጥ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ያስረዱት ዋና ሥራ አስፈፃሚው የሥራ አመራር ምደባው በሥራ አመራር ቦርድ በፀደቀው መመሪያ መሠረት አቅምና ብቃትን መሰረት በማድረግ በውድድር መካሄዱን አስረድተዋል። ‎ ‎የመዋቅር ሥራውን እስከ ታችኛው ሠራተኛ ድረስ በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ ስለመሆኑ አንስተዋል። ‎ ‎የሠራተኛውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በዓመታዊ የደመወዝ ጭማሪ ከስኬል የወጡትን ለማስተካከል አዲስ የደመወዝ ጥናት መከናወኑንና በቀጣይ ለቦርድ በማቅረብ ተፈፃሚ እንደሚሆን ተናግረዋል። ‎ ‎የተቋሙ የራስ ኃይል ግንባታ ክፍል የፀጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ጭምር እየገባ መስራቱን ያወሱት ዋና ሥራ አስፈጻሚው ሆኖም ከፕሮጀክት አፈጻጸም አንጻር ችግሮች ይስተዋሉበት እንደነበረ አስታውሰዋል። ‎ ‎ስለሆነም ክፍሉን ይበልጥ ተወዳዳሪ እንዲሆንና ከሀገር ውጭ እንዲሰራ ጭምር የተቋሙ ሥራ አመራር የሚያደርገውን ክትትልና ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። ‎ ‎በሠራተኛው የተነሱ ጥያቄዎችን እንደ ግብዓት በመውሰድ እንደሚሰራ የጠቆሙት ኢንጂነር አሸብር በተቋሙ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በሚደረገው ጥረት ሠራተኛው በባለቤትነት ስሜትና በቁርጠኝነት ለተቋማዊ ስኬቱ የበኩሉን ሚና እንዲወጣም አሳስበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

photo content
+9

‎ተቋሙ በ2017 በጀት ዓመት የተሻለ አፈጻጸም አስመዝግቧል፤ ‎.....///.... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2017 በጀት ዓመት በበርካታ ፈተናዎች ውስጥ የተሻለ አፈጻጸም ማስመዝገቡን የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጅነር አሸብር ባልቻ ገለጹ። ‎ ‎የተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ ከመ/ቤቱ የሥራ መሪዎች እና ሠራተኞች ጋር በተቋሙ የ2017 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም እና በ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ውይይት እያደረገ ነው። ‎ ‎የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጅነር አሸብር ባልቻ በተቋሙ የ2017 በጀት ዓመት በኃይል ማመንጨትና ማስተላለፍ፣ በኃይል ሽያጭ፣ በፕሮጀክቶች አፈጻጸም፣ በሠው ኃይል ልማት እና በፋይናንስ ዘርፍ እንዲሁም ተቋሙ እያካሄደ ባለው ሪፎርም ዙሪያ የተከናወኑ ሥራዎችን አቀርበዋል። ‎ ‎በበጀት ዓመቱ ለሀገር ውስጥና ለጎረቤት ሀገራት ከቀረበ የኃይል ሽያጭ ከ2016 በጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር ከሦስት እጥፍ በላይ ያለው ገቢ መገኘቱንም ጠቁመዋል። ‎ ‎ይህ ውጤት ሊመዘገብ የቻለው ያረጁ መስመሮችን በመቀየር፣ የጥገናና የኦፕሬሽን ሥራዎችን በማዘመን፣ የውዝፍ ገቢ አሰባሰቡን በማጠናከር፣ የገቢ አማራጮችን በማስፋት፣ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ተርባይኖች ወደ ኦፕሬሽን በማስገባት እና የታሪፍ ማሻሻያ በመደረጉ ነው ብለዋል። ‎ሆኖም በፕሮጀክት አስተዳደር፣  በተለያዩ ወሳኝ የሙያ መስኮች የበቁ ባለሙያዎችን አለማፍራት፣ በቴክኖሎጂ የተደገፉ አሰራሮችን በተሟላ መልኩ አለመተግበር እና በመልሶ ግንባታ ላይ ፈጣን ሥራዎችን ከመስራት አንጻር ክፍተቶች መታየታቸውን አንስተዋል። ‎ ‎ኢንጅነር አሸብር አክለውም ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ስርቆት፣ ከካሳ ክፈያ ጥያቄዎችና በአንዳንደ አካባቢዎች የነበሩ የፀጥታ ችግሮች በበጀት ዓመቱ የገጠሙ ተግዳሮቶች መሆናቸው አብራርተዋል። ‎ ‎በ2017 በጀት ዓመት የነበሩ ጠንካራ ጎኖችን በማጎልበትና ክፍተቶችን በማረም እንዲሁም ጠንካራ የፕሮጀክት ክትትልና ቁጥጥር ሥርዓት በመዘርጋት በ2018 በጀት ዓመት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ይሰራል ብለዋል። ‎ ‎በበጀት ዓመቱ የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት ለካፒታል ወጭዎች፣ ለመደበኛ በጀት እንዲሁም ለወለድ ክፍያ 251 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በጀት እንደተያዘ የጠቆሙት ዋና ሥራ አስፈፃሚው ከዚህ ውስጥ ከ55 በመቶ በላይ የሚሆነውን ከተቋሙ የኃይል ሽያጭና ልዩ ልዩ ገቢዎች ለመሸፈን መታቀዱን ተናግረዋል። ‎ ‎ሕዳሴ እና አሰላ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ እንደሚገቡ የተናገሩት ኢንጅነር አሸብር ቀሪ ፕሮጀክቶችን አፈጻጸም በማሻሻልና ብክነትን በመቀነስ በኩል ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራም ገልጸዋል። ‎ ‎ለዚህም የቦርዱ ሁለንተናዊ ድጋፍ፣ የተቋሙ ሠራተኛና አመራር ቅንጅታዊ አሰራሩን በማሳደግ ለዕቅዱ ስኬት የበኩሉን ሚና እንዲወጣ ጠይቀዋል። ‎ ‎በቀረበው ሪፖርት ላይ ሠራተኞች ጥያቄዎችና አስተያየቶችን እያቀረቡ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

‎ሥራ አመራር ቦርዱ ከተቋሙ ሥራ መሪዎችና ሠራተኞች ጋር ውይይት እያደረገ ነው፤ ‎.....///..... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር ቦርድ ከተቋሙ የሥራ መሪዎች እና ሠራተኞች ጋር በተቋሙ የ2017 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም እና በ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ውይይት እያደረገ ነው። ‎ ‎በውይይቱን ላይ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለጹት ተቋሙ ለሀገር እድገትና ሁለንተናዊ ብልጽግና ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። ‎ ‎የ2017 በጀት ዓመት የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ለምርቃት ዝግጁ ማድረግን ጨምሮ በተቋሙ ድርብርብ ድሎች የተመዘገቡበት ነበር ብለዋል። ‎ ‎ለዚህም የቦርድ ድጋፍና ክትትል እንዲሁም የተቋሙ ሠራተኛና አመራር ያላሳለሰ ጥረት ከፍተኛ ሚና መጫወቱ ገልጸዋል። ‎ ‎የውይይት መድረኩ የ2017 በጀት እቅድ አፈጻጸምን በመገምገም በ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ሠራተኛው የጋራ ግንዛቤ ኖሮት ለተሻለ ለውጥ እንዲተጋ ለማድረግ ያለመ ነው ብለዋል። ‎ ‎በመድረኩ የተቋሙ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ በተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጅነር አሸብር ባልቻ እየቀረበ ነው። ‎ ‎በቀረበው ዕቅድና ሪፖርት ላይ በሠራተኛው ውይይት እንደሚደረግበትና የሥራ አመራር ቦርዱም ቀጣይ የሥራ አቅጣጫ እንደሚሰጥ ይጠበቃል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

የማከፋፈያ ጣቢያው ለከተሞች መስፋፋትና የኢኮኖሚ ዕድገት ሚናው የጎላ ነው …….///……. የራይቱ ማከፋፈያ ጣቢያ በአካባቢው ለሚገኙ ከተሞች መስፋፋትና ለኢኮኖሚ እድገት ከፍተኛ ሚና እየተወጣ መሆኑን በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ባሌ ዞን የራይቱ ወረዳ አስተዳደር አስታወቀ፡፡ የወረዳው አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተሾመ ጉታ እንዳስታወቁት ማከፋፈያ ጣቢያው አገልግሎት መስጠት ከመጀመሩ በፊት ወረዳው ከምሽቱ 12 ሰዓት እስከ ሌሊት 6 ሰዓት ብቻ በነዳጅ መብራት ሲያገኝ ነበር፡፡ በዚህ የተነሳ በአካባቢው የተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች በስፋት ይስተዋሉ እንደነበር አንስተዋል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያው መገንባት ለወረዳዉ ማህበረሰብ የኤሌክትሪክ ኃይል ከማቅረብ ባለፈ የተለያዩ በረከቶችን ይዞ መምጣቱንም አቶ ተሾመ ገልፀዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የወረዳው መቀመጫ ደደቼ በላ ከተማን ጨምሮ በወረዳው ሥር የሚገኙ ስድስት ቀበሌዎች ከማከፋፈያ ጣቢያው አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል በማግኘታቸው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች እየተቃለሉ  መምጣታቸውን ተናግረዋል፡፡ እንደ ኃላፊው ገለጻ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦቱ በወረዳው ኢንቨስትመንትን በመሳብ፤ የተለያዩ መሰረተ ልማቶች እንዲስፋፉ እና የአካባቢው ወጣቶች በተለያዩ የሥራ ዘርፎች እንዲሰማሩ በማስቻል ለከተሞች መስፋፋትና ለአካባቢው ኢኮኖሚያዊ እድገት ከፍተኛ ሚና መጫወቱን አስረድተዋል፡፡ በተጨማሪም የአካባቢው ማህበረሰብ ዘመናዊ የአኗኗር ዘይቤ እንዲከተል እና የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የመረጃ ባለቤት እንዲሆን ማስቻሉን ጠቅሰዋል፡፡ የደደቼ በላ ከተማ ከንቲባ አቶ አወል ኡመር በበኩላቸው የማከፋፈያ ጣቢያው በከተማዋ ላይ መገንባቱ የነዋሪዎች ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ በማድረግ የከተማዋ ወጣቶችን በብረታ ብረት፣ በእንጨት ሥራዎችና በጎሚስታ አገልግሎቶች እንዲሰማሩ በማድረግ የሥራ ዕድል ፈጠራን እያገዘ ስለመሆኑ አብራርተዋል፡፡ ለማህበረሰቡ ኢኮኖሚያዊ እድገት እያደረገ ካለው አስተዋጽዖ ባለፈ ከአካባቢው አየር ፀባይ ጋር በተያያዘ የሚደርሱ ማህበራዊ ችግሮችን በማቃለል የራሱን ሚና እየተወጣ ይገኛል ብለዋል፡፡ ማህበረሰቡ የኤሌክትሪክ ኃይልን ሚና በመገንዘብ መሰረተ ልማቶችን በኃላፊነት እንዲጠብቅ  ከግንዛቤ ማስጨበጫ ጀምሮ የተለያዩ ሥራዎችን ለማከናወን አስተዳደራቸው ቁርጠኛ መሆኑንም የሥራ ኃላፊዎቹ አረጋግጠዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 25 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

ለአካባቢ ጥበቃ ሥራዎች የታየ ቁርጠኝነት - በመትከል ማንሰራራት ........///.......... ‎ ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ የሚገኘውን 7ኛው የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ፕሮጀክቶቹ እና ኃይል ማመንጫዎቹ በሚገኙበት ቦታ ላይም ቀጥሏል። ‎ ‎በዚህም መሰረት የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት፣ የመልካ ዋከና እና የቆቃ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ሠራተኞችና አመራሮችም የችግኝ ተከላ  አከናውነዋል። በኮይሻ ፕሮጀክት ከተቋሙ ሠራተኞች በተጨማሪ የተቋራጩ ዊ ቢዩልድ ሰራተኞች እና የፌደራል ፖሊስ አባላት ተሳትፈዋል። ‎ ‎በመርሀ ግብሩ ላይ የተሳተፉ ሠራተኞችና አመራሮች እንደ ሀገር ለቀረበው ጥሪ በጎ ምላሽ በመስጠት የተቋሙን ተልዕኮ ለማሳካት ችግኝ መትከላቸውን ተናግረዋል። ተቋሙ ከአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂ የተቀዳ የታዳሽ ኃይል አማራጮችን ለመጠቀም እየሰራ ላለው ሥራ የበኩላቸውን ሚና ለመወጣት እድል በማግኘታቸው መደሰታቸውን ገልፀዋል። ‎ ‎የተከሏቸው ችግኞች ለምግብነት የሚውሉ መሆናቸውን የጠቆሙት ተሳታፊዎቹ ከመትከል ባለፈ በመንከባከብ ኃላፊነታቸውን እንደሚወጡም አረጋግጠዋል።  ‎ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 24 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+9

በመትከል ማንሰራራት ........///.......... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምስራቅ ሁለት ሪጅን የሥራ መሪዎች እና ሠራተኞች  በሶማሌ ክልል ምክር ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ ከ1000 በላይ ለምግብነት የሚውሉ ፍራፍሬዎችንና ሀገር በቀል ችግኞችን ተክለዋል፡፡ ሪጅኑ ባለፉት ዓመታት በክልሉ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሮች ላይ በንቃት በመሳተፍ በአካባቢና የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ሥራ ላይ ተጨባጭ ለውጥ እንዲመጣ የጎላ ሚና ተጫውቷል። በችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ ላይ በተቋሙ የምስራቅ ሁለት ሪጅን ዳይሬክተር አቶ አብዱላሂ አብሽርን ጨምሮ የትራንስሚሽን ቢዝነስ የሰው ኃይል አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ተማም አፍደል እና የማዕከላዊ ሦስት ሪጅን ዳይሬክተር አቶ እስማኤል ሙዘይን ተሳትፈዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በደቡብ ሁለት ሪጅን የኢትዮ ኬንያ ኮንቨርተር ጣቢያ ሰራተኞች ለሰባተኛ ጊዜ በተካሄደው የአረንጓዴ አሻራ  መርሃግብር ላይ ተሳትፈዋል። በመርሃግብሩ ላይ የትራንስሚሽን ቢዝነስ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አንዷለም ሲአ ተሳትፈዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 24 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6