uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 559 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 384-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 165-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 559 obunachiga ega bo‘ldi.

23 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 0 ga, so‘nggi 24 soatda esa -2 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 25.89% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 15.48% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 4 026 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 408 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 9 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
EEP Communication

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 24 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 559
Obunachilar
-224 soatlar
-37 kunlar
Ma'lumot yo'q30 kunlar
Postlar arxiv
photo content
+6

የመንግስት እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ለሕዝብ አገልግሎት ዝግ የሚሆኑባቸው በሀገርአቀፍ ደረጃ ተከብረው የሚውሉ ብሔራዊ በዓላት ፡- 1. መስከረም 1 ቀን የዘመን መለወጫ (እንቁጣጣሽ) በዓል 2. የካቲት 23 ቀን የአድዋ ድል በዓል 3. ሚያዚያ  23 ቀን የዓለም የሠራተኞች (የላብአደሮች) ቀን 4. ሚያዚያ  27 ሰባት ቀን የአርበኞች (የድል) ቀን በዓል የሚከተሉት በዓላት በሀገርአቀፍ ደረጃ ታስበው የሚውሉ ብሔራዊ በዓላት ናቸው ፡- 1. የካቲት 12 ቀን የሰማዕታት ቀን 2. ሕዳር 29 ቀን የኢትዮጵያ ህብረ-ብሄራዊነት (የብሔር ብሔረሰቦች) ቀን በተጠቀሱት ብሔራዊ በዓላት የመንግስት እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ለሕዝብ አገልግሎት ክፍት ይሆናሉ፡፡ የሚከተሉት በዓላት በሀገርአቀፍ ደረጃ የሚከበሩ ሃይማኖታዊ በዓላት ናቸው :: 1. መስከረም 17 ቀን የመስቀል በዓል 2. በየአራት ዓመቱ የሚመጣው ልዩነት እንደተጠበቀ ሆኖ ታህሳስ 29 ቀን የሚውለው የገና ወይም የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል 3. ጥር 11 ቀን የጥምቀት በዓል 4. የስቅለት በዓል 5. የትንሳኤ (ፋሲካ) በዓል 6. የኢድ-አልአድሃ (አረፋ) በዓል 7. የመውሊድ በዓል 8. የኢድ አልፈጥር በዓል በተጠቀሱት ሃይማኖታዊ በዓላት የመንግስት እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ለሕዝብ አገልግሎት ዝግ ይሆናሉ። ግንቦት 20 ግን የሕዝብ በዓላትን እና የበዓላትን አከባበር ለመወሰን በወጣው አዋጅ ውስጥ አልተካተተም። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 19 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

#ExamResult የፈተና ውጤት ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር-4ኛ የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር መጋቢት 22 ቀን 2017 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወቃል፡፡
+1
#ExamResult የፈተና ውጤት ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር-4ኛ የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር መጋቢት 22 ቀን 2017 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወቃል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁ ተወዳዳሪዎች መካከል በተሰጠው የተግባር ፈተና ከተራ ቁጥር 1 እስከ ተራ ቁጥር 10 ስማችሁ የተገለጸው ተወዳዳሪዎች ከግንቦት 20 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 (አምስት) የስራ ቀናት ውስጥ ኮተቤ በሚገኘው በዋናው መ/ቤት የሰው ኃይል ምደባ ቢሮ በመገኘት የትምህርት ማስረጃ፣ የስራ ልምድ ዋናውን እና ኮፒ በመያዝ ቀርባችሁ የቅጥር ሂደት እንድትፈጽሙ እናሳውቃለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 19 ቀን 2017 ዓ.ም

የኃይል አቅርቦቱ የከተሞችን ሁለንተናዊ ዕድገት እያፋጠነ ነው .......///........ የኃይል አቅርቦት አስተማማኝነት የከተሞችን ሁለንተናዊ ዕድገት እያፋጠነ መሆኑን የአዳማ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የሞጆ ከተማ ከንቲባ ገለጹ። የአዳማ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ንጋቱ ሞቱማ እንደገለጹት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የገነባቸውና የሚያስተዳድራቸው የንፋስና የውኃ ኃይል ማመንጫዎች እንዲሁም የተለያየ የቮልቴጅ መጠን ያላቸው ማከፋፈያ ጣቢያዎች በከተማዋ ዙሪያ ይገኛሉ። ተቋሙ የገነባቸው እነዚህ የኃይል መሰረተ ልማቶች የአካባቢውን የኃይል አቅርቦት በማሳደግ አዳማ ከተማን የኢንዱስትሪና የኮንፈረንስ ማዕከል እንዳደረጋት ተናግረዋል። እንደ ምክትል ከንቲባው ገለፃ አሁን ላይ በከተማዋ አስተማማኝ ኃይል በመኖሩ በርካታ ዜጎችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚ የሚያደርጉና ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያላቸው ፋብሪካዎችን ጨምሮ ትልልቅ ኢንቨስትመንቶች ወደ ሥራ እየገቡ ነው። ለአዳማ ከተማ ነዋሪዎች ለመጠጥ እየዋለ ያለውን ውኃ ከቆቃ የኃይል ማመንጫ ግድብ እንደሚያገኙ የተናገሩት ምክትል ከንቲባው የኃይል መሰረተ ልማቶቹ ንጹህ የመጠጥ ውኃን ተደራሽ ከማድረግ ባለፈ የማህበረሰቡን የአኗኗር ዘይቤ በማዘመን በኩል ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ መሆኑንም አብራርተዋል። አስተዳደራቸው በኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀሙ ስርቆቶችን ከተቋሙ ጋር ያለውን ቅንጅታዊ አሰራር በማጠናከር ለመከላከል እንደሚሰራ በመግለፅ ቀጣይ የከተማዋን ዕድገት ታሳቢ ያደረገ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ተቋሙ በትኩረት እንዲሰራም ጠይቀዋል። የሞጆ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ገዛሊ ሀሹ በበኩላቸው ከተማዋ የሎጅስቲክስና የኢንዱስትሪ ማዕከል በመሆኗ እና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት በመኖሩ የኢንቨስትመንት ፍሰቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል ብለዋል። ቀደም ሲል በከተማዋ ላይ ኢንቨስት ያደረጉ ከ300 በላይ ባለሃብቶች ከ30 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን ነው የተናገሩት። በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው በርካታ የኢንቨስትመንት ጥያቄዎች ለከተማ አስተዳደሩ ቀርበው በሂደት ላይ እንደሚገኙ ጠቁመዋል። ለገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በከተማዋ አቅራቢያ እየተገነባ መሆኑን የጠቆሙት ከንቲባው በቀጣይም የከተማዋን ፈጣን እድገት የሚያስቀጥል የኃይል አቅርቦት እንዲኖር የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል። የከተማው ነዋሪ፣ የፋብሪካ ባለቤቶች እንዲሁም ከተማ አስተዳደሩ ለሚያቀርበው የኃይል ፍላጎት ጥያቄ ተቋሙ እየሰጠ ላለው ምላሽ ምስጋና አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥጌ/ሞመ ግንቦት 19 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

#ዜናእረፍት! ዜና እረፍት! በተቋሙ የጀነሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ ሥራ ባልደረባ የነበሩት አቶ ጌትነት በቀለ ባደረባቸው ህመም በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ህክምና ሲከታተሉ ቆይተው ከዚህ ዓለም በሞት በመለየታቸው ተቋሙ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ይገልፃል፡፡ አቶ ጌትነት በቀለ ከአባታቸው ከአቶ በቀለ ወልደአማኑኤል እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ሲደልለኝ ተመቸ በአዲስ አበባ ጉለሌ ክ/ከተማ መስከረም 21 ቀን 1968 ዓ.ም ተወለዱ። ከ1972 እስከ 1985 ዓ.ም ድረስ የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአዲስ አበባ ቀጨኔ ደብረ ሠላም፣ ወ/ሮ ቀለመወርቅ ጥሩነህ፣ ኢትዮጵያ ትቅደም እና ጀኔራል ዊንጌት ት/ቤቶች ተከታትለዋል። በ1990 ዓ.ም በተቋሙ ማሰልጠኛ ለ6 ወራት በኤሌክትሮ ሜካኒክ የሙያ መስክ ሥልጠና ወስደው ታህሳስ 18 ቀን 1990 ዓ.ም በቆቃ ኃይል ማመንጫ ሥራ መጀመራቸውን የግል ማህደራቸው ያስረዳል፡፡ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዳማ ሣይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በኤሌክትሪካል (ኤሌክትሮኒክስ) ቴክኖሎጂ በ1999 ዓ.ም ያገኙት አቶ ጌትነት ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ደግሞ በ2014 ዓ.ም ከጅማ ዩኒቨርሲቲ በኤሌክትሪካል ፓወር ምህንድስና አጠናቀዋል። አቶ ጌትነት ላለፉት 27 ዓመታት በባለሙያነትና በተለያዩ የሥራ ኃላፊነቶች ተቋሙን በቅንነት፣ በታማኝነት፣ በታታሪነት ሲያገለግሉ የቆዩ ሲሆን በባህሪያቸውም እጅግ በጣም ትሁት፣ ሰው አክባሪ፣ ጥሩ ሥነ-ምግባርን የተላበሱ ትጉህ ሠራተኛ ነበሩ። አቶ ጌትነት በተቋሙ የጀነሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ የክላስተር አንድ የኃይል ማመንጫዎች መምሪያ ዳይሬክተር ሆነው ሲያገለግሉ ቆይተዋል። አቶ ጌነትነት ባደረባቸው ህመም ምክንያት በተወለዱ በ49 ዓመታቸው ግንቦት 17 ቀን 2017 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩ ሲሆን የቀብር ሥነ-ሥርዓታቸውም በዛሬው ዕለት ግንቦት 18 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8 ሰዓት በአቃቂ ቃሊቲ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ-ክርስቲያን ይፈፀማል፡፡ አቶ ጌትነት ባለትዳርና የሦስት ልጆች አባት ነበሩ። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በአቶ ጌትነት በቀለ ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን በድጋሜ እየገለፀ ለቤተሰቦቹ እና ወዳጅ ዘመዶቹ መፅናናትን ይመኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥጌ/ሞመ ግንቦት 18 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

የኃይል አቅርቦት ያልተዳረሰባቸውን አካባቢዎች ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ነው ….....///….... የኃይል አቅርቦቱ ያልተዳረሰባቸውን አካባቢዎች ተደራሽ የሚያደርጉ የኃይል መሰረተ ልማቶች ግንባታ እያከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ። በተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን እንደተናገሩት እስከ አሁን ምንም ዓይነት የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ያልተገነባባቸውና የኃይል አቅርቦቱ ያልተዳረሰባቸው አካባቢዎች አሉ። የተደራሽነት ችግርን ለመቅረፍ የሚገነቡት የማከፋፈያ ጣቢያዎችና የማስተላለፊያ መስመሮች እስከ አሁን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ያልነበሩ አካባቢዎችን ታሳቢ ያደረጉ መሆናቸውን ጠቁመዋል። የደብባዊ ግሪድ ማስፋፈያ ፕሮጀክት አካል የሆኑት የሺግዳን እና ቲርጋ የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶችን ጨምሮ የተደራሽነት ሽፉኑን የሚያሳድጉ የኃይል መሰረተ ልማት ግንባታዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን ለአብነት ጠቅሰዋል። እንደ ሀገር ያለውን 54 በመቶ የኤሌክትሪክ ሽፋን ወደ 78 በመቶ ለማሳደግ ተቋሙ ዕቅድ ነድፎ እየሰራ ስለመሆኑ አብራርተዋል። ቀሪ አካባቢዎች ከግሪድ ጋር ባልተገናኘ መንገድ ኃይል የሚያገኙበትን አቅጣጫ መቀመጡንም ተናግረዋል። እንደ አቶ ሞገስ ገለፃ ተቋሙ የኤሌክትሪክ ተደራሽነት ሽፋንን የሚያሰፉ አዳዲስ የማከፋፈያ ጣቢያዎችንና ማስተላለፊያ መስመሮችን ከመገንባት በተጓዳኝ ተጨማሪ የኃይል ፍላጎት ባለባቸው አካባቢዎች የአቅም ማሳደግ እና የማዘመን ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከ20 ሺ 650 ሰርኪዩት ኪሎ ሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው 307 የማስተላለፊያ መስመሮችን እንዲሁም 194 ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ያስተዳድራል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥጌ/ሞመ ግንቦት 18 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ማከፋፈያ ጣቢያው የኃይል ብክነትን በማስወገድ አስተማማኝ ኃይል እያቀረበ  ነው .....///...... የአዳማ አንድ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ የኃይል ብክነትን በማስወገድ አስተማማኝ ኃይል እያቀረበ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለጹ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ብርሃኑ ቦንገር እንደገለፁት ጣቢያው ለአዳማ ከተማ እንዲሁም የአዳማ ቆርቆሮን ጨምሮ በዙሪያዋ ለሚገኙ በርካታ ፋብሪካዎች ኃይል እያቀረበ ይገኛል። ከከተማዋ መስፋፋትና ከኢንዱስትሪዎች ፍሰት መጨመር ጋር ተያይዞ እየቀረበ ያለውን የኃይል ጥያቄ ለመመለስ ተጨማሪ ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፔር ተንቀሳቃሽ የማከፋፈያ ጣቢያ  እንደተተከለለት ተናግረዋል። በዚህም ከ80 ሜጋ ዋት በላይ በመጫን ቀደም ሲል ጣቢያው የነበሩትን ሰባት ወጭ መስመሮች ወደ 13 በማሳደግ ለአዳዲስ እና ተጨማሪ ኃይል ለሚጠይቁ ነባር ደንበኞች አስተማማኝ ኃይል ማቅረብ እንደተቻለ  ጠቁመዋል። ለደንበኞች ያልተቆራረጠ ኃይል ለማቅረብ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አዳማ ዲስትሪክት ጋር በመተባበር የስካዳ ሥርዓት መተግበሩንም ገልጸዋል። ቀደም ሲል ጣቢያው ከ90 በመቶ በላይ የአዳማን የኃይል ፍላጎት ሲያሟላ መቆየቱን ያስታወሱት ሥራ አስኪያጁ አሁን ላይ የአዳማ ሁለት ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ተገንብቶ ወደ ሥራ በመግባቱ በጣቢያው ላይ የነበረውን ጫና እንዲቀንስ አድርጎታል ብለዋል። የጣቢያውን ኃይል ጭነት እና ፍሰት የሚቆጣጠሩና ብክነትን የሚቀንሱ ሦስት "ፓወር ሪአክተሮች" መተከላቸውን አቶ ብርሃኑ አስረድተዋል። የማከፋፈያ ጣቢያውን ደህንነት ለማረጋገጥ የመቆጣጠሪያ ክፍሉን የማሻሻልና የማዘመን ሥራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውንም ተናግረዋል። የመቆጣጠሪያ ቅየራው ክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች አስተባባሪ አቶ ክብሮም በረኼ በበኩላቸው የጣቢያው የመቆጣጠሪያ ሥርዓቶች ረጅም ዓመት ያገለገሉ ከመሆናቸው ጋር ተያይዞ ሲ ዋይ ጂ በተባለ የቻይና ኩባንያ አማካኝነት በአዲስ መልክ የመቀየር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን አብራርተዋል። ይህም በተለያየ ምክንያት ሊያጋጥሙ የሚችሉ አደጋዎችን በመከላከል የኃይል መቆራረጡን ለማስወገድ እና የቁጥጥር ሥርዓቱን ለማዘመን እንደሚያስችል አስረድተዋል፡፡ አዳማ አንድ ማከፋፈያ ጣቢያ ከአዋሽ ሰባት፣ ከቆቃ እና ከአዳማ 2 ንፋስ ኃይል ማመንጫዎች ኃይል ይቀበላል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥጌ/ሞመ ግንቦት 16 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+8

ፆታ ተኮር ጥቃትን መከላከል የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት ሊሆን ይገባል ……////……. ፆታ ተኮር ጥቃትን መከላከል የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት ሊሆን እንደሚገባ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሴቶች ሕፃናትና ወጣቶች ጉዳይ መምሪያ አስታወቀ፡፡ መምሪያው ከሪጅኖች፣ ከኃይል ማመንጫዎች  እና ከዋናው መስሪያ ቤት ለተውጣጡ ሠራተኞች በሥርዓተ ፆታ እና ልማት እንዲሁም በፆታ ተኮር ጥቃት ላይ ያተኮረ ሥልጠና በተቋሙ መሰብሰቢያ አዳራሽ ሰጥቷል። ሥልጠናውን በንግግር ያስጀመሩት የሴቶች ሕፃናትና ወጣቶች ጉዳይ መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ እንደገለፁት ፆታ ተኮር ጥቃቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚፈፀሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ናቸው፡፡ የሴቶችን መብት ለማስከበር በርካታ የህግና የፖሊሲ ማዕቀፎች በሥራ ላይ እንደዋሉ የጠቆሙት ዳይሬክተሯ ይሁን እንጂ ከጊዜ ወደ ጊዜ በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ ፆታዊ ጥቃቶችን በሚፈለገው ደረጃ ማስቆም እንዳልተቻለ ተናግረዋል፡፡ የሥልጠናው ተሳታፊዎች በአካባቢያቸውና በሥራ ቦታቸው ላይ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ በመገንዘብ ፆታ ተኮር ጥቃቶችን እንዲከላከሉና የግንዛቤ ፈጠራ ሥራዎችን እንዲያከናውኑ ዕድል ይሰጣል ብለዋል፡፡ ሥልጠናው ፆታ ተኮር ጥቃት የሚደርስባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች የህግ፣ የሥነ-ልቦና እና ጤና ነክ ድጋፎችን እንዲያገኙ የማመቻቸት ሥራ እንዲሰሩ እንደሚያግዛቸውም ነው ያብራሩት፡፡ እንደ ዳይሬክተሯ ገለፃ የሥልጠናው ተሳታፊዎች ሥርዓተ ፆታ ከልማት ጋር ያለውን ትስስርና የሚያመጣውን ሁለተናዊ ዕድገት በመረዳት የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የግንዛቤ ፈጠራ ሥራዎችን ይሰራሉ፡፡ በተቋሙ የካሳ ጉዳዮች አስተዳደር ሥራ አስኪያጅ አቶ ደረጄ አጥናፌ በሥልጠናው ላይ እንደገለፁት ጥቃት ሰዎች ሰው በመሆናቸው ብቻ የተጎናፀፏቸውን እና በተለያዩ ዓለም አቀፍ ሰነዶች እውቅና የተሰጣቸውን ሰብዓዊ መብቶች የሚጥስ ድርጊት ነው፡፡ ፆታ ተኮር ጥቃት በሰዎች ላይ አካላዊ፣ ወሲባዊ እና ሥነ-ልቦናዊ ችግሮችን የሚያስከትል ፆታን መሰረት አድርጎ የሚፈፀም የኃይል ድርጊት መሆኑንም ነው የገለፁት፡፡ እንደ አቶ ደረጄ ገለፃ ያልተፈለገ እርግዝና፣ የአባላዘር በሽታ፣  የቤተሰብ ግጭት፣ አካላዊ እና ሥነ ልቦናዊ ጉዳቶች እንዲሁም ሞት የፆታ ተኮር ጥቃት ውጤቶች ናቸው፡፡ መንግሥትም ሆነ ተቋማት ፆታ ተኮር ጥቃቶች ላይ የተደነገጉ ህጎችን ወደ ተግባር በመቀየር ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚጠብቅባቸው አፅዕኖት ሰጥተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 15 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቱ ኃይል ማመንጨት ጀመረ .........///........ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በሦስት ተርባይኖች ኃይል ማመንጨት ጀምሯል። የፕርጀክቱን የግንባታ ሂደት እና የኃይል ማመንጨት የመጀመር ሥራ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሰመሪታ ሰዋሰው፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ፣ የደንማርክ አምባሳደር ሚስተር ሱነ ክሩግስትረፕ፣ የአውሮፓ ህብረት እና ፕሮጀክቱን ፋይናንስ የሚያደረገው የዳኒሽ ባንክ ተወካዮች ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ ላይ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሰመሪታ ሰዋሰው እንደተናገሩት ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነትን ለማሳደግ እና የኃይል ስብጥርን ለማመጣጠን ትኩረት ሰጥታ እየሰራች ነው። የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትም ኢትዮጵያ የኃይል ስብጥር ላይ ትኩረት ለማድረጓ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ የአውሮፓ ህብረትና የደንማርክ መንግስትም በኃይል ልማት ዘርፉ ላይ እያደረጉት ካለው ድጋፍ ባለፈ ለሌሎች መሠረተ ልማቶች ድጋፍ በማድረግ ለሀገሪቱ እድገት የበኩላቸውን እየተወጡ ይገኛሉ ነው ያሉት። የትብብር ሥራው ታዳሽ ኃይል ወደ ግሪድ በማስገባት የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ለማሳደግ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እንደሚያስችል ተናግረዋል፡፡ በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት ተወካይ ሚስተር ቪንሰንት ቪያዉድ በበኩላቸው አሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ኢትዮጵያ ለታዳሽ ኃይል ልማት ለሰጠችው ትኩረት አመላካች መሆኑን ገልፀዋል። በቀጣይ ኢትዮጵያ በኃይል ልማት ዘርፉ ለምታከናውናቸው ሥራዎች ህብረቱ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በኢትዮጵያ የደንማርክ አምባሰደር ሚስተር ሱነ ክሩግስትረፕ እንደተናገሩት የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በኢትዮጵያና በደንማርክ መካከል ያለውን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግረዋል ብለዋል፡፡ ሀገራቸው በንፋስ ኃይል ማመንጫ ያላትን ተሞክሮ ለኢትዮጵያ ብሎም ለአፍሪካ እያካፈለች እንደምትገኝ ገልፀው የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ላይ ያደረገችው ድጋፍም ለዚሁ ማሳያ መሆኑን ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማምጣት የኃይል መሠረተ ልማት ቁልፍ መሳሪያ እንደሆነ  በመገንዘብ የደንማርክ መንግስት  ለፕሮጀክቱ ካደረገው የመዋዕለ ነዋይ ድጋፍ በተጨማሪ የግንባታ ሥራውን በቅርበት ሲከታተል እንደነበር አስታውሰዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደተናገሩት በሀገሪቱ ያለውን የኃይል ተደራሽነት ለማስፋፋት በርካታ ፕሮጀክቶች እየተገነቡ ይገኛሉ። የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ማመንጨት እንዲጀምር የአውሮፓ ህብረትና የደንማርክ መንግስት ላደረጉት ድጋፍም ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ ጉብኝቱ ለፕሮጀክቱ ድጋፍ ያደረጉ አካላት ፕሮጀክቱ የደረሰበትን የግንባታ እና የመጀመሪያውን ኃይል የማመንጨት ሂደት በማየት ለቀሪ ሥራዎች አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ያለመ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡ ጉብኝቱ በቀጣይ በአካባቢው ለመገንባት ለታሰበው ተመሳሳይ ፕሮጀክት ድጋፍ የሚያደርጉበትን ዕድል እንደሚፈጥርም ዋና ሥራ አስፈፃሚው ተናግረዋል፡፡ በዕለቱ ፕሮጀክቱ ስለደረሰበት ሂደትና ስለተከናወኑ ዋና ዋና ሥራዎች እንዲሁም በግንባታ ሂደት እያጋጠሙ ስላሉ ችግሮች በፕሮጀክቱ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ገለፃ ተደርጓል። ፕሮጀክቱ ከሚኖሩት 29 ተርባይኖች መካከል ዛሬ ሦስቱ ኃይል ማመንጨት የጀመሩ ሲሆን በቀጣይም ሌሎቹ ተርባይኖች ኃይል ወደማመንጨት ሥራ እንደሚገቡ ይጠበቃል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስና ትክክለኛ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 14 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

photo content
+9

የዋና መሥሪያ ቤት ህንፃ ግንባታ ዓለም አቀፍ ጨረታ ወጣ .......///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በአዲስ አበባ ሜክሲኮ አካባቢ ለሚያስገነባው ባለ 66 ወለል ዘመናዊ የዋና መሥሪያ ቤት ሕንፃ ዓለም አቀፍ  ጨረታ አውጥቷል። አጠቃላይ ግንባታው በ20 ሺህ 792 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የሚያርፍ ሲሆን ሲጠናቀቅ 208 ሺህ 724 ካሬ ሜትር የሆነ አጠቃላይ የወለል ስፋት እና 345 ነጥብ 5 ሜትር ከፍታ ይኖረዋል። በአዲስ አበባ የፋይናንስ ማዕከል ተብሎ በተለየው በሜክሲኮ የሚገነባው ይህ ግዙፍ ሕንፃ ዲዛይኑ በተቋሙ እና በአማካሪ ድርጅት በኩል የተዘጋጀ ሲሆን አሸናፊው ተቋራጭ ግንባታውን ብቻ የሚያከናውንበት የውል ዓይነት ነው። የወጣው ጨረታ የግንባታውን የስራ ዝርዝር እና ግንባታውን ለማከናወን ተቋራጮች ሊያሟሉት የሚገባውን የፋይናንስና የቴክኒክ መስፈርት በዝርዝር የሚያመለክት ነው። በዚህ መሰረት ተጫራቾች ያለፉትን አምስት ዓመታት የኦዲት ሪፖርታቸውን እንዲሁም በአማካይ ቢያንስ 230 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ዓመታዊ ገቢ ማቅረብ እንደሚጠበቅባቸው የጨረታ ሰነዱ ያመለክታል። ከቴክኒክ አንፃር ደግሞ ቢያንስ ለ10 ዓመታት በግንባታ ላይ ልምድ ያላቸውና እያንዳንዳቸው ቢያንስ 370 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ዋጋ ያላቸው ሦስት ፕሮጀክቶችን በተሳካ ሁኔታ ያጠናቀቁ መሆን ይኖርባቸዋል። የንድፍ እና የግንባታ ክትትል አማካሪ በመሆን ዳር አል-ሃንዳሳ ነው። የግንባታውን ወጪ በተለያዩ የፋይናንስ አማራጮች ለመሸፈን ተቋሙ አማራጮችን እያየ  ሲሆን የጨረታው ሂደት እንደተጠናቀቀ አጠቃላይ የግንባታው ዋጋ የሚገለጽ ይሆናል። በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገፆች  ስለግንባታው ወጪና ሌሎች መረጃዎች የወጡት መረጃዎች በተቋሙ በኩል ያልወጡና የተሳሳቱ እንደሆኑ ለመግለጽ እንወዳለን። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስና ትክክለኛ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 13 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

“እንደ ሀገር ያለን ብቸኛ አማራጭ ለተጨማሪ ስኬት መትጋት ነው” ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) …///… ኢትዮጵያ እንደ ሀገር እና ህዝብ ያላት ብቸኛ አማራጭ የተገኙ ስኬቶችን በማፅናት ለተጨማሪ ድል መትጋት መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ 1፣ 2 እና 3 ሪጅኖች እና የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ሠራተኞች "የመሐሉ ዘመን" በሚል መሪ ሀሳብ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ውይይት አካሂደዋል። በመድረኩ "የመሐሉ ዘመን" ወጥመዶች እና የመሻገር ሂደቶችን የሚዳስስ ሰነድ በኮሚሽነር ዘለቀ የቀረበ ሲሆን በኢትዮጵያ ባለፉት ሰባት ዓመታት በኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ዘርፎች የተመዘገቡ ስኬቶች፣ የድህረ ለውጡ መሰናክሎች፣ የዓለምአቀፉ የኃይል አሰላለፍ እንዲሁም በመንግስት የተወሰዱ እርምጃዎች እና የታዩ ክፍተቶችን ዳሰዋል፡፡ ስኬት ቀጣይነት ባለዉ ትጋት የማይታጀብ ከሆነ ውድቀት አይቀሬ ነው ያሉት ኮሚሽነሩ ጊዜያዊ ስኬት ብቻውን ለሀገራዊ ድል ዋስትና ሆኖ ሊቆይ እንደማይችል ገልፀው የመሐሉ ዘመን የተሟላ ስኬት ላይ ያልደረስንበት መሆኑ መታወቅ አለበት ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ በለውጥ ሂደት በርካታ ተፈጥሯዊ እና ሰው ሠራሽ ፈተናዎችን መሻገሯን የጠቀሱት ኮሚሽነሩ ድርቅ፣ ጎርፍ፣ የበረሃ አንበጣ፣ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ እንዲሁም የእርስ በርስ ግጭትና መፈናቀል ለውጡን የፈተኑ ጉዳዮች መሆናቸውን ለአብነት አንስተዋል። የሕዝብ ጥያቄዎችን በመመለስ፣ የትርክት ለውጥ በማምጣት፣ አካታች ፖለቲካዊ አጀረጃጀት እና ኢኮኖሚያዊ ሪፎርም በመተግበር ስኬት ማስመዝገብ መቻሉን ገልፀዋል። ለውጥ የአንድ ተቋም ወይም ግለሰብ ብቻ እንዳልሆነ የጠቀሱት ኮሚሽነር ዘለቀ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኃይል ልማት ዘርፉ እያከናወናቸው የሚገኙትን የለውጥ ሥራዎች ቀጣይነት ባለው መልኩ በማሳለጥ የኤሌክትሪክ አቅርቦቱን ለማሻሻል መስራት እንደሚገባው ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ፋይናንስና ኃብት አስተዳደር ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ በበኩላቸዉ 55 በመቶ የደረሰውን የኤሌክትሪክ አቅርቦት ሽፋን ለማሳደግ ለኢትዮጵያ ተጨማሪ ህዳሴ እንደሚያስፈልጋት ገልፀዋል፡፡ እንደ አቶ ደመረ ገለፃ በኃይል አቅርቦት ዘርፍ ከተሰማሩ ሌሎች ተቋማት ጋር በመተባበር እና በመደጋገፍ ለላቀ ስኬት መስራት ለነገ የማይባል ጉዳይ ነው፡፡ በውይይት መድረኩ ላይ በኢትዮጵያ ኢንሸስትመንት ሆልዲንግ የኢነርጂ ዘርፍ ዳይሬክተር ጌትነት መላክ (ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ፋይናንስና ኃብት አስተዳደር ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ፣ የዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝን ጨምሮ ከአዲስ አበባ ሪጅኖቹ እና ከብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል የተውጣጡ ሠራተኞች እና አመራሮች ተሳትፈዋል፡፡ ከዚህ በፊት ከዋና መስሪያ ቤት ሠራተኞች ጋር ተመሳሳይ ውይይት መካሄዱ የሚታወስ ነው፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ኑሀ/ፍጌ ግንቦት 13 ቀን 2017 ዓ.ም