uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 692 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 014-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 155-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 692 obunachiga ega bo‘ldi.

30 Avgust, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 145 ga, so‘nggi 24 soatda esa 2 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 31.28% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 16.96% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 4 909 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 661 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 10 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
EEP Communication

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 31 Avgust, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 692
Obunachilar
+224 soatlar
+187 kunlar
+14530 kunlar
Postlar arxiv
photo content
+3

መኾኒ ከተማ በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ   ከ500 በላይ የታወር ብረቶች ተያዙ …///… በሰሜን ሪጅን ከአላማጣ – መኾኒ – መቐለ አቅጣጫ በተዘረጋው የ230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት መምሰሶዎች ላይ ተሰርቀው የተደበቁ ከ500 በላይ ብረቶች መያዙን የሰሜን ሪጅን ፊዚካል ሴኩሪቲ አስታወቀ፡፡  በሪጅኑ የመሰረተ ልማት ደህንነት ፊዚካል ሴኩሪቲ አባል ኮሎኔል ማዕረግ አሰፋ እንዳስታወቁት በሪጅኑ ከአላማጣ – መኾኒ – መቐለ አቅጣጫ በተዘረጋው የ230 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር በሚያጋጥመው ተደጋጋሚ ስርቆት ከፍተኛ ውድመት የሚደርስበት አካባቢ ነው፡፡ በተለይም በትግራይ ክልል ደቡባዊ ዞን፣ ራያ ዓዘቦ ወረዳ፣ መኾኒ ከተማና አካባቢው ከፍተኛ ትኩረት የሚሻ በመሆኑ ከመደበኛ የጥገና ሥራዎች ጎን ለጎን የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማት ደህንነትን ለማስጠበቅ ዘርፈ ብዙ ሥራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡ የአካባቢውን ማህበረሰብ በማወያየት የቅድመ መከላከል ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የጠቀሱት ኮሌኔሉ በሥጋት ቀጠናዎች ላይ ክትትል እና ድንገተኛ ፍተሻ በማድረግ  ተጠርጣሪዎችን በህግ ቁጥጥር ሥር እያዋሉ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ እንደ ኮሌኔሉ ገለጻ በመኾኒ ከተማ በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ ለጊዜው ግምታዊ ዋጋቸው ያልታወቀ ከ500 በላይ የታወር ብረቶች የተያዙ ሲሆን በጉዳዩ ላይ አንድ ባጃጅ እና አምስት ተጠርጣሪ ግለሰቦች በሕግ ቁጥጥር ሥር ውለው ክስ ተመስርቶባቸዋል። በሪጅኑ የሚገኙ የተቋሙን መሰረተ ልማቶች ደህንነት የመጠበቅ ሥራ ከሪጅኑ አመራርና ሠራተኛ እንዲሁም ከአካባቢው የመስተዳደር አካላትና ከመላው ማህበረሰብ ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 20  ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+3

🌍 Today is World Clean Energy Day! (January 26) Did you know that Ethiopia is one of the greenest countries in the world whe
🌍 Today is World Clean Energy Day! (January 26) Did you know that Ethiopia is one of the greenest countries in the world when it comes to energy? 🇪🇹 Here are 4 reasons why today matters: 1️⃣ Climate Protection: Renewable energy is helping us fight the 1.5°C global warming limit. 2️⃣ Affordability: Solar energy is now the cheapest source of electricity in history! 3️⃣ National Success: 98% of our electricity comes from clean sources like the sun, wind, and water. 4️⃣ Regional Leadership: With a capacity of over 9,700 MW, Ethiopia is becoming the clean energy hub for all of East Africa. Let’s celebrate a cleaner, brighter future for our children. Happy World Clean Energy Day! #CleanEnergy #Ethiopia #GreenEnergy #WorldCleanEnergyDay #Sustainability

🌍 የዓለም የንፁህ ኢነርጂ ቀን (ጥር 18) የንፁህ ኢነርጂ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ በየዓመቱ ጥር 18 ወይም እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ጃንዋሪ 26 ቀን ይከበራል። ዋነኛ ዓላማው፦ ✅ አካባቢን የማይበክሉ የንፁህ ኢነርጂ ምንጮችን (ፀሃይ፣ ንፋስ፣ ሃይድሮ፣ ጂኦተርማል፣ ባዮማስ) ማስተዋወቅ እና ጥቅም ላይ ማዋል ✅ የነዳጅ ጥገኛነት መቀነስ ✅ ርካሽ ኢነርጂን ለተጠቃሚው ማቅረብ ✅ የማህበረሰብ ግንዛቤ ማሳደግ የኢነርጂ ዘርፍ በየጊዜው በርካታ ታሪካዊ ስኬቶችን አስመዝግቧል። 1. የአቅም እድገት 💡 30%፦ በዓለም አቀፍ የኤሌክትሪክ ምርት ውስጥ የታዳሽ ኃይል ግምታዊ ድርሻ። o በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በበርካታ ታላላቅ ኢኮኖሚዎች ውስጥ የንፋስ እና የፀሐይ ኃይል ከድንጋይ ከሰል (Coal) የተሻለ ውጤት እያስመዘገቡ ነው። 💡 510 ጊጋ ዋት (GW)፦ ባለፈው ዓመት ብቻ በዓለም አቀፍ ደረጃ የተጨመረው የታዳሽ ኃይል መጠን ሲሆን፣ ይህም ካለፉት ዓመታት የ50% እድገት አሳይቷል። 💡 $1.8 ትሪሊዮን ዶላር፦ ባለፈው ዓመት ለንፁህ ኢነርጂ ቴክኖሎጂዎች (የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች፣ ለኃይል ማመንጫዎች እና ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ግንባታ) ኢንቨስት የተደረገው ግምታዊ ዓለም አቀፍ በጀት ነው። ይህም ለነዳጅ እና ጋዝ ከሚወጣው መዋዕለ ንዋይ በእጅጉ ይበልጣል። 2. የፀሐይ እና የንፋስ ኃይል የበላይነት 🎯 ከ$0.02 – $0.05 ዶላር በኪሎዋት ሰዓት (kWh)፦ በትላልቅ የፀሐይ ኃይል ማመንጫዎች የሚመረት የኤሌክትሪክ አማካኝ ዋጋ ሲሆን ይህም በታሪክ ውስጥ በብዙ የዓለም ክፍሎች የፀሐይ ኃይልን ርካሹ የኤሌክትሪክ ምንጭ አድርጎታል። 🎯 1 ቴራዋት (TW)፦ በዓለም አቀፍ ደረጃ የተተከለው የፀሐይ ኃይል አቅም ነው፤ ይህም ታሪካዊ ዕድገት ተብሎ ተመዝግቧል። 🎯 11%፦ በአሁኑ ወቅት ከንፋስ ኃይል የሚገኘው የዓለም አቀፍ የኤሌክትሪክ ድርሻ ሲሆን በተለይም በባህር ላይ የሚገነቡ የንፋስ ኃይል ማመንጫዎች ፈጣን እድገት እያሳዩ ነው። 3. የአፍሪካ ሁኔታ (በተለይ የኢትዮጵያ ሁኔታ) 🇪🇹 98%፦ በዜና ዘገባዎች እንደተጠቀሰው፣ ይህ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ከታዳሽ ምንጮች (በዋነኝነት ከውሃ፣ ከንፋስ እና ከጂኦተርማል) የሚመረትበት መቶኛ ነው። 📊 600 ሚሊዮን፦ ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት የኤሌክትሪክ አገልግሎት የማያገኙ ሰዎች ቁጥር ነው። ይህም እንደ IRENA እና COP32 ያሉ ጉባኤዎች ችግሩን ለመፍታት መስራት ያለባቸው ን ሰፊ የ"ንፁህ ኢነርጂ ክፍተት" እንዳለ ያሳያል። 📊 5,150 ሜጋዋት (MW)፦ የምስራቅ አፍሪካ የንፁህ ኢነርጂ የጀርባ አጥንት የሆነው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ (GERD) የኃይል ማመንጨት አቅም ነው። ኢትዮጵያ እንደሀገር ከ9 ሺህ 7 መቶ ሜጋ ዋት በላይ የማመንጨት አቅም ፈጥራለች፡፡ 4. የአካባቢ ተፅዕኖ 🌱 1.50C፦ ዓለም የሙቀት መጠኗ ከዚህ እንዳያልፍ እየታገለች ያለችበት ገደብ ነው። ይህንን ለማሳካት የታዳሽ ኃይል አቅም እስከ 2030 ድረስ በሶስት እጥፍ ማደግ ይኖርበታል። 🌱 12 ጊጋ ቶን፦ በአሁኑ የታዳሽ ኃይል አጠቃቀም እና የኢነርጂ ብክነትን በመቀነስ እርምጃዎች አማካኝነት በየዓመቱ ወደ ከባቢ አየር እንዳይለቀቅ የተደረገ የCO2 መጠን ነው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 18 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

የክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ የሥራ መደብ መረጃ የሥራ መደብ መጠሪያ፦ ቧንቧ ጥገና ሰራተኛ (Plumber Technician) የሥራ ደረጃ፦ ጂኤስ4 ደመወዝ፦ በድርጅቱ ስኬል መሰረት ብዛት፦ እንደ አስ
የክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ የሥራ መደብ መረጃ የሥራ መደብ መጠሪያ፦ ቧንቧ ጥገና ሰራተኛ (Plumber Technician) የሥራ ደረጃ፦ ጂኤስ4 ደመወዝ፦ በድርጅቱ ስኬል መሰረት ብዛት፦ እንደ አስፈላጊነቱ የሥራ ቦታ፦ ዋናው መ/ቤት የቅጥር ሁኔታ፦ በቋሚነት የመመዝገቢያ ቀን፦ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 (አስር) ተከታታይ የሥራ ቀናት ብቻ ይሆናል ። የምዝገባ ቦታ፦ ኮተቤ ብረታብረት በሚገኘው በድርጅቱ ዋና መ/ቤት የሰው ኃይል ቅጥርና ምደባ ቢሮ በአካል በመገኘት መመዝገብ ይቻላል ። ለተጨማሪ መረጃ ከላይ የተያያዘዉን ፎቶ ይመልከቱ! 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 16 ቀን 2018 ዓ.ም

መምሪያው የተቋሙን የአሠራር ስርዓት ለማዘመን እየሰራ መሆኑን ገለፀ …….///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፕሮሰስ፣ ፖሊሲና የለውጥ ሥራ አመራር መምሪያ ቀልጣፍ እና ውጤትን መሠረት ያደረገ
+3
መምሪያው የተቋሙን የአሠራር ስርዓት ለማዘመን እየሰራ መሆኑን ገለፀ …….///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፕሮሰስ፣ ፖሊሲና የለውጥ ሥራ አመራር መምሪያ ቀልጣፍ እና ውጤትን መሠረት ያደረገ የአሠራር ስርዓት ለመዘርጋት የሚያስችሉ ተግባራት እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ አንዷለም ኪዳኔ እንደተናገሩት የአሰራርና የዶክመንቴሽን ስርዓቶችን በማዕከል ለማደራጀት፣ ደህንነታችውን ለመጠበቅና ለተጠቃሚዎች ምቹ ለማድረግ የሚያስችል ሲስተም የማበልጸግ ስራ ተከናውኗል። የተቋሙን የመፈፀም አቅም የሚያጎለብቱ የፖሊሲ ዝግጅት፣ መመሪያ፥ ማጣቀሻ ሰነዶች እና ቴምፕሌቶች ተዘጋጅተው ወደ ስራ መገባቱን ዳይሬክተሩ አብራርተዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=መምሪያው-የተቋሙን-የአሠራር-ስርዓት-ለማ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 15 ቀን 2018 ዓ.ም

ዘርፉ የተጀመሩ የቅንጅት ሥራዎች ይበልጥ መጠናከር አለባቸው ……///……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መልካም አስተዳደርን በዘላቂነት ለማስፈን በኮርፖሬት ገቨርናንሰ እና ኮምፕሊያንስ ዘርፍ ሥር የሚ
+9
ዘርፉ የተጀመሩ የቅንጅት ሥራዎች ይበልጥ መጠናከር አለባቸው ……///……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መልካም አስተዳደርን በዘላቂነት ለማስፈን በኮርፖሬት ገቨርናንሰ እና ኮምፕሊያንስ ዘርፍ ሥር የሚገኙ መምሪያዎች በቅንጅት መስራት እንደሚጠበቅባቸው የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ አሳሰቡ፡፡ በዘርፉ ሥር የሚገኙት የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን፤ የህግ አገልግሎት፤ የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ እንዲሁም የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያዎች በ2018 በጀት ዓመት ባለፉት ስድስት ወራት ያከናወኗቸውን ሥራዎች አቅርበው ተገምግሟል፡፡ የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ በተቋሙ የሚገኙ ሴት ሠራተኞች መብትና ጥቅም ለማስከበር እና ማህበራዊ ችግሮቻቸውን ለመፍታት መንቀሳቀሱን ሲገልጽ የህግ አገልግሎት መምሪያ በበኩሉ የተቋሙን ጥቅም የሚያስጠብቁ የፍትሐብሔር፣ የሥራ ክርክር እና  የካሳ ጉዳዮችን በመከታተል የመርታት አቅሙን ማሳደጉን ገልጿል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ዘርፉ-የተጀመሩ-የቅንጅት-ሥራዎች-ይበልጥ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 14 ቀን 2018 ዓ.ም

‎ዘርፉ የስድስት ወራት ዕቅድ አፈጻጸም እየገመገመ ነው             ‎.....///..... ‎በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ገቨርናንስ እና ኮምፕሊያንስ ሥራ አስፈፃሚ ዘርፍ  የ2018 በጀት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምን መገምገም ጀምሯል። ‎ የዘርፉ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዱጉማ ነዳ ‎በግምገማው መክፈቻ ላይ እንደገለጹት እንደ ተቋም የተያዙ ስትራቴጂያዊ ዕቅዶችን ለማሳካት የዘርፉን አበርክቶ መገምገም አስፈላጊ ነው። ስለሆነም በዘርፉ ስር ያሉ ሁሉም መምሪያዎች በስድስት ወራት ውስጥ ያከናወኗቸውን ዋና ዋና ሥራዎችን በዝርዝር በማቅረብ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማስቀጠልና የታዩ ክፍተቶችን ለማረም ግምገማው ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። በበጀት ዓመቱ በመጀመሪያው ግማሽ ዓመት በዘርፉ የተከናወኑ የዕቅድ አፈጻጸሞች በግምገማው የሚቀርቡ ሲሆን የተመዘገቡ ጠንካራ ጎኖችና የታዩ ክፍተቶችን በመገምገም እንዲሁም የቀጣይ ሥራዎችን አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ግምገማው ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 14 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+5

ተቋሙ የመሰረተ ልማት ሥርቆትን ለመከላከል የዘረጋው ስትራቴጂ ውጤት እያመጣ ነው ..….///….… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ የሚፈ
+2
ተቋሙ የመሰረተ ልማት ሥርቆትን ለመከላከል የዘረጋው ስትራቴጂ ውጤት እያመጣ ነው ..….///….… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ የሚፈፀሙ የስርቆት ወንጀሎችን ለመከላከል የተዘረጋው ስትራቴጂ ውጤት እያመጣ መሆኑን በተቋሙ የኃይል መሰረተ ልማት ደህንነት፣ ክትትልና ቁጥጥር መምሪያ ገለፀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ከሊል ሽፋ እንደገለፁት ባለፉት ስድስት ወራት በመሰረተ ልማቶቹ ላይ ይፈፀም የነበረው ስርቆት ካለፉት ዓመታት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የመቀነስ አዝማሚያ ታይቷል፡፡ በ12 ሪጅኖች የቀድሞ የመከላከያ መኮንኖችን በመመደብ የኃይል መሰረተ ልማት ደህንነትን ለማሻሻል የሚያስችሉ ሥራዎች በመከናወን ላይ መሆኑን ነው የተናገሩት፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-የመሰረተ-ልማት-ሥርቆትን-ለመከላከ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 13 ቀን 2018 ዓ.ም

ባለፉት ስድስት ወራት ለ139 ጉዳዮች ምላሽ ተሰጥቷል ……///….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2018 በጀት ዓመት ስድስት ወራት ከውጭ ተገልጋዮች እና ከተቋሙ አመራርና ሠራተኞች ለቀረቡ 139 አ
+4
ባለፉት ስድስት ወራት ለ139 ጉዳዮች ምላሽ ተሰጥቷል ……///….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2018 በጀት ዓመት ስድስት ወራት ከውጭ ተገልጋዮች እና ከተቋሙ አመራርና ሠራተኞች ለቀረቡ 139 አስተዳደራዊ ጥያቄዎች ምላሽ መሰጠቱን የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡ የጽ/ቤት ኃላፊው አቶ ሙላት ገዛኸኝ እንደገለፁት ባለፉት ስድስት ወራት ለ 152 አስተዳደራዊ ጉዳዮች ምላሽ ይሰጣል በሚል የታቀደ ቢሆንም ለቀረቡት 139 አስተዳደራዊ ጥያቄዎች ሙሉ በሙሉ ምላሽ ተሰጥቷል፡፡ ከዋና ስራ አስፈጻሚ በተሰጠ ውክልና መሠረት የተቋሙ ባለሙያዎች ለሚያከናውኗቸው ሙያዊ ተልዕኮዎች ድጋፍ ከመስጠት አንፃር ለ107 ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች የፓስፖርት እድሳትና አዲስ ፓስፖርት እንዲያገኙ መደረጉን አስታውቀዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ባለፉት-ስድስት-ወራት-ለ139-ጉዳዮች-ምላሽ-ተሰ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 13 ቀን 2018 ዓ.ም

የኃይል አቅርቦት ኢንዱስትሪዎችን በመደገፍ ረገድ ሚናው የጎላ ነው ……///……. የኃይል አቅርቦት በኮምቦልቻ ከተማ በተኪና ወደውጭ የሚላኩ ምርቶችን በማምረት ላይ ለተሰማሩ እንዲሁም ለፌደራል ለመንግ
+6
የኃይል አቅርቦት ኢንዱስትሪዎችን በመደገፍ ረገድ ሚናው የጎላ ነው ……///……. የኃይል አቅርቦት በኮምቦልቻ ከተማ በተኪና ወደውጭ የሚላኩ ምርቶችን በማምረት ላይ ለተሰማሩ እንዲሁም ለፌደራል ለመንግስት ታክስ በመክፈል በሀገር ኢኮኖሚ ላይ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ያሉ ኢንዱስትሪዎችን በመደገፍ በኩል ሚናው የጎላ እንደሆነ የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ፡፡ የአስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አቶ ወንድወሰን ልሳነወርቅ እንዳስታወቁት በኮምቦልቻ ከተማ 127 ከፍተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች እንዲሁም በሺዎች የሚቆጠሩ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ይገኛሉ፡፡ ከማህበረሰቡና ከመንግስታዊ ተቋማት በተጨማሪ በከተማዋ የሚገኙት የአገልግሎት ሰጭ ተቋማት፣ የአምራችና የማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎች እንዲሁም የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ከፍተኛ የሆነ የኃይል ፍላጎት እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-አቅርቦት-ኢንዱስትሪዎችን-በመደ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 8 ቀን 2018 ዓ.ም

የኃይል አቅርቦት አስተማማኝነት የሚያሳድጉ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው …….///…… በኮምቦልቻ ቁጥር 2 ማከፋፈያ ጣቢያ በየጊዜው እያደገ የሚመጠውን የኃይል ፍላጎት ጥያቄ ለመመለስ የሚያስችሉ ሥራዎች
+7
የኃይል አቅርቦት አስተማማኝነት የሚያሳድጉ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው …….///…… በኮምቦልቻ ቁጥር 2 ማከፋፈያ ጣቢያ በየጊዜው እያደገ የሚመጠውን የኃይል ፍላጎት ጥያቄ ለመመለስ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን የጣቢያው ኃላፊ አስታውቀዋል፡፡ ኃላፊው አቶ ዝናቡ ገብሩ እንዳስታወቁት የህዝብ ቁጥር መጨመር፣ የኢንዱስትሪ እና ከተሞች መስፋፋትን ተከትሎ በማከፋፈያ ጣቢያው ላይ ያለው የኃይል አቅርቦት ፍላጎት በፍጥነት እያደገ ይገኛል፡፡ ማከፋፈያ ጣቢያው በ2002 ዓ.ም አገልግሎት መስጠት ሲጀምር 63 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያለው አንድ ትራንስፎርመር እና አራት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች ብቻ እንደነበሩት ያስታወሱት አቶ ዝናቡ በየጊዜው እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት መሰረት በማድረግ በተለያዩ ጊዜያት የአቅም ማሳደግ፣ ማስፋፊያና ማዘመን ሥራዎች እንደተከናወኑለት ተናግረዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-አቅርቦት-አስተማማኝነት-የሚያሳ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 9 ቀን 2018 ዓ.ም

ሪጅኑ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች ማከናወኑን ገለፀ ……..///……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምዕራብ ሪጅን ባለፉት ስድስት ወራት አስተማማኝ የኃይል አቅርቦ
+7
ሪጅኑ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች ማከናወኑን ገለፀ ……..///……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምዕራብ ሪጅን ባለፉት ስድስት ወራት አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች ማከናወኑን አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ተሻገር እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች እና ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ በዕቅድ ላይ የተመሰረቱ የአስቸኳይ ጥገና እና የፍተሻ ሥራዎች ተሰርተዋል። በግማሽ በጀት ዓመቱ የኤሌክትሪክ አቅርቦትን ለማረጋጋት እና ተደራሽነትን ለማስፋፋት የሚያስችሉ የጥገና እና የማሻሻያ ሥራዎች መከናወናቸውን ገልፀው ይህም የኃይል መቆራረጥን ለመቀነስ እና የኢንዱስትሪዎችን ፍላጎት ለማሟላት ያለመ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ https://www.eep.com.et/?amh-news=ሪጅኑ-አስተማማኝ-የኃይል-አቅርቦትን-ለማ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 9 ቀን 2018 ዓ.ም

ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ .....///...... የሥራ መደብ፡ የኤሌክትሪክ መኪና ቻርጅ አድራጊ ቴክኒሻን I (Technician I EV Battery Charger) የትምህርት ደረጃ፡ ኮሌጅ ዲፕሎማ
ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ .....///...... የሥራ መደብ፡ የኤሌክትሪክ መኪና ቻርጅ አድራጊ ቴክኒሻን I (Technician I EV Battery Charger) የትምህርት ደረጃ፡ ኮሌጅ ዲፕሎማ/TVET 10+3 ወይም በደረጃ 4 በአውቶሞቲቭ ኤሌክትሪካል/ኤሌክትሮኒክስ ወይም አውቶሞቲቭ ኤሌክትሮ ሜካኒካል የተመረቀ። ልዩ መስፈርት፡ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ (COC) ማቅረብ የሚችል። የሥራ ልምድ፡ አይጠይቅም (0 ዓመት)። የምዝገባ ቦታ፡ ኮተቤ ብረታ ብረት ፋብሪካ በሚገኘው የድርጅቱ ዋና መሥሪያ ቤት፣ የሰው ኃይል ቅጥርና ምደባ ቢሮ (በአካል በመገኘት) ለበለጠ መረጃ በድረ ገጻችን https://www.eep.com.et/?amh-announcement=ክፍት-የሥራ-ቦታ-ማስታወቂያ መመልከት ትችላላችሁ። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 8 ቀን 2018 ዓ.ም

የአይሻ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን የፋይናንስ ሥምምነት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው …..///….. በመንግሥት እና የግል አጋርነት ማዕቀፍ ለሚገነባውና 300 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ላለው
+6
የአይሻ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን የፋይናንስ ሥምምነት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው …..///….. በመንግሥት እና የግል አጋርነት ማዕቀፍ ለሚገነባውና 300 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ላለው የአይሻ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የፋይናንስ ሥምምነት ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ፡፡ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ ከገንዘብ ሚኒስቴር እና ከዋና ዋና የልማት አጋሮች ጋር በመተባበር የከፍተኛ ደረጃ የአበዳሪዎች የቅድመ ኢንቨስትመንት ምርመራ ስብሰባ በሸራተን አዲስ ሆቴል ተካሂዷል፡፡ በስብሰባው ላይ የተገኙት የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ የማክሮ ኢኮኖሚ እና የውጭ ምንዛሪ ማሻሻያዎችን በማድረግ እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት መንግሥት በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የአይሻ-1-የንፋስ-ኃይል-ማመንጫ-ፕሮጀክትን&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 8 ቀን 2018 ዓ.ም

@9:00

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ ትርፍ አገኘ .....///…... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ቀደም ሲል የነበረበትን ከፍተኛ የዕዳ ጫና በመቋቋም እና አሠራሩን በማዘመን ለመጀመሪ
+1
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ ትርፍ አገኘ .....///…... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ቀደም ሲል የነበረበትን ከፍተኛ የዕዳ ጫና በመቋቋም እና አሠራሩን በማዘመን ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ትርፋማነት መሸጋገሩን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ አስታወቀ። የኢንቨስትመንት ሆልዲንጉ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ብሩክ ታዬ ( ዶ/ር) እንደገለፁት ተቋሙ በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት ከ 2 ቢሊዮን ብር በላይ ትርፍ አስመዝግቧል፡፡ አሁን ላይ የተመዘገበው ትርፍ ተቋሙ ካለበት የብድር ጫና ወጥቶ ራሱን እንዲችል መንገድ የሚከፍት መሆኑ ጠቁመዋል። ተቋሙ የነበረበት ከፍተኛ የብድር ጫና ወደ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መተላለፉ፣ በመንግሥት የተተገበረው የኢኮኖሚ ሪፎርም እና የተደረገው የታሪፍ ማሻሻያ ለትርፉ መመዝገብ ድርሻው የጎላ መሆኑን ዶ/ር ብሩክ አብራርተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 8 ቀን 2018 ዓ.ም