ch
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

前往频道在 Telegram

EEP Communication

显示更多

📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览

频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 553 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 406,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 161

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 553 名订阅者。

根据 19 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -3,过去 24 小时变化为 -5,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 26.69%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.00% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 150 次浏览,首日通常累积 2 332 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 10

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
EEP Communication

凭借高频更新(最新数据采集于 20 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。

15 553
订阅者
-524 小时
+97
-330
帖子存档
photo content
+3

ለሥራ አመልካቾች በሙሉ፤ መጋቢት 30 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ለወጣውን የሥራ ማስታወቂያ አመልካቾች እንዲመዘገቡበት የተገለፀው የመመዝገቢያ ሊንክ በጊዜያዊ የቴክኒክ ችግር ምክን
ለሥራ አመልካቾች በሙሉ፤ መጋቢት 30 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ለወጣውን የሥራ ማስታወቂያ አመልካቾች እንዲመዘገቡበት የተገለፀው የመመዝገቢያ ሊንክ በጊዜያዊ የቴክኒክ ችግር ምክንያት አመልካቾችን ማስተናገድ አልቻለም። በአሁኑ ወቅትም ተቋማችን ችግሩን ለመፍታት ጥረት እያደረገ ሲሆን የመመዝገቢያ ሊንኩ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር ወዲያውኑ በይፋዊ የፌስቡክ ገጻችን እና በቴሌግራም ቻናላችን የምናሳውቅ መሆኑን እንገልፃለን። አመልካቾች ለተፈጠረው መስተጓጎል ከልብ ይቅርታ እየጠየቅን፣ ችግሩ ተፈትቶ ምዝገባው እስከሚጀምር ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለን። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 9 ቀን 2018 ዓ.ም

ባለፉት የለውጥ ዓመታት በኃይል አቅርቦት የተመዘገቡት ውጤቶች ሀገሪቱ በለውጥ ጎዳና ላይ መሆኗን የሚያሳዩ ናቸው …..///…. ባለፉት የለውጥ ዓመታት በኃይል አቅርቦት እንዲሁም በመንገድ፣ በመስኖ እና በከተማ ማስዋብ ዘርፎች የተመዘገቡት ውጤቶች ሀገሪቱ በትክክለኛ የለውጥ ጎዳና ላይ መሆኗን የሚያሳዩ መሆናቸውን የኢፌዲሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ “ኢትዮጵያ ትገነባለች!” በሚል መሪ ቃል በኢፌዴሪ ከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር አማካኝነት ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘጋጀው ሀገራዊ የመሠረተ ልማትና የኮንስትራክሽን ሣምንት በኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ በይፋ ተከፍቷል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመክፈቻ ንግግራቸው እንደገለጹት ኢትዮጵያ አሁን ያለችበት ወቅት የሥራና የውጤት ዘመን መሆኑንና ሣምንቱ ለቀጣይ የግንባታ ሥራዎች ግብዓት የሚገኝበትና ትልቅ ዕድል የሚፈጥር ነው። ባለፉት የለውጥ ዓመታት በግንባታ ሥራዎች ላይ የተመዘገቡት ውጤቶች ከሥራ ዕድል ፈጠራ ባለፈ የሙያ ባለቤቶችን በማፍራት ረገድም የጎላ ፋይዳ እንዳላቸው አብራርተዋል። እንደ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለጻ የመሠረተ ልማትና ኮንስትራክሽን ሳምንት የመደመር መንግሥትን የልማት እይታና ሀገራዊ ራዕይ ያስተሳሰረ ነው። የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ በበኩላቸው ሣምንቱ የታላቁ የህዳሴ ግድብን ጨምሮ ሌሎች ሀገራዊ ሜጋ ፕሮጀክቶችን የግንባታ ሂደት ትኩረት አድርጎ የሚከበር መሆኑን ተናግረዋል። ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ ታላላቅ የፕሮጀክት ግንባታ ሥራዎች ላይ የታዩ ጠንካራ ጎኖችና ክፍተቶችን በመዳሰስ ለቀጣይ ሥራዎች ልምድ የሚወሰድበት መሆኑንም ሚኒስትሯ ጠቁመዋል። ሣምንቱ የሀገር ውስጥ የዘርፉ ተዋናዮች አዳዲስ ፈጠራዎችና ልምዶችን እንዲቀስሙ፣ የቴክኖሎጂ እድገቶችን እና የአሰራር ሥርዓቶችን እንዲገበዩ የሚያግዝ መሆኑን የተናገሩት ወይዘሮ ጫልቱ በዘርፉ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ተቋማትና ግለሰቦች ዕውቅናና ሽልማት እንደሚሰጥም ገልጸዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን ጨምሮ በኢነርጂ፣ በውሃ፣ በኢኖቬሽን፣ በኮንስትራክሽን፣ በሎጂስቲክስ፣ በዲጂታል መሠረተ ልማት እና ፖሊሲ ላይ ትኩረት አድርገው የሚሰሩ ተቋማት በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ፡፡ የኢትዮጵያ መሠረተ ልማትና ኮንስትራክሽን ሣምንት ከዛሬ ጀምሮ እስከ ሚያዚያ 12 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ ይሆናል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 9 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+2

🌍 COP32 በኢትዮጵያ፡ የአየር ንብረት የዲፕሎማሲያችን አዲስ ምዕራፍ! 🇪🇹 COP (Conference of the Parties) ማለት በዓለም አቀፍ ደረጃ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል የሚ
🌍 COP32 በኢትዮጵያ፡ የአየር ንብረት የዲፕሎማሲያችን አዲስ ምዕራፍ! 🇪🇹 COP (Conference of the Parties) ማለት በዓለም አቀፍ ደረጃ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል የሚካሄድ ትልቁ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጉባኤ ነው። ኢትዮጵያ በ2027 (እ.ኤ.አ) ይህንን ጉባኤ ለማስተናገድ መመረጧ ምን ጥቅሞች አሉት? 1. በአረንጓዴ አሻራ እና በተፈጥሮ ጥበቃ የተጀመሩ ስራዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያገኛሉ፤ 2. በአሥር ሺዎች የሚቆጠሩ ልዑካን ወደ አገራችን ስለሚመጡ ለሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ ትልቅ ገቢ ያስገኛል፣ 3. ኢትዮጵያ በአፍሪካና በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ድርድር ያላትን ተሰሚነት ያሳድጋል፣ 4. የኃይል ሽያጭና የኢንቨስትመንት አጋርነት ለመፍጠር ይረዳል፣ 5. ተቋማችን የሚያመነጨው ንጹህና ታዳሽ ኃይል (ውኃና ንፋስ) ለዓለም ገበያ ይተዋወቃል። በጥቅሉ ኢትዮጵያ በታዳሽ ኃይልና በአረንጓዴ ልማት ያላትን እምው አቅም ለዓለም የምታሳይበት ታሪካዊ መድረክ ነው! 💚🌿 #COP32 #Ethiopia #GreenLegacy #RenewableEnergy 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 9 ቀን 2018 ዓ.ም

ተቋሙ በሀገር አቀፍ የመሠረተ ልማትና ኮንስትራክሽን አውደርዕይ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል ….///…. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በአዲስ ዓለም አቀፍ የኮንቬንሽን ማዕከል ዛሬ ሚያዝያ 9 ቀን 2018
+3
ተቋሙ በሀገር አቀፍ የመሠረተ ልማትና ኮንስትራክሽን አውደርዕይ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል ….///…. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በአዲስ ዓለም አቀፍ የኮንቬንሽን ማዕከል ዛሬ ሚያዝያ 9 ቀን 2018 ዓ.ም በተከፈተው ሀገር አቀፍ የኢትዮጵያ መሠረተ ልማትና ኮንስትራክሽን ሣምንት ላይ እየተሳተፈ ይገኛል። በኮንስትራክሽንና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር በተዘጋጀው በዚህ ዝግጅት ላይ በሀገራዊ የመሠረተ ልማት አመራር፣ ቅንጅት እና አፈጻጸም ዙሪያ እንዲሁም በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ሂደት የታዩ ስኬቶች እና የተገኙ ተሞክሮዎች ቀርበው ውይይት የሚደረግባቸው ይሆናል፡፡ ከዛሬ ሚያዚያ 9-12 ቀን 2018 ዓ.ም በሚቆየው የኢትዮጵያ መሠረተ ልማትና ኮንስትራክሽን ሣምንት ላይ በኢነርጂ፣ በውሃ፣ በኢኖቬሽን፣ በኮንስትራክሽን፣ በሎጂስቲክስ፣ በዲጂታል መሠረተ ልማት እና ፖሊሲ ላይ ትኩረት አድርገው የሚሰሩ ተቋማት በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ፡፡ ተጨማሪ መረጃዎችን ይዘን እንመለሳለን። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 9 ቀን 2018 ዓ.ም

መንግሥት የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል የሚያስችሉ ሥራዎችን እያከናወነ ነው ......///....... መንግሥት የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል በኢነርጂ ዘርፍ ላይ በርካታ ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ተናገሩ፡፡ ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ በአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የምረቃ ሥነ-ስርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር የመንግስት ዋነኛ ትኩረት የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ማሻሻልና ጫናዎችን ማቃለል ነው፡፡ የአሰላ የንፋስ ኃይል ፕሮጀክት የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል እየተከናወኑ ካሉ ሥራዎች መካከል አንዱ መሆኑንም ተናግረዋል። መንግስት የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በኃይል ማመንጨት ዘርፍ በርካታ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ አቶ ሽመልስ  አብራርተዋል። አሰላ ቀደም ሲል በግብርና ምርታማነቷ በስፋት የምትታወቅ ቢሆንም አሁን ላይ ደግሞ በኃይል ማመንጨት በኩል ጉልህ አስተዋጽዖ እያበረከተች መሆኑን ገልፀዋል። የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በአካባቢው ያለውን ምርታማነት በማሳደግ ለአርሶ አደሩ ከፍተኛ እገዛ ከማድረጉም ባሻገር አርሶ አደሩ ካለበት ባህላዊ አሰራር ወጥቶ ወደ ላቀ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ እንዲሸጋገር ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር ጠቁመዋል፡፡ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቱ በአርሲና በአካባቢው ለረጅም ጊዜ የነበረውን የኃይል አቅርቦት ችግር በዘላቂነት እንደሚፈታው ያላቸዉን ተስፋ ገልፀው የማመንጫ ጣቢያው ሥራ መጀመር ድህነትንና ወደኋላ ቀርነትን ለመቅረፍ በሚደረገው ጥረት ውስጥ የራሱ የሆነ ሚና እንደሚኖረውም ተናግረዋል። ፕሮጀክቱ የአካቢውን የኢኮኖሚ እድገት ከማፋጠኑም በላይ የማህበረሰቡ የኑሮ ሁኔታ ወደተሻለ ደረጃ ያሸጋግራል ብለዋል። የዞኑ ህዝብ ያገኘውን መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ድህነት እና ኋላ ቀርነትን ለማስወገድ መረባረብ እንዳለበት አቶ ሽመልስ አሳስበዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 8 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+4

ዴንማርክ ለኢትዮጵያ የኢነርጂ ዘርፍ የምታደርውን ድጋፍ አጠናክራ ትቀጥላለች .......///......... ዴንማርክ የኢትዮጵያን የታዳሽ ኃይል ልማት ዘርፍ እንደምትደግፍ በኢትዮጵያ የዴንማርክ አምባሳደር ሱን ክሮግስትራፕ ገለጹ። አምባሳደሩ እንደገለፁት የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በዴንማርክና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን ጠንካራና የላቀ አጋርነት ማሳያ ነው። የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ቀጣይነት ላለው የኢትዮጵያ ዕድገት ወሳኝ ምዕራፍ  መሆኑን አምባሳደሩ ተናግረዋል:: ፕሮጀክቱ ኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂን ተግባራዊ በማድረግ ንፁህና አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ያስችላል ብለዋል:: ዴንማርክ በንፋስ ኃይል ማመንጨትና በዘላቂ የኃይል አጠቃቀም ረገድ ያላትን ሰፊና የበለጸገ ልምድ በመጠቀም የኢትዮጵያን የኃይል ስርዓት ለማዘመን አስተዋጽኦ በማበርከቷ ኩራት እንደሚሰማቸው አምባሳደሩ ተናግረዋል። ይህ የሁለቱ ሀገራት ትብብር የኢትዮጵያን የታዳሽ ኃይል የማመንጨት አቅም ከማሳደጉም በላይ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ወዳጅነት ይበልጥ የሚያጠናክር መሆኑን አብራርተዋል። ፕሮጀክቱ በቴክኖሎጂ ሽግግርና በንጹህ ኢነርጂ አቅርቦት ረገድ ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ትልቅ ፋይዳ እንዳለውም አምባሳደሩ አስረድተዋል። ዴንማርክ ወደፊትም የኢትዮጵያን የኢነርጂ ዘርፍ ለማልማትና ለማሸጋገር በሚደረገው ጥረት ውስጥ በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆኗን አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያን የአረንጎዴ አሻራ ለማስቀጠል እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እንዲሁም የኢትዮጵያ መንግስት የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል የሚያከናውነውን የኢነርጂ ልማት ዴንማርክ እንደምትደግፍ አምባሳደሩ አረጋግጠዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 8 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+3

የምናስመርቃቸው ፕሮጀክቶች የተቋሙን አፈጻጸም የሚያሳዩ የድል ማህተሞች ናቸው - አንጂነር አሸብር ባልቻ .......///....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እያስመረቃቸው ያሉ የኃይል ማመንጫ ፕ
+9
የምናስመርቃቸው ፕሮጀክቶች የተቋሙን አፈጻጸም የሚያሳዩ የድል ማህተሞች ናቸው - አንጂነር አሸብር ባልቻ .......///....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እያስመረቃቸው ያሉ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን የብልፅግና ጉዞን የሚያፋጥኑ እና የተቋሙን የላቀ አፈጻጸም የሚያሳዩ የድል ማህተሞች መሆናቸው የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ገለፁ። ዋና ሥራ አስፈፃሚው ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ምርቃት ላይ እንደተናገሩት በኢትዮጵያ ከተለያዩ የኃይል አማራጮች ከ160 ጊጋ ዋት በላይ ኃይል ለማመንጨት የሚያስችል እምቅ አቅም አለ። ተቋሙ ይህን እምቅ አቅም በመጠቀም እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት በአስተማማኝ መልኩ ለመመለስ ትውልድን ታሳቢ ያደረጉ ዘመን ተሻጋሪ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች እየገነባ ይገኛል ብለዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የምናስመርቃቸው-ፕሮጀክቶች-የተቋሙን-አ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 8 ቀን 2018 ዓ.ም

በተቋሙ ላይ የተከናነው የለውጥ ሥራ ውጤት ተገኝቶበታል .......///........ መንግሥት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያከናወነው የለውጥ ሥራ ውጤት እንደተገኘበት የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢ
+9
በተቋሙ ላይ የተከናነው የለውጥ ሥራ ውጤት ተገኝቶበታል .......///........ መንግሥት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል  ያከናወነው የለውጥ ሥራ ውጤት እንደተገኘበት የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታወቁ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ምረቃ ላይ እንደተናገሩት አርሲ በስንዴና ገብስ ምርት ብቻ ሳይሆን በኢነርጅ ዘርፍም ከፍተኛ አቅም አለው። በአካባቢው ከአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ በተጨማሪ ሁለት የከርሰ ምድር እንፋሎት የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች በግንባታ ሂደት ላይ ይገኛሉ ብለዋል። ከለውጡ በፊት በኢትዮጵያ 4 ሺህ ሜጋ ዋት አካባቢ የነበረው ኃይል የማመንጨት አቅም አሁን ላይ ወደ 10 ሺህ ሜጋ ዋት መጠጋቱን እንዲሁም 7 ቢሊዮን ብር የነበረው የተቋሙ ዓመታዊ ገቢ ከ75 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠቅሰዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በተቋሙ-ላይ-የተከናነው-የለውጥ-ሥራ-ውጤት&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 8 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+9

የፈተና ማስታወቂያ .......///....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሞግዚት /Child varegivers/ የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም የውጭ ማ
+1
የፈተና ማስታወቂያ .......///....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሞግዚት /Child varegivers/ የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም የውጭ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ በዚሁ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች ሚያዚያ 13 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ ብረታ ብረት ፊት ለፊት በሚገኘው ዋናው መ/ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ የጽሁፍ ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ  ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 7 ቀን 2018 ዓ.ም

ተቋሙ የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎችን የኃይል ፍላጎት ታሳቢ ያደረጉ ሥራዎችን እያከናወነ ነው ….///…. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎችን የኃይል ፍላጎት ታሳቢ ያደረጉ የተለያዩ ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን በተቋሙ የኮርፖሬት ፕላኒንግ ተወካይ ሥራ አስፈጻሚ ገለፁ፡፡ ከጋና የመጡ ባለሙያዎች ተቋሙ በኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች የኃይል አቅርቦት ዙሪያ እያከናወናቸው ባሉ ሥራዎች ዙሪያ በተዘጋጀው የልምድ ልውውጥ መድረክ ላይ ተወካይ ሥራ አስፈጻሚው ኢንጂነር ያለውአይቀር ማንደፍሮ እንደገለጹት እንደ ሀገር እ.ኤ.አ እስከ 2029 የሚቆይ የብሔራዊ የኤሌክትሪክ መኪኖች ትግበራ ስትራቴጅ ተቀርጾ ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡ ለኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሀገራዊ የቴክኒክ ኮሚቴ አባል ሆኖ እየሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ ተቋሙ የአፍሪክ የታዳሽ ኃይል ማዕከል የመሆን ርዕይ ሰንቆ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል ያሉት አቶ ያለውአይቀር ኢትዮጵያ አሁን ላይ 100 ሺህ የሚደርሱ የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎችን ወደ ሥራ በማስገባት ከአፍሪክ ቀዳሚ መሆኗንም ጠቁመዋል፡፡ ተቋሙ በስትራቴጅክ ዕቅዱ ላይ በተቀመጠው መሠረት በሚቀጥሉት 5 ዓመታት ሊኖሩ የሚችሉ የኤሌክትሪክ መኪኖችን ታሳቢ በማድረግ በግሪድና በኦፕሬሽን ሥራዎች ላይ ሊፈጥር የሚችለውን ተጽዕኖ በተመለከተ የባለሙያዎች ቡድን አዋቅሮ ጥናት ማከናወኑን ተናግረዋል፡፡ የኢነርጅ ሴኪዩሪቲ ከኃይል አቅርቦት በተሻገረ የሀገር ደህንነት መሆኑን ያነሱት ተወካይ ሥራ አስፈጻሚው የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪ ፈጣን ቻርጀሮች በግሪዱ እና በኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ ተፅዕኖ እንዳያሳድሩ በጥናት ላይ የተመሰረቱ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በትኩረት እየተከናወኑ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ በትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር የአየር ንብረት ለውጥ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ይዘንጋው ይታይህ የትራንስፖርት ዘርፉ ከአየር ብክለት የጸዳ እና የዘመነ እንዲሆን እንደ ሀገር የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎችን በስፋት ወደ ሥራ እንዲገቡ እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል፡፡ በ2030 ላይ 500 ሺህ የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎችን እና 2 ሺህ 230 የቻርጅ ማዕከላት እንዲኖሩ በስትራቴጅው በዕቅድ ተይዞ እየተሰራበት መሆኑንም አብራርተዋል፡፡ ይህም በዓመት ለነዳጅ የሚወጣውን ከ5 እስከ 6 ቢሊዮን ዶላር ወጪ እና ወደ ከባቢ አየር የሚለቀቀውን የበካይ ጋዝ ልቀት በ13 ነጥብ 9 ሚሊዮን ቶን ካርቦን ዳይኦክሳይድ ለመቀነስ የሚረዳ ነው ብለዋል፡፡ የጋና ልዑካን ቡድን አባልና በጋና ፐብሊክ ዩቲሊቲ ሪጉላቶሪ ኮሚሽን ሪጅናል ኦፕሬሽን ዳይሬክተር ሚስተር አልሃጂ አቡካሪ በበኩላቸው ኢትዮጵያ በአፍሪክ በኤሌክትሪክ ተሸከርካሪ አተገባበር ላይ የተሻለች በመሆኗ እስከ አሁን ከመጣችበትና እየተገበረቻቸው ካሉ አሰራሮች ልምድ ለመውሰድ እና በዘርፉ ውጤታማ ሥራ ለማከናወን ወደ ኢትዮጵያ መምጣታቸውን አብራርተዋል፡፡ በኤሌክትሪክ መኪኖች ላይ ባለድርሻ የሆኑ የትራንስፖርትና የኃይል ዘርፎችን እንዲሁም ተቆጣጣሪ መ/ቤቶች ላይ የልምድ ልውውጥ ማድረጋቸውንና በቆይታቸው ተጨባጭ እውቀቶችንና ልምዶችን መቅሰማቸውን ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያ ለኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች ትግበራ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጀምሮ ከፍተኛ የመንግስት አካላት ትኩረት ሰጥተው በመስራታቸው ከፍተኛ ውጤት ሊመዘገብ መቻሉን እንደታዘቡም ጠቁመዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዝያ 6 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+7

ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ ......///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (EEP) በተለያዩ የሥራ መደቦች ላይ አመልካቾችን አወዳድሮ በቋሚነት መቅጠር ይፈልጋል። በመሆኑም መስፈርቶቹን የም
ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ ......///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (EEP) በተለያዩ የሥራ መደቦች ላይ አመልካቾችን አወዳድሮ በቋሚነት መቅጠር ይፈልጋል። በመሆኑም መስፈርቶቹን የምታሟሉ አመልካቾች በ https://vacancy.eep.com.et/VacancyList በመግባት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን። የምዝገባ ጊዜ፡ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ብቻ ይሆናል፡፡ ዝርዝሩን በተያያዘው ምስል ይመልከቱ! 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 5 ቀን 2018 ዓ.ም

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች፣ የተቋማችን የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች፤ ......///...... በመጀመሪያ እንኳን ለጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳዔ በዓል በሠላም አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ። ትንሳዔ ሞትን ድል የማድረግ፣ ከውድቀት የመነሳትና ጨለማን በብርሃን የመርታት ተምሳሌት እንደሆነው ሁሉ፣ ተቋማችንም በመንግስት ልዩ ትኩረትና እገዛ የታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ከነበረበት መጓተትና ተግዳሮት አውጥቶ ለስኬት ማብቃቱ የድል ጉዞ ማሳያ ነው።  ይህ ታላቅ ፕሮጀክት ለፍሬ መብቃቱ ልክ እንደ ትንሳዔው ሁሉ ተስፋ የመቁረጥን ጨለማ ገፎ በታላቅ ብርሃንና በድል መነሳታችንን ያበሰረበት ታላቅ አገራዊ ስኬት ነው። በተጨማሪም ትንሳዔ የአዲስና የተስፋ ምልክት እንደሆነው ሁሉ፣ ተቋማችንም በሌሎች የልማት ዘርፎች ወደ ላቀ አፈፃፀም በመሸጋገር አዲስ የታሪክ ምዕራፍ የከፈተበት ዓመት ላይ ነው። በተለይ በበጀት ዓመቱ መባቻ ላይ የታላቁ ሕዳሴ ግድብን፣ በግማሽ ዓመቱ ደግሞ የአይሻ ንፋስ ኃይል ማመንጫን ማስመረቅ መቻላችን እንዲሁም በቅርቡ የምናስመርቀው የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን ጨምሮ ተቋማችን ለመጀመሪያ ጊዜ ከኪሳራ ወጥቶ ወደ ትርፋማነት መሸጋገሩ ትልቁ ድላችንና የሪፎርማችን ውጤት መሆኑን በኩራት እገልፃለሁ። እነዚህ ስኬቶች ተቋማችን ለያዘው የልማት ግብና የታዳሽ ኃይል ስብጥርን ለማሳደግ ያለውን ጽኑ ቁርጠኝነት የሚያረጋግጡ ናቸው። ውጤቶቹ የሀገራችንን የኢኮኖሚ ዕድገት ለማፋጠን በሚደረገው ርብርብ ላይ ትልቅ አቅም የሚፈጥሩና የተቋማችንን ብሩህ ተስፋ የሚያመለክቱ በመሆናቸው ትርጉማቸው የላቀ ነው። በመሆኑም እያንዳንዱ የሥራ ኃላፊና ሠራተኛ እነዚህን አገራዊና ተቋማዊ ድሎችን መነሻ በማድረግ፣ የተሰጠንን አደራ በኃላፊነትና በታማኝነት የአገልጋይነት መንፈስ ለሀገራችን ሁለንተናዊ ለውጥና ለተቋማችን ዘላቂ ውጤታማነት የድርሻችንን እንድንወጣጥሪዬን አቀርባለሁ። በድጋሚ በዓሉ የሠላም፣ የደስታ እና የአብሮነት ይሁንላችሁ። መልካም የትንሳኤ በዓል! ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 4 ቀን 2018 ዓ.ም

.
.

photo content