uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 692 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 024-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 156-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 692 obunachiga ega bo‘ldi.

28 Avgust, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 137 ga, so‘nggi 24 soatda esa -5 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 35.24% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 17.40% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 5 528 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 730 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 12 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
EEP Communication

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 29 Avgust, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 692
Obunachilar
-524 soatlar
-17 kunlar
+13730 kunlar
Postlar arxiv
ተቋሙ በቢሾፍቱ ከተማ የሚያስገነባውን የስልጠና ማዕከል ፕሮጀክት ለመጀመር የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ ...…///….... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቢሾፍቱ ከተማ የሚ
+8
ተቋሙ በቢሾፍቱ ከተማ የሚያስገነባውን የስልጠና ማዕከል ፕሮጀክት ለመጀመር የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ ...…///….... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቢሾፍቱ ከተማ የሚያስገነባውን የስልጠና ማዕከል እና የአቅም ግንባታ ፕሮጀክት ሥራን ለመጀመር የሚያስችሉ የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን የፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ አቶ እንዳለ የሺጥላ ገለጹ።  አቶ እንዳለ እንደገለጹት ፕሮጀክቱ የተቋሙን የሰው ሀብት ሥራ አመራርና የስልጠና አቅርቦት በማዘመን እንዲሁም በዘመናዊ መሠረተ ልማቶችና ቴክኖሎጂዎች የተሟላ የማሰልጠኛ ማዕከል በመገንባት ተቋማዊ አቅምን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ያለመ ነው። ፕሮጀክቱ በተቋሙ በብቃት ላይ የተመሠረተ የሰው ሀብት ሥራ አመራር ሥርዓት ለመዘርጋት፣ በሁሉም የሥራ ክፍሎች የሥርዓተ-ፆታ አካቶን ለማዳበር እንዲሁም የማዕከሉን አገልግሎት በኃይል ዘርፉ ለተሰማሩ የሀገር ውስጥና የውጭ አካላት ክፍት በማድረግ በኢትዮጵያና በቀጣናው ተመራጭ ለመሆን ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወትም ሥራ አስኪያጅ ገልጸዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-በቢሾፍቱ-ከተማ-የሚያስገነባውን-የ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ-ገጽ https://www.eep.com.et ሐምሌ 01 ቀን 2018 ዓ.ም

‹‹ድንበር ተሻጋሪ የኃይል ንግድን ለማሳለጥ የሚያስችሉ መሠረተ ልማቶች ተጠናቀዋል›› ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ...////… ድንበር ተሻጋሪ የኤሌክትሪክ ኃይል ንግድን ለማሳለጥና ቀጣናዊ ትስስሩን ለማ
+3
‹‹ድንበር ተሻጋሪ የኃይል ንግድን ለማሳለጥ የሚያስችሉ መሠረተ ልማቶች ተጠናቀዋል›› ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ...////… ድንበር ተሻጋሪ የኤሌክትሪክ ኃይል ንግድን ለማሳለጥና ቀጣናዊ ትስስሩን ለማጠናከር የሚያስችሉ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች መጠናቀቃቸውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ እና የምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር የሥራ አስፈፃሚዎች ኮሚቴ ሰብሳቢ አስታወቁ፡፡ 37ኛው የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር የአመራር ኮሚቴ ልዩ ስብሰባ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው፡፡ ስብሰባው በአባል ሀገራቱ በቀረቡት የመንግሥታት እና የተቋማት የጋራ መግባቢያ ስምምነቶች እንዲሁም ተያያዥ የአስተዳደር ሰነዶች ማሻሻያ ሐሳቦች ላይ ለመምከር ያለመ ነው፡፡ በስብሰባው ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ እና የወቅቱ የምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር የሥራ አስፈፃሚዎች ኮሚቴ ሰብሳቢ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በአባል ሀገራቱ መካከል የኤሌክትሪክ ኃይል እጥረትን በመቅረፍ አስተማማኝና ቀጣይነት ያለው የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ለማስቻል ይሰራል ብለዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ድንበር-ተሻጋሪ-የኃይል-ንግድን-ለማሳ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ-ገጽ https://www.eep.com.et ሐምሌ 01 ቀን 2018 ዓ.ም

37ኛው የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር የሥራ አስፈጻሚዎች ኮሚቴ ልዩ ስብሰባ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል                               …///… የምስራቅ አፍሪካ ሀገራትን የኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማት እርስ በርስ በማገናኘት ቀጣናዊ የኃይል ትስስር ለመፍጠር የተቋቋመው የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር የሥራ አስፈጻሚዎች ኮሚቴ 37ኛውን ልዩ ስብሰባ በአዲስ አበባ እያካሄደ ነው፡፡ በስብሰባው ላይ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ክቡር ዶ/ር ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ፣ የምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር ዋና ጸሐፊ ኢንጂነር ጄምስ ዋሆጎና የኮሚቴ አባላት እንዲሁም ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች  እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡ ስብሰባው የሰው ኃብትና አስተዳደር ኮሚቴ እንዲሁም የሕግ ባለሙያዎች በቀደሙት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔዎች መሠረት በውስጣዊ የመንግስት እና   የአገልግሎት መግባቢያ ሰነዶች ላይ ያዘጋጁትን የማሻሻያ ረቂቆች  የደረሱበትን ደረጃ የሚገመግም ይሆናል፡፡ የተዘጋጁ የማሻሻያ ረቂቆች በሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ከታዩ በኋላ ሐምሌ 3 እና 4 ቀን 2018 ዓ.ም በፑሉ የወደፊት አስተዳደር እና በቀጠናዊ የኤሌክትሪክ ገበያ ሥራ ማስጀመር ላይ  በሚካሄደው 22ኛው የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ የሚቀርቡ ምክረ ሀሳቦችን እንደሚያዘጋጅ ይጠበቃል። የምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር የሥራ አስፈጻሚዎች ኮሚቴ ሰብሳቢነትን የአባል ሀገራቱ የኢነርጂ ዘርፍ ተቋማት በየተራ የሚመሩት እንደሆነ ይታወሳል፡፡ ኢትዮጵያ የምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር የስትሪንግ  ኮሚቴ መሪነቱን ከኬንያ በመረከብ ለቀጣይ አንድ ዓመት የምታስተዳድር ስትሆን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አሸብር ባልቻ (ኢንጂነር)  ደግሞ የሥራ አስፈጻሚ  ኮሚቴው ሰብሳቢ በመሆን ፑሉን ይመራሉ፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+3

ተቋሙ የቴክኒሺያኖች አቅም ለማጎልበት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል፤ …….///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሲቪል እና ኤሌክትሮ ሜካኒካል ቴክኒሽያኖችን አቅም ቀጣይነት ባለው መልኩ ለመገንባት
+5
ተቋሙ የቴክኒሺያኖች አቅም ለማጎልበት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል፤ …….///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሲቪል እና ኤሌክትሮ ሜካኒካል ቴክኒሽያኖችን አቅም ቀጣይነት ባለው መልኩ ለመገንባት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ገለጸ፡፡ ተቋሙ ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከየካ ክፍለ ከተማ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ጋር በመተባበር በኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ በኮንስትራክሽን ማኔጅመንት መምሪያ ውስጥ የሚገኙ የሲቪል እና ኤሌክትሮሜካኒካል ኤሬክሽን ቴክኒሺያኖች አሰልጥኖ አስመርቋል። የተቋሙን ዋና ሥራ አስፈፃሚ በመወከል በምረቃ ሥነ- ሥርዓቱ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የሰው ኃይል ሥራ አስፈፃሚ አቶ አታላይ አበበ እንደተናገሩት ቴክኒሺያኖች በተግባር የተፈተነ ብቃት እንዲኖራቸው ለማድረግና አቅማቸውን ለማሳደግ ተቋሙ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል፡፡ ከሀገር ውስጥ ባለፈ በውጭ ሀገራት ጭምር የተሻለ የግንባታና የኦፕሬሽን ሥራዎችን ማከናወን የሚችልበት ደረጃ ላይ እንዲደረስ ተቋሙ አቅዶ እየሰራ መሆኑንና መሰል ሥልጠናዎችም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ጠቁመዋል፡፡ ‎ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-የቴክኒሺያኖች-አቅም-ለማጎልበት-ት&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም

#COP32 ታማኝነት፡- "በግልጽነትና በሃቀኝነት መስራት!" የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለአረንጓዴ ልማትና ለኮፕ 32 የአየር ንብረት ማስተካከያ (Climate Adaptation) የሚውሉ ማናቸውንም
#COP32 ታማኝነት፡- "በግልጽነትና በሃቀኝነት መስራት!" የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለአረንጓዴ ልማትና ለኮፕ 32 የአየር ንብረት ማስተካከያ (Climate Adaptation) የሚውሉ ማናቸውንም ሀብቶችና ፋይናንሶች በግልጽነትና በሃቀኝነት ለታለመላቸው ዓላማ በማዋል ኃላፊነቱን በታማኝነት ይወጣል። ⚖️💚 #COP32 #ታማኝነት #ግልጽነት #EEP 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም

‎በሪጅኑ የኃይል አቅርቦት አስተማማኝነትን ለማስቀጠል የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው፤ ‎.....///.... ‎በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ደቡብ ሁለት ሪጅን ያለውን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት
‎በሪጅኑ የኃይል አቅርቦት አስተማማኝነትን ለማስቀጠል የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው፤ ‎.....///.... ‎በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ደቡብ ሁለት ሪጅን ያለውን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት አስተማማኝነት ለማስቀጠል የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን የሪጅኑ ዳይሬክተር ገለፁ። ‎ ‎ዳይሬክተሩ አቶ ምትኩ ታዬ እንደገለፁት ሪጅኑ በስምንት ማከፋፈያ ጣቢያዎችና 1 ሺህ 178 ኪሎ ሜትር በሚሸፍኑ የማስተላለፊያ መስመሮች ለኢትዮ-ኬኒያ ኮንቨርተር ጣቢያ ጨምሮ ለደቡባዊ የኢትዮጵያ ክፍል አስተማማኝ ኃይል እያቀረበ ይገኛል። ‎ ‎የአካባቢው የኃይል ፍላጎት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን ከግምት በማስገባት በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የማዘመንና የአቅም ማሳደግ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል። ‎ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በሪጅኑ-የኃይል-አቅርቦት-አስተማማኝነ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም

ተቋሙ ለተለያዩ ተቋማት የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን እየሰጠ ይገኛል ....///.....‎ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተለያዩ ዘርፎች ለመንግሥታዊና መንግሥታዊ ላልሆኑ ተቋማት የአቅም ግንባታ ስልጠ
+9
ተቋሙ ለተለያዩ ተቋማት የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን እየሰጠ ይገኛል ....///.....‎ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተለያዩ ዘርፎች ለመንግሥታዊና መንግሥታዊ ላልሆኑ ተቋማት የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን መስጠት መጀመሩን በተቋሙ የኢትዮ ፓወር አካዳሚ አስታወቀ፡፡ ተቋሙ ላለፉት አምስት ቀናት "በኤሌክትሪካል ፓወር ሲስተም ኦፕሬሽን፣ ጥገናና ፕሮቴክሽን" ጉዳዮች ላይ ለንብ ኢነተርናሽናል ባንክ የኤሌክትሪክ ሲስተም ኦፕሬሽንና ጥገና ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጥቷል፡፡ የኢትዮ ፓወር አካዳሚ ዳይሬክተር ወንድወሰን ካሳ (ዶ/ር) በስልጠናው ማጠናቀቂያ ወቅት እንደተናገሩት የተቋሙ አካዳሚ በአቅም ግንባታ ሥራዎች የረጅም ጊዜ ልምድ አለው በዚህም በኃይል ዘርፉ በርካታ ባለሙያዎችን ከማፍራቱም ባሸገር ለሌሎች ተቋማትም የተለያዪ ስልጠናዎችን ለመስጠት መብቃቱን ገልፀዋል ። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-ለተለያዩ-ተቋማት-የአቅም-ግንባታ-ስ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 26 ቀን 2018 ዓ.ም

የ‎ኮንቨርተር ጣቢያው የተቋሙን ርዕይ ማሳካት በሚያስችል ቁመና ላይ ይገኛል፤‎ ....///.....‎ የኢትዮ ኬኒያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት ኮንቨርተር ማከፋፈያ ጣቢያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአፍ
+9
የ‎ኮንቨርተር ጣቢያው የተቋሙን ርዕይ ማሳካት በሚያስችል ቁመና ላይ ይገኛል፤‎ ....///.....‎ የኢትዮ ኬኒያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት ኮንቨርተር ማከፋፈያ ጣቢያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል ለመሆን የያዘውን ርዕይ ለማሳካት በሚያስችል አስተማማኝ ቁመና ላይ እንደሚገኝ የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለፁ።‌‎ ሥራ አስኪያጁ አቶ ሀብታሙ ግርማ እንደገለፁት ከወላይታ ሶዶ ከተማ በ7 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው ጣቢያው እስከ ኬኒያ የተዘረጋውን 1 ሺ 45 ኪሎ ሜትር የማስተላለፊያ መስመር በመጠቀም 2 ሺህ ሜጋ ዋት ኃይል ለጎረቤት ሀገራት የማስተላለፍ አቅም ይዞ 2014 ዓ.ም ላይ ወደ ኦፕሬሽን ገብቷል።‌‎ ጣቢያው የተገነባበት የቴክኖሎጅ ዓይነት የኤሌክትሪክ ፍሰቱ ሳይወዛወዝ ወደ አንድ አቅጣጫ ብቻ ቀጥ ብሎ የሚጓዝበት ቀጥተኛ የኤሌክትሪክ ዥረት (Direct Current - DC) መሆኑ ተጨማሪ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችንና የማከፋፈያ ጣቢያዎችን ግንባታ በማስቀረት ከፍተኛ ወጪ እንዲድን ማስቻሉን ጠቁመዋል።‎ ‎ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኮንቨርተር-ጣቢያው-የተቋሙን-ርዕይ-ማ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም

‎ማከፋፈያ ጣቢያው ለደቡባዊ ግሪድ ዋነኛ የኃይል ማዕከል በመሆን እያገለገለ ነው፤ ‎....///.... ‎በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የወላይታ ሶዶ ሁለት ባለ 400 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ለአካባ
+9
‎ማከፋፈያ ጣቢያው ለደቡባዊ ግሪድ ዋነኛ የኃይል ማዕከል በመሆን እያገለገለ ነው፤ ‎....///.... ‎በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የወላይታ ሶዶ ሁለት ባለ 400 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ለአካባቢውና ለደቡባዊ ግሪድ ዋነኛ የኃይል ማዕከል በመሆን እያገለገለ እንደሚገኝ የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለጹ። ‎ ‎ሥራ አስኪያጁ አቶ በላይነህ ህንዳሞ እንደገለጹት ጣቢያው ከጊቤ ሦስት የሚመነጨውን 1 ሺህ 870 ሜጋ ዋት ኃይል የሚቀበል ሲሆን ከግልገል ጊቤ ሁለት እንዲሁም በይርጋለም ቁጥር ሁለት በኩል ደግሞ ከገናሌ ዳዋ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ጋር በቀጥታ የተገናኘ ነው። ‎ ‎ከኃይል ማመንጫዎች ከሚቀበለው ኃይል ውስጥ 60 ከመቶ የሚሆነውን በቀጥታ ለገላን ማከፋፈያ ጣቢያ እንደሚሰጥ ገልጸዋል። ‎ ‎በባለ 132 ኪሎ ቮልት ለሀላባ እና ለወላይታ ቁጥር አንድ፣ በባለ 230 ኪሎ ቮልት ለአዲሱ የአርባ ምንጭ ቁጥር ሁለት ማከፋፈያ ጣቢያዎች እንዲሁም በ33/15 ኪሎ ቮልቶች ለዳታ ማይኒንግ ድርጅቶችና ለኢትዮጵያ ኤእሌክትሪክ አገልግሎት የአካባቢው ዲስትሪክት እንደሚያቀርብም ጠቁመዋል። ‎ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ማከፋፈያ-ጣቢያው-ለደቡባዊ-ግሪድ-ዋነኛ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም

የተሰረዘ ማስታወቂያ .......///...... 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEP
የተሰረዘ ማስታወቂያ .......///...... 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም

የተቋሙን ስትራቴጂክ ዕቅድና አፈፃፀም ለማስተዳደር የሚያስችል መተግበሪያ ወደ ሥራ ለማስገባት ታቅዷል …///… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የስትራቴጂክ ዕቅድና አፈፃፀምን ለመከታተልና ለማስተዳደር የ
+4
የተቋሙን ስትራቴጂክ ዕቅድና አፈፃፀም ለማስተዳደር የሚያስችል መተግበሪያ ወደ ሥራ ለማስገባት ታቅዷል …///… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የስትራቴጂክ ዕቅድና አፈፃፀምን ለመከታተልና ለማስተዳደር የሚያስችል “ኢ.ኢ.ፒ ቢ.ኤስ.ሲ” ተሰኘ የድረ-ገፅ መተግበሪያ በሥራ ላይ ለማዋል እየሰራ መሆኑን የዲጅታል ትራንስፎርሜሽን ዘርፍ አስታወቀ፡፡ የዘርፉ ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ጽዮን በቀለ እንደተናገሩት መተግበሪያው የተቋሙን የዕቅድ አፈጻጸም ምዘናዎች በቴክኖሎጂ እንዲታገዙ በማድረግ የቆየውን ወረቀት ተኮር አሠራር ሙሉ በሙሉ የሚያስቀር ነው። መተግበሪያው የተቋሙን ስትራቴጂካዊ ግቦች፣ የሥራ ክፍሎችንና የሠራተኞችን የሥራ አፈፃፀም ደረጃ በዲጂታል ሥርዓት ለመከታተልና ለመገምገም ከፍተኛ እገዛ ያደርጋልም ብለዋል። የአሠራር ሥርዓቱ ከዚህ በፊት የነበሩትን የወረቀትና የተበታተኑ የሪፖርት ማቅረቢያ መንገዶችን በማስቀረት ሥራዎችን በጥራት፣ በፍጥነትና ያለሰው ንክኪ ለመከታተል እንደሚያስችልም ነው ያብራሩት፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የተቋሙን-ስትራቴጂክ-ዕቅድና-አፈፃፀም-ለ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 24 ቀን 2018 ዓ.ም

የኃይል መሠረተ ልማቶች እንዲጠበቁ የአካባቢው ማህበረሰብ ሚናውን መወጣት አለበት፤ .....///..... በአካባቢው የሚገኙ የኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማቶችን በመጠበቅ በኩል ማህበረሰቡ ሚናውን ሊወ
+5
የኃይል መሠረተ ልማቶች እንዲጠበቁ የአካባቢው ማህበረሰብ ሚናውን መወጣት አለበት፤ .....///..... በአካባቢው የሚገኙ የኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማቶችን በመጠበቅ በኩል ማህበረሰቡ ሚናውን ሊወጣ እንደሚገባ የወላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ ገለፁ። ከንቲባዋ ወይዘሮ እታገኝ ኃይለማሪያም እንደገለፁት በወላይታ ሶዶ ከተማና ዙሪያዋ የኢትዮ ኬኒያ ኮንቨርተር ጣቢያን ጨምሮ ሌሎች ሁለት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችና የማስተላለፊያ መስመሮች ይገኛሉ። ሁለቱ ማከፋፈያ ጣቢያዎች የከተማዋንና የአካባቢውን የኃይል ፍላጎት በአስተማማኝ መልኩ በማሟላት በኩል ሚናቸው የጎላ መሆኑን ጠቁመዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-መሠረተ-ልማቶች-እንዲጠበቁ-የአካ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 22 ቀን 2018 ዓ.ም

ማብቃት፡- የሰው ኃይል አቅምን መገንባትና ማበረታታት ….///…. በታዳሽ ኃይልና በአረንጓዴ ቴክኖሎጂ ዘርፍ የተሰማሩ ምሁራኖቻችንን እና ሠራተኞቻችንን አቅም ማሳደግ፣ ለኮፕ 32 ስኬት እና ለአየር
ማብቃት፡- የሰው ኃይል አቅምን መገንባትና ማበረታታት ….///…. በታዳሽ ኃይልና በአረንጓዴ ቴክኖሎጂ ዘርፍ የተሰማሩ ምሁራኖቻችንን እና ሠራተኞቻችንን አቅም ማሳደግ፣ ለኮፕ 32 ስኬት እና ለአየር ንብረት መቋቋም ሽግግር መሠረት ነው። አቅምን በማልማት የአየር ንብረት ፈተናዎችን እናሸንፋለን። #COP32 #ማብቃት #የሰውኃይልአቅም #EEP 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም

አስተማማኝነት፡- "በማንኛውም ጊዜ የሚታመን አገልግሎት መስጠት!" ….///…. ተለዋዋጭ የሆነውን የአየር ንብረት ሁኔታ መቋቋም የሚችል እና በማንኛውም ወቅቶች የማይቆራረጥ የንጹሕ ኃይል አቅርቦት ለ
አስተማማኝነት፡- "በማንኛውም ጊዜ የሚታመን አገልግሎት መስጠት!" ….///…. ተለዋዋጭ የሆነውን የአየር ንብረት ሁኔታ መቋቋም የሚችል እና በማንኛውም ወቅቶች የማይቆራረጥ የንጹሕ ኃይል አቅርቦት ለሕዝባችን ማድረስ፣ ተቋማችን በኮፕ 32 ጉባዔ ላይ የሚያስተጋባውና በተግባር እያረጋገጠው የሚገኘው ትልቁ ስኬቱ ነው። #COP32 #አስተማማኝነት #የሚታመንአገልግሎት #EEP 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 20 ቀን 2018 ዓ.ም

የተቋማችን አንዱ ትልቅ እሴት ዘላቂነት ነው ….///…. "ለአሁኑም ሆነ ለወደፊቱ ትውልድ የሚተርፍ ሥራ መሥራት!" የኮፕ 32 (COP32) ጉባዔ ዋና ዓላማም መጪውን ትውልድ ከአየር ንብረት አደጋ መ
የተቋማችን አንዱ ትልቅ እሴት ዘላቂነት ነው ….///…. "ለአሁኑም ሆነ ለወደፊቱ ትውልድ የሚተርፍ ሥራ መሥራት!" የኮፕ 32 (COP32) ጉባዔ ዋና ዓላማም መጪውን ትውልድ ከአየር ንብረት አደጋ መታደግ በመሆኑ፣ ይህ ተቋማዊ እሴታችን ከጉባዔው ዓለም አቀፋዊ ግብ ጋር አብሮ ይጓዛል። #COP32 #ዘላቂነት #ለቀጣይትውልድ #EEP 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 19 ቀን 20

በሪጅኑ በተለያዩ ምክንያቶች ወድቀው የነበሩ 20 የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ተጠግነው ወደ ሥራ ገብተዋል ….///…. በተለያዩ ጊዚያት ወድቀው የነበሩ 20 የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎችን መ
+6
በሪጅኑ በተለያዩ ምክንያቶች ወድቀው የነበሩ 20 የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ተጠግነው ወደ ሥራ ገብተዋል ….///…. በተለያዩ ጊዚያት ወድቀው የነበሩ 20 የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎችን መልሶ በመጠገን ወደ ሥራ ማስገባቱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምዕራብ ሪጅን አስታወቀ። የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ኃይሉ በቀለ እንዳስታወቁት በሪጅኑ በሚገኙ ከፍተኛ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ በደረሰው ጉዳት የተቋረጠውን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ችግር ለመፍታት የእንጨት ምሰሶዎችን በመትከል ኃይል ሲቀርብ ቆይቷል፡፡  አሁን ላይ በተለያዩ የማስተላለፊያ መስመሮች ላይ ወድቀው የነበሩ የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎችን በመጠገን ወደ ነበሩበት መመለስ መቻሉን ገልጸዋል፡፡ በመንዲ-ጊዳሚ 132 ኪሎ ቮልት ማስላለፊያ መስመር ላይ አምስት ታዎሮች፣ በመንዲ-አሶሳ 132 ኪሎ ቮልት ማስተላለፊያ መስመር ላይ 13 ታዎሮች እና በነቀምት - ጊዳ አያና 132 ኪሎ ቮልት ማስተላለፊያ መስመር ላይ  ሁለት ታወሮች በድምሩ በ20 ታዎሮች ላይ የጥገና ሥራ የተከናወነ መሆኑን ዳይሬክተሩ አስረድተዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በሪጅኑ-በተለያዩ-ምክንያቶች-ወድቀው-የነ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 18 ቀን 20

መደመር ማለት "በጋራ እና በቅንጅት የላቀ ውጤት ማምጣት!" ማለት ነው። ......///....... የአየር ንብረት ለውጥን ማሸነፍ የሚቻለው በተናጠል ሳይሆን በጋራ በመቆም በመሆኑ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክ
መደመር ማለት "በጋራ እና በቅንጅት የላቀ ውጤት ማምጣት!" ማለት ነው። ......///....... የአየር ንብረት ለውጥን ማሸነፍ የሚቻለው በተናጠል ሳይሆን በጋራ በመቆም በመሆኑ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመደመርን እሴት ሰንቆ በኮፕ 32 ጉባዔ ላይ ከዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ተሟጋቾች ጋር በቅንጅት ይሠራል። 🌍 #COP32 #መደመር #የጋራውጤት #EEP 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም

ደንበኛ ተኮርነት እና አስተማማኝ አገልግሎት ......///....... "የደንበኞቻችንን ፍላጎት ቅድሚያ መስጠት!" አስተማማኝ፣ ጥራት ያለውና ለአካባቢ ጥበቃ ተስማሚ የሆነ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦ
ደንበኛ ተኮርነት እና አስተማማኝ አገልግሎት ......///....... "የደንበኞቻችንን ፍላጎት ቅድሚያ መስጠት!" አስተማማኝ፣ ጥራት ያለውና ለአካባቢ ጥበቃ ተስማሚ የሆነ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትን ለደንበኞቻችን ማድረስ ዋነኛ መርሀችን ነው። ይህንን ለአካባቢ ጥበቃ የምናደርገውን ጥረት በኮፕ 32 (COP 32) ጉባኤ መድረክ ላይ በማቅረብ ንፁህ ኃይልን በተደራሽነት የማቅረብ ታማኝነታችንን ዳግም እናረጋግጣለን። #COP32 #ደንበኛተኮርነት #አስተማማኝአገልግሎት #EcoFriendly #EEP 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 17 ቀን 2018 ዓ.ም

ተቋሙ በራስ አቅም የሚያከነውናቸውን የፕሮጀክት ግንባታዎች አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገለፀ …///… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በራስ አቅም የሚያከናውናቸውን የኃይል ማከፋፈያና ማስተላለፊያ መስመር ግን
+4
ተቋሙ በራስ አቅም የሚያከነውናቸውን የፕሮጀክት ግንባታዎች አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገለፀ …///… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በራስ አቅም የሚያከናውናቸውን የኃይል ማከፋፈያና ማስተላለፊያ መስመር ግንባታዎች አጠናክሮ እንደሚቀጥል በተቋሙ የኢንጅነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ አስታወቀ፡፡ የዘርፉ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ውድነህ የማነ እንደተናገሩት ፕሮጀክቶችን ከዲዛይን እስከ ግንባታ ያለውን ሙሉ ሂደት በራስ አቅም በማከናወን ረገድ እየተመዘገበ ያለው ውጤት አበረታች ነው፡፡ ተቋሙ ወደፊት በራስ አቅም የሚከናወኑ ሥራዎችን ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ የውስጥ አሰራርን ከማሻሻልና የውጭ ተፅዕኖዎችን ከመቆጣጠር አንፃር የተለያዩ የሪፎርም አቅጣጫዎችን ለይቶ እየሰራ እንደሚገኝም አስረድተዋል። የውስጥ አሰራርን ለማሻሻል በግንባታ እና በድጋፍ ሰጪ የሥራ ክፍሎች መካከል ያለውን ቅንጅት፣ ቅልጥፍና እና የጋራ ግንዛቤ በማሳደግ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን በዘላቂነት መፍታት እንደሚገባ ኢንጂነር ውድነህ አብራርተዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-በራስ-አቅም-የሚያከነውናቸውን-የፕ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 17 ቀን 2018 ዓ.ም