en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 553 subscribers, ranking 8 406 in the Technologies & Applications category and 2 161 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 553 subscribers.

According to the latest data from 19 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -3 over the last 30 days and by -5 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 26.69%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.00% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 150 views. Within the first day, a publication typically gains 2 332 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 20 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 553
Subscribers
-524 hours
+97 days
-330 days
Posts Archive
ተቋሙ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 92 ቢሊዮን ብር ገቢ አግኝቷል ‎........///....... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2018 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገራት ከቀረበ የኃይል ሽያጭ እና ተጓዳኝ አገልግሎቶች 92 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ፡፡ ‎ ‌‎በተቋሙ የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ተወካይ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ያለውአይቀር ማንደፍሮ የተቋሙን የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ባቀረቡበት ወቅት እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 24 ሺህ 970 ጊጋ ዋት ስዓት ኃይል ለሀገር ውስጥና ለጎረቤት ሀገራት በመሸጥ 90 ነጥብ 16 ቢሊዮን ብር ገቢ ተገኝቷል። በበጀት ዓመቱ ለውጭ ሀገራት እና ለቴክኖሎጂ ካምፓኒዎች ከቀረበ የኃይል ሽያጭ 366 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር መገኘቱንና ይህም ካለፈው በጀት ዓመት የ138 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ብልጫ እንዳለው ገልፀዋል፡፡ ‎ በፕሮጀክቶች አፈጻጸም ላይ የተሻለ ውጤት መመዝገቡን የተናገሩት አቶ ያለውአይቀር ባለፉት ዘጠኝ ወራት ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ጨምሮ የአሰላና አይሻ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ወደ ኦፕሬሽን መግባታቸውን አስታውሰዋል፡፡ በተቋሙ የኮርፖሬት ፋይናንስና ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ በበኩላቸው እንደገለፁት ገቢው ከኃይል ሽያጭ፣ ከኦፕቲካል ፋይበር ኪራይ፣ ከማማከር እና ካለፈው በጀት ዓመት ከዞረ ተሰብሳቢ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ለገቢው ከፍ ማለት ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ወደ ኦፕሬሽን መግባቱ፣ የኃይል ምርት እና አቅርቦት መጠን ማደጉ፣ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች የኃይል ሽያጭ በውጭ ምንዛሪ መከናወኑ፣ የብር ከዶላር ጋር ያለው ምንዛሪ ማደጉ፣ መንግስት ለተቋሙ ያደረገው የእዳ ሽግሽግ፣ የታሪፍ ማሻሻያ እና የተቋሙ የገቢ አሰባሰብ ማደግን አንስተዋል፡፡ የተቋሙ ሠራተኞች እና የሥራ መሪዎችም በቀረበው ሪፖርት እና አፈፃፀም ላይ ጥያቄዎች አቅርበው በሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ ቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+3

photo content
+9

‎ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ27 ሺህ ጊጋ ዋት ስዓት በላይ ኃይል ተመርቷል ‎......///..... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2018 በጀት ዓመት ያለፉት ዘጠኝ ወራት ከ27 ሺህ በላይ ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል መመረቱን አስታወቀ። ‎ ‎የኮርፖሬት ፕላኒግ ተወካይ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ያለውአይቀር ማንደፍሮ የተቋሙን የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ባቀረቡበት ወቅት እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 29 ሺህ 381 ነጥብ 8 ጊጋ ዋት ሰዓት ለማምረት ታቅዶ 27 ሺህ 105 ነጥብ 6 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ማምረት ተችሏል። ‎ ‎ይህም የዕቅዱ 92 ነጥብ 4 በመቶ መሳካቱን የሚያሳይ ሲሆን በ2017 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከተመረተው ኃይል የ27 ነጥብ 3 በመቶ ብልጫ ያለው መሆኑን አብራርተዋል። ‎ ‎ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከመነጨው ኃይል ውስጥ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ 50 ነጥብ 8 በመቶ እንዲሁም የጊቤ ሦስትና የበለስ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የ18 ነጥብ 3 በመቶ እና የ6 ነጥብ 9 በመቶ በማመንጨት ከፍተኛ ድርሻ እንደነበራቸው ተጠቅሷል። ‎ ‎በበጀት ዓመቱ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ጨምሮ የአይሻና የአሰላ ንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ወደ ኦፕሬሽን በመግባታቸው የማመንጨት አፈጻጸሙ የተሻለ እንዲሆን ማድረጉን ጠቅሰዋል። ‎ ‎የባለሙያዎችን አቅም በማሳደግ ጠንካራና ቀጣይነት ያላቸው የጥገና ሥራዎች ሲከናወኑ እንዲሁም በማዕቀፍ ግዥ ጭምር የመለዋወጫ ዕቃዎች ሲቀርቡ መቆየታቸውን አንስተዋል።  ‎ ‎በቀሪ ሦስት ወራት የግድቦችን ደህንነት በማረጋገጥ እና የነበሩ ክፍተቶችን በማረም እንዲሁም አማካይ የኃይል ጭነትን በማሻሻል የታቀደውን ዓመታዊ የኃይል ምርት ግብ ለማሳካት እንደሚሰራ አቶ ያለው አይቀር ተናግረዋል:: ‎ ‎ከመነጨው ኃይል ውስጥ 24 ሺህ 970 ጊጋ ዋት ስዓት ኃይል መሸጡንም ጠቁመዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+8

‎ተቋሙ የበጀት ዓመቱን የ9 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም እየገመገመ ነው ‎.....///..... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የ2018 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም የተቋሙ ዋና ሥራ አሥፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻን ጨምሮ ሁሉም ሥራ መሪዎችና የዋና መ/ቤት ሠራተኞች በተገኙበት በተቋሙ የመሰብሰቢያ አዳራሽ መገምገም ጀምሯል። ‎ ‎የግምገማ መድረኩ ባለፉት ዘጠኝ ወራት የተከናወኑ የኦፕሬሽን፣ የፕሮጀክትና ሌሎች ተቋማዊ ሥራዎች እንዲሁም የተመዘገቡ ስኬቶችን እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን በመለየት ቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ ነው። ‎ ‎በበጀት ዓመቱ ያለፉት ዘጠኝ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጨምሮ የአይሻና የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫዎችን አስመርቆ ወደ ሥራ በማስገባት ትልቅ ታሪክ የተመዘገበበት መሆኑን ተገልጿል። ‎ ‎በተለያየ የግንባታ ሂደት ላይ በሚገኙ የኃይል መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ላይ ቀጣይነት ያለው መሻሻል መመዝገቡንም በመድረኩ ላይ ተብራርቷል። ‎ ‎ተቋሙ አዳዲስ ፕሮጀክቶችን ከመገንባት ባሻገር ነባር የኃይል መሠረተ ልማቶችን በማዘመንና አቅማቸውን በማሳደግ በኩልም ቁልፍ ሥራዎች መከናዎናቸውም ተነግሯል። ‎ ‎በበጀት ዓመቱ ተቋሙ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ከኪሳራ ወጥቶ ትርፍ የተመዘገበ ሲሆን ለዚህ ስኬት የመንግስት ድጋፍ እንደተጠበቀ ሆኖ የተቋሙ ሠራተኞችና አመራሮች የራሳቸው ድርሻ እንደነበራቸው ተገልጿል። ‎ ‎በግምገማ መድረኩ የተቋሙን የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም የኮርፖሬት ፕላኒንግ ተወካይ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ያለውአይቀር ማንደፍሮ እየቀረበ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+4

ከኢትዮጵያ አልፎ ለአፍሪካ ብርሃን የሚፈነጥቀው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ! 🇪🇹⚡️🌍 ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ (GERD) የሀገራችንን የኃይል ፍላጎት ከማሟላት ባለፈ ለምሥራቅ አፍሪካ አ
ከኢትዮጵያ አልፎ ለአፍሪካ ብርሃን የሚፈነጥቀው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ! 🇪🇹⚡️🌍 ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ (GERD) የሀገራችንን የኃይል ፍላጎት ከማሟላት ባለፈ ለምሥራቅ አፍሪካ አዲስ የኢኮኖሚና የኢነርጂ ትስስር ምዕራፍ እየከፈተ ይገኛል። ኢትዮጵያ ያላትን የታዳሽ ኃይል ፀጋ ወደ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ በመለወጥ ቀጣናዊ ውህደትን የምታፋጥንበት ስትራቴጂካዊ መሣሪያም ሆኖ እያገለገለ ነው። የግድቡ ስትራቴጂካዊ ሚና በሦስት ዋና ዋና ዘርፎች ይገለፃል፡፡ 1. የአፍሪካ የኃይል ቋት ማዕከልነት 🔋 ኢትዮጵያ የአፍሪካ የኃይል ቋት ማዕከል በመሆን ለጎረቤት ሀገራት አስተማማኝና በዋጋ ተወዳዳሪ የሆነ ኃይል ታቀርባለች። ይህ ኃይል ለኢትዮጵያም ሆነ ኃይል ከኢትዮጵያ ለሚገዙ ወገኖች ትልቅ ፋይዳ አለው፡፡ • ለኢትዮጵያ፦ ከግድቡ የሚመነጨው ኃይል ሙሉ በሙሉ ቢሸጥ በዓመት እስከ 1 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ይገኛል። ይህም ከቡና ቀጥሎ ትልቁ የውጭ ምንዛሬ ምንጭ የመሆንዕድል እንዳለው ያሳያል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ከኢትዮጵያ-አልፎ-ለአፍሪካ-ብርሃን-የሚፈ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም

ጤናማ አዕምሮ ለተሻለ የሥራ ውጤት! 👷♂️🛡🧠 በየዓመቱ በሚያዝያ ወር የሚታሰበው የዓለም የሥራ ላይ ደህንነትና ጤንነት ቀን ዘንድሮ "ጤናማ የስነ-ልቦናና ማህበራዊ የስራ አካባቢን እናረጋግጥ" በ
ጤናማ አዕምሮ ለተሻለ የሥራ ውጤት! 👷♂️🛡🧠 በየዓመቱ በሚያዝያ ወር የሚታሰበው የዓለም የሥራ ላይ ደህንነትና ጤንነት ቀን ዘንድሮ "ጤናማ የስነ-ልቦናና ማህበራዊ የስራ አካባቢን እናረጋግጥ" በሚል መሪ ቃል ይከበራል። ስለ ሥራ ቦታ ደህንነት ስናስብ መጀመሪያ ወደ አእምሮአችን የሚመጣው የአካል ጉዳትን መከላከል ቢሆንም የዘንድሮው መሪ ቃል ትኩረት ግን ከዚያም ያለፈ ነው። አንድ ሠራተኛ ውጤታማ እንዲሆን ከአካላዊ ደህንነት በተጨማሪ የተረጋጋ ሥነ-ልቦና እና ጤናማ ማህበራዊ ግንኙነት ያለው የሥራ ድባብ ያስፈልገዋል። ለምን ንቁ ተሳትፎ ያስፈልገናል? ✅ ደህንነት የጋራ እሴት ስለሆነ፤ የአደጋ መከላከያ መመሪያዎችን መተግበር የአንድ ክፍል ኃላፊነት ብቻ ሳይሆን የእያንዳንዱ ሠራተኛና አመራር የዕለት ተዕለት ተግባር መሆን አለበት። ✅ የአእምሮ ጤና ለውጤታማነት አጋዥ ስለሆነ፤ ጭንቀትና ጫና የበዛበት የሥራ አካባቢ ለአደጋዎች መከሰት ዋነኛ መንስኤ ነው። የተረጋጋ ሥነ-ልቦና ሲኖር ግን ፈጠራና ጥራት ይጨምራል። ✅ መከላከል ቀዳሚ ትኩረት መሆን ስላለበት፤ የሥራ ላይ አደጋዎችን ቀድሞ በመለየትና ሪፖርት በማድረግ የራሳችንንና የባልደረቦቻችንን ሕይወት መታደግ ይኖርብናል። በመሆኑም በተቋማችን ውስጥ ማንም ሠራተኛ በአካልም ሆነ በሥነ-ልቦና ሳይሰጋ በደስታና በሙሉ አቅሙ የሚሠራበትን አካባቢ ለመፍጠር በጋራ መቆም ይጠበቅብናል። የሥራ ላይ ደህንነት ደንቦችን እናክብር፤ አንዳችን ለሌላችን ደህንነት ዘብ እንቁም! ጤናማ የሥራ አካባቢ ለሁሉም! 🇪🇹⚙️

🇪🇹⚡️ ኢትዮጵያ የኃይል ማማ (Power Hub) የመሆን ጉዞዋን አፋጥናለች! 🇪🇹 🇪🇹🏗⚡️ ሀገራችን ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በኃይል ማመንጨት ዘርፍ አስደናቂ ለውጥ እያስመዘገበች ትገኛለች። አጠቃላይ ሀገራዊ የማመንጨት አቅማችን አሁን ላይ 9,760 ሜጋ ዋት (MW) ደርሷል፤ ይህም ለኢንዱስትሪዎቻችን ዕድገትና ለቀጣናዊ ትስስር ትልቅ ግብዓት እንደሚሆን ይታመናል፡፡ 🇪🇹 የውሃ ኃይል ማመንጫዎቻችን ድርሻ በኃይል ማመንጨት ሂደት ውስጥ የአንበሳውን ድርሻ የሚይዙት የውሃ ኃይል ማመንጫዎቻችን ሲሆን ከሚመነጨው 96% አስተዋጽዖ አላቸው፡፡ 🇪🇹🌊🏗⚡️ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ (GERD)፦ በ 5,150 MW ግዙፍ አቅሙ የኃይል ማመንጫችን በመሆን በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት ውስጥ ከመነጨው የ51% ድርሻ ነበረው፡፡ 🇪🇹🌊🏗⚡️ ጊቤ III (1,870 MW)፣ በለስ (460 MW) እና ሌሎችም የኃይል ማመንጫዎች እንደ ማመንጨት አቅማቸው ለኃይል አቅርቦቱ የራሳቸውን አስተዋጽዖ በማበርከት ላይ ይገኛሉ። 🇪🇹 እያደገ የመጣው የንፋስ እና የሌሎች ታዳሽ ኃይሎች ድርሻ 💧 🌊 የንፋስ ኃይል (~504 MW)፦ በአዳማ፣ በአሸጎዳ፣ በአይሻ እና በአሰላ የሚገኙ የንፋስ ኃይል ማመንጫዎች ኢትዮጵያን በአፍሪካ የንፋስ ኃይል ቀዳሚ እያደረጓት ይገኛሉ። ♻️ ከደረቅ ቆሻሻ ኃይል ማመንጫ ፡- በረጲ የተገነባው ከደረቅ ቆሻሻ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ በአፍሪካ የመጀመሪያው ጣቢያ ሲሆን ከኃይል ማመንጨት በተጓዳኝ የከተማዋን ቆሻሻ በማስወገድ ረገድ አርአያ የሆነ ተግባር እያከናወነ ነው፡፡ ♨️🌋 ጂኦተርማል፦ በአሉቶ ላንጋኖ፡- በቱሉ ሞዬና በኮርቤቲ የሚከናወኑ የከርሰ-ምድር እንፋሎት ፍለጋዎች አዲስ የኃይል አማራጭና ስብጥሩን የሚያሰፉ ዕድሎችን ይዘውልን እየመጡ ነው። 🇪🇹 ቀጣይ ግባችን - የማመንጨት አቅምን 17,000 ሜጋ ዋት ማድረስ! 🏗 የሀገራችንን የኃይል አቅርቦት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ግዙፍ ፕሮጀክቶች በግንባታና በሂደት ላይ ይገኛሉ፡፡ 💧 ኮይሻ (1,800 MW) የውሃ ኃይል ማመንጫ፤ 🌬 አይሻ I እና III የንፋስ ኃይል ፕሮጀክቶች፤ ♨️🌋 ቱሉ ሞዬ እና ኮርቤቲ የግል ባለሀብቶች (IPPs) የሚሳተፉባቸው ግዙፍ የጂኦተርማል ፕሮጀክቶች ተጠቃሾች ናቸው፡፡ 🇪🇹 ኢትዮጵያ የራሷን የኃይል ፍላጎት ከማሟላት ባለፈ ለጎረቤት ሀገራት አስተማማኝ ኃይል በማቅረብ የቀጣናው የኢኮኖሚ ትስስር ማዕከል እየሆነች ነው። ይህ የሁላችንም ኩራትና የብልጽግናችን መሠረት ነው! 🇪🇹🌊🏗⚡️

photo content

🏛 የተቋሙን ሥነ-ምግባርና ግልጽነት ለማጎልበት የላቀ ትኩረት ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ የሥራ መሪዎች "በሥነ-ምግባርዊ የውሳኔ አሰጣጥና በጥቅም ግጭት መከላከል" ዙሪያ የተሰጠው ስልጠና
+4
🏛 የተቋሙን ሥነ-ምግባርና ግልጽነት ለማጎልበት የላቀ ትኩረት ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ የሥራ መሪዎች "በሥነ-ምግባርዊ የውሳኔ አሰጣጥና በጥቅም ግጭት መከላከል" ዙሪያ የተሰጠው ስልጠና ተጠናቋል። ሥልጠናው የተቋሙን የአሰራር ሥርዓት በዘመናዊና ግልጽነት በተሞላበት መንገድ ለመምራት፣ የጥቅም ግጭቶችን ለመከላከል እና ለተቋሙ ተልዕኮ መሳካት ወሳኝ የሆኑ መሠረቶችን ለመጣል ታሳቢ ተደርጎ የተዘጋጀ ነው። የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ እንደገለጹት ስልጠናው አመራሩ በተለያዩ ጉዳዮች የሚሰጣቸውን ውሳኔዎች ሥነ- ምግባር በተላበሰ መልኩ እንዲፈጽም ለማድረግ እና ከጥቅም ግጭት ውስጥ እንዳይገባ ቀድሞ ለመከላከል ከፍተኛ ፋይዳ አለው፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የተቋሙን-ሥነ-ምግባርና-ግልጽነት-ለማጎል&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 15 ቀን 2018 ዓ.ም

በተቋሙ የጥቅም ግጭት ስጋቶችን ለመከላከልና ተጠያቂነትን ለማስፈን በትኩረት ይሰራል …….///……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጥቅም ግጭት ስጋቶችን ለመከላከል እና ተጠያቂነትን ለማስፈን የተለያዩ
+9
በተቋሙ የጥቅም ግጭት ስጋቶችን ለመከላከልና ተጠያቂነትን ለማስፈን በትኩረት ይሰራል …….///……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጥቅም ግጭት ስጋቶችን ለመከላከል እና ተጠያቂነትን ለማስፈን የተለያዩ የአሰራር ስርዓቶችን በመዘርጋት እንደሚሰራ ተገለፀ፡፡ "ሥነ - ምግባራዊ የውሳኔ አሰጣጥና የጥቅም ግጭት መከላከልና ማስተዳደር" በሚል ርዕስ ለተቋሙ ከፍተኛ የሥራ መሪዎች ስልጠና የሰጡት በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የድህረ- ምረቃ ፕሮግራሞች አስተባባሪ አወቀ አሸናፊ (ዶ/ር ) በሥነ ምግባራዊ ውሳኔ አሰጣጥ ሂደቶችና መርሆዎች፣ የጥቅም ግጭት ምንነት፣ አይነቶች፣ መንስኤዎች፣ ተጋላጭነትና ስጋቶች እንዲሁም መከላከያ ስልቶችና ማስተዳደሪያዎች ላይ ገለፃ አድርገዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በተቋሙ-የጥቅም-ግጭት-ስጋቶችን-ለመከላከ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 15 ቀን 2018 ዓ.ም

ሪጅኑ የቴክኒሻኖች የመኖሪያ ቤትን ጨምሮ የማስፋፊያ ሥራዎችን እያከናወነ ነው ........///......... የሰሜን ምስራቅ 1 ሪጅን በሥሩ ለሚገኙ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሠራተኛ መኖሪያ ቤቶ
+5
ሪጅኑ የቴክኒሻኖች የመኖሪያ ቤትን ጨምሮ የማስፋፊያ ሥራዎችን እያከናወነ ነው ........///......... የሰሜን ምስራቅ 1 ሪጅን በሥሩ ለሚገኙ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሠራተኛ መኖሪያ ቤቶችን ጨምሮ ሌሎች መሠረተ ልማቶችን እየገነባ እንደሚገኝ አስታወቀ። የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ በድሩ አህመድ እንደገለፁት የሸዋ ሮቢት እና የኮምቦልቻ 1 ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ያለባቸውን የሠራተኛ መኖሪያ ቤት እጥረት ለመቅረፍ የሚያስችሉ ስምንት አዲስ የመኖሪያ ቤቶች በመገንባት ላይ ናቸው። የቤቶች ግንባታ 70 በመቶ የተከናወነ መሆኑን የገለፁት ዳይሬክተሩ ቤቶቹ በቀጣዮቹ ሁለት ወራት ተጠናቀው አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምሩ ተናግረዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ሪጅኑ-የቴክኒሻኖች-የመኖሪያ-ቤትን-ጨምሮ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም

የተቋሙን ተልዕኮ ለማሳካት የተቋሙ ሠራተኞችና አመራሮች ሙስናን ሊጠየፉ ይገባል ........///........ ተቋሙ እንደ ሀገር የተሰጠውን ተልዕኮ ለማሳካት እና ያለውን ሀብት ውጤታማ በሆነ መንገድ
+9
የተቋሙን ተልዕኮ ለማሳካት የተቋሙ ሠራተኞችና አመራሮች ሙስናን ሊጠየፉ ይገባል ........///........ ተቋሙ እንደ ሀገር የተሰጠውን ተልዕኮ ለማሳካት እና ያለውን ሀብት ውጤታማ በሆነ መንገድ ለመጠቀም የተቋሙ ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች ሙስናን ሊጠየፉ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አሳሰቡ። "ሥነ-ምግባራዊ ውሳኔ አሰጣጥና የጥቅም ግጭትን መከላከል እና ማስተዳደር" በሚል ርዕሰ ጉዳይ ለተቋሙ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል። በሥልጠናው መክፈቻ ላይ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጅነር አሸብር ባልቻ  እንደተናገሩትት ተቋሙ በርካታ ሀብት የሚያንቀሳቅስ እና የሥራ ፀባዩ ሙስና በረቀቀ መንገድ ሊፈፀምበት የሚችል በመሆኑ ሁሉም ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርበታል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የተቋሙን-ተልዕኮ-ለማሳካት-የተቋሙ-ሠራተ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም

የኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ጉዞ! ET 🌿 ኢትዮጵያ እንደ ሀገር የጀመረችው ወደ ታዳሽ የኃይል ምንጮች የመሸጋገር ጉዞ የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የሉዓላዊነትና የኢኮኖሚ ነፃነት ምልክትም ነው። ይህ ጉዞ ለሀገራችን ምን ጥቅም ይሰጣል? በዓለምአቀፍ መድረክስ ምን ዓይነት ቦታ ላይ ያስቀምጠናል? 1. በሀገር ውስጥ የሚኖረው ዘርፈ-ብዙ ጥቅም 🏗 • የኢንዱስትሪ መነቃቃት አስተማማኝና በአንፃራዊነት በዋጋው ርካሽ የሆነ ታዳሽ ኃይል (ከውሃ፣ ንፋስ፣ ፀሐይና የከርሰ ምድር እንፋሎት ኃይል በመጠቀም ) ለፋብሪካዎችና ለኢንዱስትሪ ፓርኮች መስፋፋት አንቀሳቃሽ ሞተር በመሆን ከፍተኛ የኢኮኖሚ መነቃቃት ይፈጥራል። • አረንጓዴ ኢኮኖሚ የአካባቢ ብክለትን በመቀነስና በከሰልና በነዳጅ ላይ ያለንን ጥገኝነት በማስቀረት የከባቢ አየርን ብክለት በመቀነስና የውጭ ምንዛሪ ወጪን በመታደግ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመፍጠር የተጀመረውን ሀገራዊ ጥረት ያግዛል። • የኤሌክትሪክ ተደራሽነት ኤሌክትሪክ ያልተዳረሰባቸውን የሀገራችን ክፍሎች ብርሃን በመስጠት የዜጎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ኑሮ እንዲለወጥ ምክንያት ይሆናል። 2. በዓለምአቀፍ መድረክ የሚኖረው ፋይዳ 🌍 • የኢትዮጵያን የአረንጓዴ ዲፕሎማሲ የመሪነት ሚና ያሳድጋል፤ ዓለም በካርቦን ልቀት ስጋት ውስጥ ባለችበት ወቅት ኢትዮጵያ በታዳሽ ኃይል ላይ የምታደርገው ኢንቨስትመንት ለቀጣናውም ሆነ ለዓለም አርአያ እንድትሆን ያደርጋታል። • ትስስርና ቀጣናዊ ተጽዕኖ ይፈጥራል፤ ኢትዮጵያ ለጎረቤት ሀገራት ኃይል በመሸጥ የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ማዕከል (Energy Hub) መሆኗ በፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ መድረኮች ያላትን የመደራደር አቅምና ተሰሚነት ይጨምራል። • ኢንቨስትመንትን ለመሳብ አቅም ይሆናል፤ አረንጓዴ ኃይል የሚጠቀሙ ሀገራት ለዓለምአቀፍ ፋይናንስና ለታላላቅ ኩባንያዎች ተመራጭ መዳረሻ እየሆኑ በመምጣታቸው ለሀገራችን ትልቅ ዕድል ይከፍትላታል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በተፈጥሮ የታደለችውን ጸጋ ወደ ታላቅ ኃይል በመቀየር አፍሪካዊ የብልጽግና ተምሳሌትነቷን እያረጋገጠች ትቀጥላለች!

photo content

ኢትዮጵያ የኮፕ 32 ጉባኤን እንድታስተናግድ መመረጧ በአረንጓዴ ልማት የመሪነት ሚናዋን በአግባቡ እየተወጣች መሆኗን ያሳያል ........///....... ኢትዮጵያ በታዳሽ ኃይል እና በአረንጓዴ አሻራ
+6
ኢትዮጵያ የኮፕ 32 ጉባኤን እንድታስተናግድ መመረጧ በአረንጓዴ ልማት የመሪነት ሚናዋን በአግባቡ እየተወጣች መሆኗን ያሳያል ........///....... ኢትዮጵያ በታዳሽ ኃይል እና በአረንጓዴ አሻራ እያከናወነቻቸው ያሉ ሥራዎች ዓለም አቀፍ እውቅና እያስገኘላት መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ዳይሬክተር ሞገስ መኮንን ገለፁ። ዳይሬክተሩ "ኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ማማ" በሚል ርዕሰ ጉዳይ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በዳጉ የቀጥታ ስርጭት ፕሮግራም ላይ እንደገለጹት ኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራን ጨምሮ የታዳሽ ኃይል ልማትን ለማስፋፋት የሚያስችሉ በርካታ መሰረቶች አስቀምጣ እየሰራች ትገኛለች፡፡ በታዳሽ ኃይል እና በአካባቢ ጥበቃ ላይ እያከናወነቻቸው ያሉ ሥራዎች ዓለም አቀፉን የአየር ንብረት ጉባኤ (ኮፕ 32) እንድታዘጋጅ ዓለም አቀፍ እውቅና እንዳስገኘላት አስታውቀዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ኢትዮጵያ-የኮፕ-32-ጉባኤን-እንድታስተናግድ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 13 ቀን 2018 ዓ.ም

ተቋሙ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ግንባታና ማሻሻያ ሥራዎች ስምምነት ተፈራረመ ....///..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኬኢሲ ኢንተርናሽናል ከተባለ የህንድ ኩባንያ ጋር የኢትዮጵያ የኃይል
+7
ተቋሙ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ግንባታና ማሻሻያ ሥራዎች ስምምነት ተፈራረመ   ....///..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኬኢሲ ኢንተርናሽናል ከተባለ የህንድ ኩባንያ ጋር የኢትዮጵያ የኃይል ዘርፍ ሪፎርም፣ ኢንቨስትመንት እና ዘመናዊነት (PRIME) ፕሮጀክት ስር የሚከናወኑ የማስተላለፊያ መስመሮች ግንባታና ማሻሻያ ሥራዎችን ለማከናወን የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ፡፡ ስምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እና በአፍሪካ የኬኢሲ ኢንተርናሽናል ኩባንያ ምክትል ፕሬዚዳንት ሚስተር ሱከሺ ቪያሊ  ተፈራርመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በፊርማ ሥነ ስርዓቱ ላይ እንደገለጹት ፕሮጀክቱ በኢትዮጵያ ያለውን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ጥራት ለማሻሻል፣ የኃይል መቆራረጥን ለመቀነስ እና ተደራሽነትን ለማስፋት ፋይዳው የጎላ ነው። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-የኃይል-ማስተላለፊያ-መስመሮች-ግን&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 12 ቀን 2018 ዓ.ም

ኢትዮጵያ የውሃ ማማ ናት የሚለው ትርክት የተፈጥሮ ሀብቷን እንዳትጠቀም የተገነባ ትርክት ነው ......///....... ኢትዮጵያ የአፍሪካ የውሃ ማማ ናት የሚለው ትርክት የተፈጥሮ ሀብቷን እንዳትጠቀም በሚፈለግ መንገድ በዐባይ የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት የተገነባ ትርክት መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር ገለፁ፡፡ ዳይሬክተሩ አቶ ሞገስ መኮንን "ኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ማማ" በሚል ርዕሰ ጉዳይ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በዳጉ የቀጥታ ስርጭት ፕሮግራም ላይ በተደረገ ውይይት እንዳስታወቁት ኢትዮጵያ ለኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫነት የሚውል እምቅ የታዳሽ ሀብት አላት፡፡ የተፈጥሮ ሀብቶቿ በሚፈለገው መልኩ በአግባቡ ጥቅም ላይ እየዋሉ ባይሆንም አሁን ላይ ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይሏን ከታዳሽ የኃይል ምንጮች ማድረጓና በርካታ ጥቅሞችን እያገኘች መሆኑን ገልፀዋል፡፡ የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት በየዓመቱ በአማካኝ የ10 በመቶ እድገት እንዳለው የጠቆሙት ዳይሬክተሩ ከኢንዱስትሪና ከከተሞች መስፋፋት እንዲሁም ከመንግስት ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር ተያይዞ እያደገ የሚሄደውን የኃይል ፍላጎት ለመሟላት ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ እንደሆነም አስረድተዋል፡፡ ተቋሙ "የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል" የመሆን ርዕዩን ለማሳካት በታዳሽ የኃይል ምንጮች ላይ በርካታ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራን ጨምሮ የታዳሽ ኃይል ልማትን ለማስፋፋት የሚያስችሉ በርካታ መሰረቶችን አስቀምጣ እየሰራች እንደሆነ የተናገሩት አቶ ሞገስ በታዳሽ ኃይል ዘርፍ እና በአካባቢ ጥበቃ  ላይ እያበረከተችው ያለው አስተዋጽኦ እና የመሪነት ሚና ዓለም አቀፉ የአየር ንብረት ጉባዔ ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጣ ከፍተኛ ሚና መጫወቱንም ጠቅሰዋል፡፡ የኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ልማት ቀጣናዊ ትስስርን በማጠናከር የአፍሪካ ሀገራትን በመሰረተ ልማት ማስተሳሰር የሚለውን የአፍሪካ ሕብረት የነደፈውን አጀንዳ 2063 ለማሳካት ጉልህ ሚና መወጣቷን እና የኢትዮጵያን የውጭ ግንኙነት ፖሊስ ወደ ተግባር መቀየሩን ከማሳየቱም ባለፈ የውሃ ዲፕሎማሲን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ ዕድል እንዳለው አስረድተዋል፡፡ ኢትዮጵያ የውሃ ማማ ናት የሚለው ትርክት ላለፉት በርካታ አስርት ዓመታት በዐባይ የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ሲቀነቀን የኖረና ሀገሪቱ ያላትን ሀብት በትክክል ከመግለጽ ይልቅ ሀብቶቿን እንዳትጠቀም በሚፈለግ መንገድ የተገነባ መሆኑን አንስተዋል፡፡ ትርክቱ ኢትዮጵያ የተለያዩ ተፋሰሶች ስላሏት የዐባይ ተፋሰስን እንዳትጠቀም በመፈልግ የተቀነቀነና በተለያዩ ጊዜያት በተፈረሙ የቅኝ ግዛት ውሎች ላይ ቆመው ኢትዮጵያን በዐባይ ተፋሰስ ላይ የልማት ሥራዎች እንዳታከናወን የሚከለክል ትርክት እንደሆነም አስታውሰዋል፡፡ ኢትዮጵያ የአፍሪካ የውሃ ማማ እንደሆነች የሚገለጸውን ትርክት ለመቀየር ለኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫነት የሚውሉ ተፋሶችን በአግባቡ መጠቀም እና የተለያዩ የታዳሽ ኃይል ምንጮችን ጥቅም ላይ በማዋል የኃይል ስብጥሩን ማስፋት እንዲሁም ኢትዮጵያን የውሃ ማማ ሳይሆን የታዳሽ ኃይል ማማ መሆኗን ማስተዋወቅ እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል፡፡ በዚህም የኢትዮጵያን የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማማነት ለማረጋገጥ የትርክት ዳግም ግንባታ ሥራውን ከሀገሪቱ ሀብት፣ ጥቅምና ፍላጎት ጋር በማያያዝ ለኃይል ማመንጫነት በሚውሉ አቅሞች አጠቃቀም ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ ሊንክ፡ ኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ማማ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 12 ቀን 2018 ዓ.ም