uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 692 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 024-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 156-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 692 obunachiga ega bo‘ldi.

28 Avgust, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 137 ga, so‘nggi 24 soatda esa -5 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 35.24% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 17.40% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 5 528 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 730 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 12 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
EEP Communication

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 29 Avgust, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 692
Obunachilar
-524 soatlar
-17 kunlar
+13730 kunlar
Postlar arxiv
ባንኩ ለአይሻ አንድ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የ110 ሚሊዮን ዶላር ብድር አፀደቀ …///… የአፍሪካ ልማት ባንክ ግሩፕ በኢትዮጵያ በመንግሥትና የግል አጋርነት ማዕቀፍ (PPP) ለሚገነባው የመ
+1
ባንኩ ለአይሻ አንድ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የ110 ሚሊዮን ዶላር ብድር አፀደቀ …///… የአፍሪካ ልማት ባንክ ግሩፕ በኢትዮጵያ በመንግሥትና የግል አጋርነት ማዕቀፍ (PPP) ለሚገነባው የመጀመሪያው የአይሻ አንድ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የ110 ሚሊዮን ዶላር ብድር ማፅደቁን አስታወቀ። የባንኩ የኢነርጂ ፋይናንስ ሶሊዩሽን ፖሊሲና ሬጉሌሽን ክፍል ዳይሬክተር ዋሌ ሾኒባሬ እንዳስታወቁት ለፕሮጀክቱ ግንባታ የሚውለው ብድር መፅደቁ ለኢትዮጵያ የኃይል ዘርፍ ታሪካዊና አዲስ ምዕራፍ ነው። ፕሮጀክቱ መቀመጫነቱ በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ በሆነውና በታዳሽ ኃይል ልማት ላይ በተሰማራው አሜአ ፓወር (AMEA Power) ኩባንያ አማካኝነት የሚገነባና ለ25 ዓመታት በባለቤትነት የሚመራ እንደሆነ ነው ባንኩ የጠቀሰው፡፡ ለፕሮጀክቱ ግንባታ የሚውለው የፋይናንስ ብድር 80 ሚሊዮን ዶላር ከባንኩ፣ 20 ሚሊዮን ዶላር ከንፁህ ቴክኖሎጂ ፈንድ እንዲሁም 10 ሚሊዮን ዶላር ከአፍሪካ ዘላቂ የኢነርጂ ፈንድ የተገኘ መሆኑንም ጠቅሷል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ባንኩ-ለአይሻ-አንድ-የንፋስ-ኃይል-ማመንጫ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም

ማህበሩ የሠራተኛውን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ሥራዎችን አከናውኗል ‎....///..... ‎ ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር በ2018 በጀት ዓመት የተቋሙን ሠራተኛ ተጠቃሚነት የ
+5
ማህበሩ የሠራተኛውን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ሥራዎችን አከናውኗል ‎....///..... ‎ ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር በ2018 በጀት ዓመት የተቋሙን ሠራተኛ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ሥራዎችን ማከናወኑን የማህበሩ ሊቀመንበር አቶ ዳንኤል ገ/ሚካኤል ገለጹ። ‎ ‎የሪጅን፣ የኃይል ማመንጫ፣ የዋናው መ/ቤት የዘርፍ ተወካዮች የሚሳተፉበትና ለሁለት ቀናት የሚቆየው የማህበሩ 11ኛ መደበኛ የምክር ቤት ስብሰባ በአዳማ ከተማ ተስፋዬ ኦሎምፒክ ሆቴል በዛሬው ዕለት መካሄድ ጀምሯል። ‌‎በስብሰባው ላይ የ2018 በጀት ዓመት ሪፖርትን ያቀረቡት አቶ ዳንኤል ገ/ሚካኤል የሠራተኛውን መብትና ጥቅም እንዲሁም የሙያ ደህንነትና ጤንነትን በማረጋገጥ የኢንዱስትሪ ሰላም እንዲፈጠር ከተቋሙ ማኔጅመንትና ሥራ አመራር ቦርድ ጋር ሕግና ሥርዓትን ተከትሎ በትብብር እየሰራ ነው ብለዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ማህበሩ-የሠራተኛውን-ተጠቃሚነት-የሚያረ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ.ም

ተቋሙ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ሥልጠና መስጠት ጀመረ …//…. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከተለያዩ ተቋማት ጋር ያለውን የሥራ ግንኙነት ለማጠናከርና የአቅም ግንባ
+6
ተቋሙ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ሥልጠና መስጠት ጀመረ …//…. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከተለያዩ ተቋማት ጋር ያለውን የሥራ ግንኙነት ለማጠናከርና የአቅም ግንባታ ሥራዎችን ለማስፋፋት በያዘው ዕቅድ መሠረት ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለሙያዎች ሥልጠና መስጠት መጀመሩን አስታወቀ። በተቋሙ የኢትዮ ፓወር አካዳሚ የሥልጠና ክፍል ተወካይ ሥራ አስኪያጅ አቶ ክብሮም ገብሬ እንደገለፁት ሥልጠናው በፓወር ላይን ሲስተም ካድ (Power Line System CAD) ሶፍትዌር እና በኃይል ማከፋፈያና የሥርጭት መስመር ዲዛይን ላይ ትኩረት ያደረገ ነው፡፡ ለአስር ቀናት በሚቆየው በዚህ ሥልጠና ባለሙያዎቹ በዘመናዊ የኮምፒውተር ፕሮግራሞች የታገዘ የኃይል ሥርጭት ቁጥጥር ስልትና በዲጂታል ቴክኖሎጂ ላይ የተመሰረቱ የዲዛይን ሥራዎችን እንዲቀስሙ ይደረጋል። ይህም ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን እና የሥርጭት መስመሮችን ለመቆጣጠርና ዲዛይን ለመንደፍ ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግላቸው አብራርተዋል። ‎ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-ለኢትዮጵያ-ኤሌክትሪክ-አገልግሎት&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም

የተቋሙን የፕሮጀክት አፈጻጸም የሚያሻሽሉ ሥልጠናዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ - ኢንጂነር ኤፍሬም ወ/ኪዳን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በፕሮጀክት አፈጻጸምና በሌሎች ዘርፎች ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ለ
+5
የተቋሙን የፕሮጀክት አፈጻጸም የሚያሻሽሉ ሥልጠናዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ - ኢንጂነር ኤፍሬም ወ/ኪዳን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በፕሮጀክት አፈጻጸምና በሌሎች ዘርፎች ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ለመሙላት የሚያስችሉ አቅም ግንባታ ሥልጠናዎችንና የልምድ ልውውጦችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ፡፡ ተቋሙ ውጤታማ የፕሮጀክት አስተዳደር ሥርዓትን በመዘርጋት የማስፈጸም አቅሙን ለማሳደግ ለፕሮጀክት ዳይሬክተሮች እና ሥራ አስኪያጆች ያዘጋጀው የመጀመሪያው ዙር ሥልጠና የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በስኬት ተጠናቋል። በሥልጠናው ማጠናቀቂያ መድረክ ላይ የተገኙት የተቋሙ የጀነሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ወልደኪዳን እንደገለጹት ተቋሙ ባለፉት ሦስት አሥርት ዓመታት በርካታ የኃይል ማመንጫ፣ ማከፋፈያ ጣቢያዎች እና የማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክቶችን ሲያከናውን ቢቆይም ወጥ የሆነ ተቋማዊ የፕሮጀክት አስተዳደር ሥርዓት ባለመኖሩ የተገኙ ዕውቀቶች በግለሰቦች አእምሮ ውስጥ ተበታትነው ቆይተዋል። ‎ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የተቋሙን-የፕሮጀክት-አፈጻጸም-የሚያሻሽ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ.ም

ፕሮጀክቶችን ውጤታማ ለማድረግ አመራሩና ሠራተኛው በቁርጠኝነት ሊሠሩ ይገባል ….//….. በተቋሙ እየተከናወኑ ያሉ ፕሮጀክቶችን ውጤታማ ለማድረግና የአሠራር ክፍተቶችን ለመሙላት አመራሩና ሠራተኛው በላቀ ቁርጠኝነትና በጋራ አስተሳሰብ ሊመራ እንደሚገባ የዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ አሳሰቡ። ኃላፊው ይህንን መልዕክት ያስተላለፉት ለፕሮጀክት ዳይሬክተሮች እና ሥራ አስኪያጆች ለአምስት ቀናት የተሰጠውን የፕሮጀክት አስተዳደር ወርክሾፕ ሥልጠና ባጠቃለሉበት ወቅት ሲሆን ተቋሙን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር መሠረታዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በተቋሙ ውስጥ መሠረታዊ የእውቀትና የቴክኒክ ክህሎት ችግር በስፋት ባይስተዋልም ባለው እውቀት ልክ ሥራዎችን መሬት ላይ አውርዶ ተግባራዊ የማድረግ ውስንነት እንደሚስተዋል የገለፁት ኃላፊው ይህንን ክፍተት ለመቅረፍ አመራሩና ሠራተኛው ራሱን ዘወትር ለውይይትና ለሥራ ዝግጁ ማድረግ እንዳለበት አሳስበዋል። በተቋሙ የሚሰጡ ሥልጠናዎች በአስተሳሰብና በክህሎት ላይ ያመጡት ለውጥ በየጊዜው መገምገም እንዳለበትና ክትትልና ድጋፉ በአመራሩ በጎ ፈቃድ ላይ ብቻ ሳይሆን በመዋቅራዊ አሠራር ሊመራ እንደሚገባም ጠቁመዋል። ወደፊት እንደዚህ ዓይነት ሥልጠናዎች ሲዘጋጁ መረጃዎችን በምስል፣ በድምፅ እንዲሁም በጽሑፍ ሰንዶ በመያዝ በቤተ መጻሕፍት እንዲቀመጥና የሁሉም እውቀትና ክህሎት በተከታታይነት እንዲያድግ እንደሚደረግም አያይዘው ገልጸዋል። አቶ ሙላት በተቋሙ የሚገነቡ የአብዛኞቹ ፕሮጀክቶች መስተጓጎል ከሃገራዊ ችግሮች ባለፈ የኃላፊዎች እና የፕሮጀክት ሥራ አስኪያጆች የቁርጠኝነት ጉድለት መሆኑን በመግለጽ ቁርጠኝነት ያላቸው ኃላፊዎች ፕሮጀክቶቻቸው ወደፊት ሲራመዱ በአንጻሩ ቁርጠኝነት የሌላቸው ግን ወደኋላ ሲቀሩ እንደሚስተዋሉና በመካከላቸው የልምድ ልውውጥ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል። ተቋሙ ከተቀመጡለት ዕቅዶችና ግዴታዎች ውስጥ ከ50 በመቶ በላይ ለማሳካት በቁርጠኝነት መንቀሳቀስ እንዳለበት ያሳሰቡት ኃላፊው አንዱ ብቻውን እየሮጠ ሌላው ወደኋላ ከቀረ ተጎታች ስለሚኖር ስኬት ሊመጣ እንደማይችልና ከግላዊ አስተሳሰብ ወጥቶ በጋራ ማሰብና መደጋገፍ እንዳለበት አስገንዝበዋል። የመረጃ አያያዝ እና ሥርዓታማ የፕሮጀክት ርክክብ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ መሠራት እንዳለበት ያነሱት ኃላፊው በአሁኑ ወቅት በመረጃ አያያዝ ላይ ያለው ክፍተት ታርሞ መረጃዎች ወጥና ተመሳሳይ እንዲሁም ነባራዊ ሁኔታውን በትክክል የሚያሳዩ መሆን አለባቸው ብለዋል። ቀደም ሲል ለነበሩ የፕሮጀክት መስተጓጎሎች በዋናነት በምክንያትነት የተጠቀሰው ጤናማ የፕሮጀክት ርክክብ አለመደረጉ በመሆኑ ከአሁን በኋላ ከአንድ ሰው ወደ ሌላ ሰው የሚደረጉ ርክክቦች በጥብቅ ሥርዓት እንዲመሩ አቅጣጫ አስቀምጠዋል። በመቀጠልም በተቋሙ አንዳንድ አካላት ዘንድ የሚስተዋሉ የሥራ ማመካኛዎችን በጥብቅ የተቹት አቶ ሙላት በተቋሙ የተዘጋጀው የሥልጣን ውክልና (Delegation of Power)  አሠራር ሥራን የሚያሰራ ነው። በመሆኑም ለማይሠራ ሰው መሸሸጊያ ወይም ማመካኛ መሆን የለበትም። ይሁንና ለአሰራር አመቺ ያልሆነ ጉዳይ ካሉ በሂደት የሚታይ ወይም የሚስተካከል መሆኑን አስገንዝበዋል። ይሁንና አሁን ያለው የሥራ አመራር አካል ከልማዳዊ አሠራር ውጪ የሚያስብ ተጨማሪ ርቀት የሚጓዝ፣ የሚያዳምጥና ተለዋዋጭ በመሆኑ ይህንን መልካም አጋጣሚ በመጠቀም የሕዝባችንን የኤሌክትሪክ ጥያቄ በአስቸኳይ መፍታት እንደሚገባ አስታውቀዋል። ለሥራ ማነቆ የሆኑ ጉዳዮችን ፈትሾ መፍትሔ ለመስጠት ማኔጅመንቱ 24 ሰዓት ሙሉ ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን ገልፀዋል። በመጨረሻም የወደፊት አቅጣጫዎችን አስመልክተው ሲናገሩ ማኔጅመንቱ ለውጥ የሚፈልግና ሌላውን የሚያሳትፍ በመሆኑ የሥራውን ስኬት ሊያደናቅፉ የሚችሉ አሉታዊ ወሬዎች ወይም አሉባልታዎችን ችላ በማለት ሠራተኛው ትኩረቱን በሥራው ላይ ብቻ በማድረግ የተቋሙን ራዕይ ማሳካት እንዳለበት አስገንዝበው ሥልጠናውን ላዘጋጁት አካላት በሙሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+6

በቢሾፍቱ ከተማ አጋጥሞ የነበረው የኃይል መቋረጥ መስተካከሉ ተገለፀ በቢሾፍቱ ቁጥር 2 ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ባጋጠመ የቴክኒክ ብልሽት ምክንያት በከተማዋ በከፊል ተቋርጦ
+1
በቢሾፍቱ ከተማ አጋጥሞ የነበረው የኃይል መቋረጥ መስተካከሉ ተገለፀ በቢሾፍቱ ቁጥር 2 ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ባጋጠመ የቴክኒክ ብልሽት ምክንያት በከተማዋ በከፊል ተቋርጦ የነበረው የኤሌክትሪክ አገልግሎት ዳግም መመለሱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ 2 ሪጅን አስታወቀ። የሪጅኑ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮሃንስ ተስፋዬ እንደገለፁት የኃይል መቋረጡ ያጋጠመው ከቀኑ 8:00 ሰዓት ላይ ነው። ብልሽቱ የተከሰተው በጣቢያው ውስጥ ከሚገኙት ሦስት ትራንስፎርመሮች መካከል በአንደኛው ትራንስፎርመር የደህንነት መከላከያ (Earthing Transformer) ላይ በመሆኑ ከጣቢያው በ15 ኪሎ ቮልት ኤሌክትሪክ የሚያገኙ የቢሾፍቱ ከተማና አካባቢው ክፍሎች አገልግሎቱ ተቋርጦባቸው ቆይቷል። ይህንን ችግር ለመቅረፍ በጣቢያው የሚገኙትን ቀሪዎቹን ሁለት ትራንስፎርመሮች በመጠቀም የኃይል ማመጣጠን ሥራ የተከናወነ ሲሆን የተቋረጠውን የኤሌክትሪክ አቅርቦት መልሶ ማቅረብ ተችሏል። በአሁኑ ወቅትም የቴክኒክ ብልሽት ያጋጠመውን የትራንስፎርመር የደህንነት መከላከያ በአዲስ ለመቀየር የሚያስችል ተግባራዊ እንቅስቃሴ መጀመሩን አቶ ዮሃንስ አክለው ገልጸዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ.ም

ኢኢፒ ማስተር ተግባራዊ በመሆኑ በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን ሪጅኑ ገለፀ ….//….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሴንትራል አንድ ሪጅን በራስ ኃይል የበለፀገ ኢኢፒ ማስተር የተሰኘ ሶፍትዌር በአስ
+7
ኢኢፒ ማስተር ተግባራዊ በመሆኑ በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን ሪጅኑ ገለፀ ….//….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሴንትራል አንድ ሪጅን በራስ ኃይል የበለፀገ ኢኢፒ ማስተር የተሰኘ ሶፍትዌር በአስር ሪጅኖች ላይ ተግባራዊ ሆኖ አበረታች ውጤት መገኘቱን የሪጅኑ ዳይሬክተር ገለፁ። የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ደረጀ ገዛኸኝ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኛ ማህበር የስራ አስፈፃሚ ቡድን በሪጂኑ ጉብኝት ባደረገት ወቅት እንደተናገሩት ይህ የዲጂታል ሲስተም የተበታተነ እና ማኑዋል አሰራርን በማስቀረት አስተማማኝ የመረጃ አያያዝ ስርዓት እንዲሰፍን አስችሏል። በተጨማሪም የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎችን በመመዝገብ የመረጃ ተደራሽነትን ከማሳደጉ ባሻገር ለቀጣይ ስራዎች ግብአት እንደሚሆንም ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። ይህ የዲጂታል ሲስተም በራስ ኃይል በልፅጎ ወደ ተግባር መግባቱ ተቋሙ በሁሉም ዘርፍ አቅም ያላቸው ባለሙያዎች ባለቤት መሆኑን ያሳያል ያሉት ደግሞ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኛ ማህበር ፕሬዚዳንት አቶ ዳንኤል ገ/ሚካኤል ናቸው። ‎ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ኢኢፒ-ማስተር-ተግባራዊ-በመሆኑ-በርካታ-ው&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ.ም

በኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶ መውደቅ ምክንያት ኃይል ተቋርጧል .......///....... ከሽሬ - ሁመራ በተዘረጋው የ230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ በአንድ የብረት ምሰሶ መውደ
በኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶ መውደቅ ምክንያት ኃይል ተቋርጧል .......///....... ከሽሬ - ሁመራ በተዘረጋው የ230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ በአንድ የብረት ምሰሶ መውደቅ ምክንያት በሁመራ ከተማና በአካባቢው ለጊዜው የኤሌክትሪክ አቅርቦት መቋረጡን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምዕራብ ሪጅን አስታወቀ የሪጅኑ የማስተላለፊያ መስመሮች ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ በላይነህ ልጅዓለም እንዳስታወቁት ችግሩ ያጋጠመው በእንድሪስ ከተማ አካባቢ ነው። በዚህም ምክንያት ማኅበረሰቡ ያጋጠመውን የኃይል መቆራረጥ ችግር ለመፍታት የሪጅኑ ባለሙያዎች ከነገ ጀምሮ ወደ ስፍራው በማምራት መንስኤውን ያጣራሉ። የወደቀውን ምሰሶ በአፋጣኝ መልሶ በመትከልና የኤሌክትሪክ አገልግሎቱን በተቻለ ፍጥነት ወደ ነበረበት ለመመለስ ተቋሙ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ይገኛል። በመሆኑም አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ የተከበራችሁ የአካባቢው ነዋሪዎች ያጋጠመውን ችግር በቅንነትና በትዕግሥት እንድታሳልፉት ተቋሙ ጥሪውን ያቀርባል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ.ም

#COP32 በCOP 32 የምናስተጋባው የፀሐይና የንፋስ ኃይል ሚና .......///....... የፀሐይና የንፋስ ኃይልን በስፋት ጥቅም ላይ ማዋል የአየር ንብረት ለውጥን ለመግታት ፍቱን መፍትሄ ነው፡
#COP32 በCOP 32 የምናስተጋባው የፀሐይና የንፋስ ኃይል ሚና .......///....... የፀሐይና የንፋስ ኃይልን በስፋት ጥቅም ላይ ማዋል የአየር ንብረት ለውጥን ለመግታት ፍቱን መፍትሄ ነው፡፡ ይህንን ራዕይ በCOP 32 እናንጸባርቃለን፡፡ #CleanEnergy #COP32 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 09 ቀን 2018 ዓ.ም

#COP32 ንጹህ ኃይል ለቀጣይ ትውልድ! .......///....... የአየር ንብረት ለውጥን መከላከል የአንድ ወገን ብቻ ሳይሆን የጋራ ኃላፊነታችን ነው፡፡ በCOP 32 የጋራ ድምፃችንን እናሰማለን!
#COP32 ንጹህ ኃይል ለቀጣይ ትውልድ! .......///....... የአየር ንብረት ለውጥን መከላከል የአንድ ወገን ብቻ ሳይሆን የጋራ ኃላፊነታችን ነው፡፡ በCOP 32 የጋራ ድምፃችንን እናሰማለን! ተቋማችን በCOP 32 ጉባኤ ላይ ከተፈጥሮ ጋር የተስማማ የልማት አሻራችንን ለማሳየት ተዘጋጅቷል፡፡ #Sustainability #COP32 #ClimateAction 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 08 ቀን 2018 ዓ.ም

በተቋሙ የተበታተኑ ዕውቀቶችን አሰባስቦ መጠቀም ያስፈልጋል- አቶ አታላይ አበበ ..…///….. ተቋሙ በየጊዜው የሚሰጣቸው ስልጠናዎች የተበታተኑ ዕውቀቶችን በማሰባሰብ የተሻለ ተቋማዊ ግንባታ ለማከናወ
+8
በተቋሙ የተበታተኑ ዕውቀቶችን አሰባስቦ መጠቀም ያስፈልጋል- አቶ አታላይ አበበ ..…///….. ተቋሙ በየጊዜው የሚሰጣቸው ስልጠናዎች የተበታተኑ ዕውቀቶችን በማሰባሰብ የተሻለ ተቋማዊ ግንባታ ለማከናወን ትልቅ ፋይዳ እንዳላቸው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰው ኃይል ሥራ አስፈጻሚ አቶ አታላይ አበበ ገለጹ። ሥራ አስፈጻሚው ይህንን ያሉት ለፕሮጀክት ዳይሬክተሮች እና ሥራ አስኪያጆች በፕሮጀክት አስተዳደር ዙሪያ በተዘጋጀው ስልጠና ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት ነው። አቶ ታላይ በመልዕክታቸው እንደገለጹት ስልጠናው በየፕሮጀክቶቹ ላይ የተለያየ እውቀትና ልምድ ያላቸው ባለሙያዎች ያላቸውን እውቀቶችና ልምዶች እርስ በርስ በመለዋወጥ የጋራ ግንዛቤ ለመፍጠር ከፍተኛ እገዛ ያደርጋል። ስልጠናውን በሚገባ ተከታትለው የሚያልፉ ብቁ ባለሙያዎች እንደሚወጡ ሙሉ እምነት እንዳላቸው የገለጹት አቶ አታላይ ሰልጣኞች የሚሰጠውን ስልጠና በትኩረት እንዲከታተሉ አሳስበዋል፡፡ ‎ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በተቋሙ-የተበታተኑ-ዕውቀቶችን-አሰባስቦ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 06 ቀን 2018 ዓ.ም

‎በኃይል መሰረተ ልማት ላይ ስርቆት ሲፈፅም የነበረ ግለሰብ በሕብረተሰቡ ንቁ ተሳትፎ በሕግ ቁጥጥር ሥር ዋለ፤ ‎……///…. በኃይል መሰረተ ልማት ላይ ስርቆት ሲፈፅም የነበረ ግለሰብ በሕብረተሰቡ ንቁ ተሳትፎ እጅ ከፍንጅ ተይዞ በሕግ ቁጥጥር ስር መዋሉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ ሁለት ሪጅን ገለፀ ፡፡ የሪጅኑ የማስተላለፊያ መስመሮች እና ኦፕቲካል ፋይበር ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጎሳዬ ደምሴ እንደገለፁት ስርቆቱ የተፈፀመው ትናንት ከሌሊቱ 8 ሰዓት አካባቢ ልዩ ቦታው ወረገኑ በተባለ አካባቢ ከቃሊቲ ወደ ቦሌ ለሚ በተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ ነው። ግለሰቡ ለጊዜው ከተሰወሩ አራት ግብረ አበሮቹ ጋር በመሆን በከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ የብረት ምሰሶ ላይ ወጥተው የኮንዳክተር ሽቦ ሲቆርጡ የአካባቢው ነዋሪዎች በተጠንቀቅ በመከታተል ለፀጥታ አካላት ጥቆማ አድርገዋል። ለሕብረተሰቡንና ለፀጥታ አካላት ፈጣን ምላሽ አድናቆታቸውን የቸሩት አቶ ጎሳዬ አንደኛው ስርቆት ፈፃሚ በሕዝቡና በፀጥታ ኃይሉ መከበቡን ሲረዳ ከብረት ምሰሶው ላይ ሳይወርድ እዚያው ለመቆየት መወሰኑን ገልፀዋል። ይህ ስርቆት ፈፃሚ ለመውረድ ፍቃደኛ ባይሆንም የቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 የፀጥታ አካላትና የአካባቢው ማኅበረሰብ በጋራ ባደረጉት ከፍተኛ የሰዓታት ትንቅንቅና ትብብር ዛሬ ከቀኑ 8:30 ላይ ከምሰሶው ላይ እንዲወርድ ተደርጎ በሕግ ቁጥጥር ሥር ሊውል መቻሉን ተናግረዋል። ለጊዜው የተሰወሩትን አራት ግብረ አበሮች በሕግ ፊት ለማቅረብ የፀጥታ አካላት ጥብቅ ክትትል እያደረጉ መሆኑን የገለፁት ሥራ አስኪያጁ የመሰረተ ልማት ጥበቃ የጋራ ኃላፊነት መሆኑን በተግባር ላሳዩት የወረዳ 12 የፀጥታ አካላትና ለመላው ማኅበረሰብ አቶ ጎሳዬ የላቀ ምስጋና አቅርበዋል። አያይዘውም በኃይል መሠረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀም መሰል የስርቆት ተግባር ለኃይል መቋረጥ ምክንያት ከመሆኑም በላይ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ትልቅ ክስረት የሚያስከትል በመሆኑ መሰል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላት ሁሉ ከጥፋት መንገዳቸው ሊታቀቡ እንደሚገባ አሳስበዋል። የኢነርጂ አዋጅ 810/2006 አንቀጽ 26 በግልፅ እንደሚደነግገው በኃይል ማመንጫ፣ ማስተላለፊያ ወይም ማከፋፈያ ተቋማት ላይ ጉዳት ያደረሰ ማንኛውም ወንጀለኛ ከ5 እስከ 15 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት ወይም እስከ 50 ሺህ ብር በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ ወይም በሁለቱም ጠንካራ ቅጣቶች እንደሚቀጣ በማስታወስ ሕብረተሰቡ የጀመረውን ጥብቅ ጥበቃና ክትትል አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 04 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+2

‎በኃይል መሰረተ ልማት ላይ ስርቆት ሲፈፅም የነበረ ግለሰብ በሕብረተሰቡ ንቁ ተሳትፎ በሕግ ቁጥጥር ሥር ዋለ፤ ‎……///…. በኃይል መሰረተ ልማት ላይ ስርቆት ሲፈፅም የነበረ ግለሰብ በሕብረተሰቡ ንቁ ተሳትፎ እጅ ከፍንጅ ተይዞ በሕግ ቁጥጥር ስር መዋሉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ ሁለት ሪጅን ገለፀ ፡፡ የሪጅኑ የማስተላለፊያ መስመሮች እና ኦፕቲካል ፋይበር ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጎሳዬ ደምሴ እንደገለፁት ስርቆቱ የተፈፀመው ትናንት ከሌሊቱ 8 ሰዓት አካባቢ ልዩ ቦታው ወረገኑ በተባለ አካባቢ ከቃሊቲ ወደ ቦሌ ለሚ በተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ ነው። ግለሰቡ ለጊዜው ከተሰወሩ አራት ግብረ አበሮቹ ጋር በመሆን በከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ የብረት ምሰሶ ላይ ወጥተው የኮንዳክተር ሽቦ ሲቆርጡ የአካባቢው ነዋሪዎች በተጠንቀቅ በመከታተል ለፀጥታ አካላት ጥቆማ አድርገዋል። ለሕብረተሰቡንና ለፀጥታ አካላት ፈጣን ምላሽ አድናቆታቸውን የቸሩት አቶ ጎሳዬ አንደኛው ስርቆት ፈፃሚ በሕዝቡና በፀጥታ ኃይሉ መከበቡን ሲረዳ ከብረት ምሰሶው ላይ ሳይወርድ እዚያው ለመቆየት መወሰኑን ገልፀዋል። ይህ ስርቆት ፈፃሚ ለመውረድ ፍቃደኛ ባይሆንም የቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 የፀጥታ አካላትና የአካባቢው ማኅበረሰብ በጋራ ባደረጉት ከፍተኛ የሰዓታት ትንቅንቅና ትብብር ዛሬ ከቀኑ 8:30 ላይ ከምሰሶው ላይ እንዲወርድ ተደርጎ በሕግ ቁጥጥር ሥር ሊውል መቻሉን ተናግረዋል። ለጊዜው የተሰወሩትን አራት ግብረ አበሮች በሕግ ፊት ለማቅረብ የፀጥታ አካላት ጥብቅ ክትትል እያደረጉ መሆኑን የገለፁት ሥራ አስኪያጁ የመሰረተ ልማት ጥበቃ የጋራ ኃላፊነት መሆኑን በተግባር ላሳዩት የወረዳ 12 የፀጥታ አካላትና ለመላው ማኅበረሰብ አቶ ጎሳዬ የላቀ ምስጋና አቅርበዋል። አያይዘውም በኃይል መሠረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀም መሰል የስርቆት ተግባር ለኃይል መቋረጥ ምክንያት ከመሆኑም በላይ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ትልቅ ክስረት የሚያስከትል በመሆኑ መሰል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላት ሁሉ ከጥፋት መንገዳቸው ሊታቀቡ እንደሚገባ አሳስበዋል። የኢነርጂ አዋጅ 810/2006 አንቀጽ 26 በግልፅ እንደሚደነግገው በኃይል ማመንጫ፣ ማስተላለፊያ ወይም ማከፋፈያ ተቋማት ላይ ጉዳት ያደረሰ ማንኛውም ወንጀለኛ ከ5 እስከ 15 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት ወይም እስከ 50 ሺህ ብር በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ ወይም በሁለቱም ጠንካራ ቅጣቶች እንደሚቀጣ በማስታወስ ሕብረተሰቡ የጀመረውን ጥብቅ ጥበቃና ክትትል አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 04 ቀን 2018 ዓ.ም

#COP32 ተቋማችን ለተሻለችና ለአረንጓዴ ዓለም ያለውን ጽኑ ቁርጠኝነት ይዞ ወደ COP 32 ያመራል! የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የምናደርገውን ጉዞ ይከታተሉ፡፡ #COP32 #GreenEnergy
#COP32 ተቋማችን ለተሻለችና ለአረንጓዴ ዓለም ያለውን ጽኑ ቁርጠኝነት ይዞ ወደ COP 32 ያመራል! የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የምናደርገውን ጉዞ ይከታተሉ፡፡ #COP32 #GreenEnergy 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 04 ቀን 2018 ዓ.ም

የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ባሉበት በ25 ሜትር ራዲየስ ውስጥ ቁፋሮ ማካሄድ የሚከለክል መመሪያ ፀደቀ ……///……. የአዲስ አበባ ከተማ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን በከተማዋ ክልል ውስጥ የሚካሄደውን
+2
የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ባሉበት በ25 ሜትር ራዲየስ ውስጥ ቁፋሮ ማካሄድ የሚከለክል መመሪያ ፀደቀ ……///……. የአዲስ አበባ ከተማ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን በከተማዋ ክልል ውስጥ የሚካሄደውን የኮንስትራክሽን ማዕድናት ፍለጋ፣ ምርት እና ስርጭት የሚቆጣጠር አዲስ መመሪያ አውጥቷል፡፡ "የኮንስትራክሽን ማዕድን ፈቃድ አፈጻጸም መመሪያ ቁጥር 191/2018" በሚል ተግባራዊ እንዲሆን የፀደቀው መመሪያው ከማዕድን ቁፋሮ ጋር በተያያዘ ይታዩ የነበሩ የአሰራር ክፍተቶችን በመድፈን ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት ሥርዓት ለመዘርጋት ያለመ መሆኑ ተጠቅሷል። በመመሪያው መሰረት ከከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች በ25 ሜትር ራዲየስ ውስጥ ማንኛውንም ቁፋሮ ማካሄድ የተከለከለ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ከመኖሪያ መንደሮችና ከኢንዱስትሪ ፓርኮች በ500 ሜትር ራዲየስ ውስጥ እንዲሁም ከወንዝ ዳርቻዎች በ30 ሜትር ራዲየስ ውስጥ ቁፋሮ ማከናወን ተከልክሏል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 03 ቀን 2018 ዓ.ም

የወደፊት ዕጣ ፈንታችን በምንጠቀመው የኃይል አማራጭ ላይ የተመሰረተ ነው፡፡ በCOP 32 ጉባኤ ላይ ዘላቂ መፍትሄዎችን በጋራ እንዘይዳለን፡፡ #Innovation #COP32 #GreenEnergy 💡 "
የወደፊት ዕጣ ፈንታችን በምንጠቀመው የኃይል አማራጭ ላይ የተመሰረተ ነው፡፡ በCOP 32 ጉባኤ ላይ ዘላቂ መፍትሄዎችን በጋራ እንዘይዳለን፡፡ #Innovation #COP32 #GreenEnergy 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 03 ቀን 2018 ዓ.ም

‎ፕሮጀክቱ በግብርና ሥራችን ምርታማ እንድንሆን አስችሎናል፤ -የባንካ ቀበሌ አርሶ አደሮች ‎.....///..... ‎የኮይሻ የውኃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ያከናወናቸው የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎች በግ
+9
‎ፕሮጀክቱ በግብርና ሥራችን ምርታማ እንድንሆን አስችሎናል፤ -የባንካ ቀበሌ አርሶ አደሮች ‎.....///..... ‎የኮይሻ የውኃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ያከናወናቸው የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎች በግብርና ሥራቸው ምርታማ እንዲሆኑ እንዳስቻላቸው በጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳ የባንካ ቀበሌ አርሶ አደሮች ገለጹ። ‎ ‎የአካባቢው ነዋሪ የሆኑት አርሶ አደር ደነቀ ደስታ እንደገለጹት ፕሮጀክቱ ከመጀመሩ በፊት በአካባቢው የመንገድን መሰረተ-ልማት ችግር የነበረ በመሆኑ ነዋሪው እርስ በእርስ ለመገናኘትና አካባቢውን አልምቶ ወደ ገበያ ለማውጣት አስቸጋሪ ነበር። ‎ ‎በተለይም በኦሞ ወንዝ ላይ ድልድይ ባለመኖሩ የኮንታንና የጎፋ ሕዝቦችን ከመለየቱም በላይ ታላቅ ወንድማቸውን ጨምሮ በርካታ ሠዎች በውኃ ሙላት ተወስደው ሕይወታቸው ማለፉን አስታውሰዋል። ‎ ‎የኮይሻ ፕሮጀክት በኦሞ ወንዝ ላይ ሁለቱን ሕዝቦች የሚያገናኝ ድልድይ እና መንገድ በመስራት የአካባቢው ማህበረሰብ ከምርቱ ተጠቃሚ እንዲሆን ማስቻሉን ጠቁመዋል። ‎ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ፕሮጀክቱ-በግብርና-ሥራችን-ምርታማ-እን&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 02 ቀን 2018 ዓ.ም

የፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ በፍጥነት እየተከናወነ ነው፤ ….///…. የኮይሻ የውኃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታ ሥራ በፍጥነትና በጥራት እየተከናወነ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፕሮጀክቱ ምክት
+9
የፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ በፍጥነት እየተከናወነ ነው፤ ….///…. የኮይሻ የውኃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታ ሥራ በፍጥነትና በጥራት እየተከናወነ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፕሮጀክቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ገለጹ፡፡ ምክትል ሥራ አስኪያጁ ኢንጂነር አባይነህ ጌትነት እንደገለጹት የኃይል ማመንጫ ግድቡ ከባህር ወለል በላይ 179 ሜትር ቁመት እና 2 ነጥብ 4 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ውኃ የመያዝ አቅም እንዲኖረው ሆኖ በፍጥነት እየተገነባ ይገኛል። ቀደም ባለው ጊዜ በፋይናንስ እጥረት ምክንያት የግንባታ መዘግየቶች አጋጥመውት የነበረ ቢሆንም አሁን ላይ መንግስት ቀጥተኛ የፋይናንስ ድጋፍ በማድረጉ እና ተቋማዊ የክፍያ አፈጻጸሞች በመሻሻላቸው ያለ ምንም የፋይናንስ ችግር ግንባታው እየተፋጠነ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በግድቡ የተለያዩ አካላት ላይ የሚከናወኑ የግንባታ ሥራዎች በመርኃ ግብራቸው መሰረት እየሄዱ ይገኛሉ ያሉት ኢንጂነር አባይነህ ከውጭ የሚመጡ አስፈላጊ ግብዓቶችም ያለምንም መቆራረጥ ወደ ሣይቱ እየገቡ ሥለመሆኑ አብራርተዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የፕሮጀክቱ-የግንባታ-ሥራ-በፍጥነት-እየተ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 02 ቀን 2018 ዓ.ም