uz
Feedback
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

Kanalga Telegram’da o‘tish

Addis abeba Ethiopia

Ko'proq ko'rsatish
5 066
Obunachilar
-25624 soatlar
-1 8217 kunlar
-3 02830 kunlar
Postlar arxiv
👉 የዓይናችን ብሌን በሆነው መከላከያ ሠራዊታችን ፈፅሞ አንደራደርም‼ ♦️ "የአበራሽን ጠባሳ ያየ፣ በእሳት አይጫወትም‼" አይበገሬው መከላከያ ሠራዊታችን የኢትዮጵያ ካዝማ እና ማገር ነው። አለኝታች
👉 የዓይናችን ብሌን በሆነው መከላከያ ሠራዊታችን ፈፅሞ አንደራደርም‼ ♦️ "የአበራሽን ጠባሳ ያየ፣ በእሳት አይጫወትም‼" አይበገሬው መከላከያ ሠራዊታችን የኢትዮጵያ ካዝማ እና ማገር ነው። አለኝታችን፣ ብሔራዊ ኩራታችን እንዲሁም ለእኛ ሠላምና ደህንነት ሲል ሌት ተቀን በቁርና በሐሩር እየማሰነ ዳግም የማትገኝ ሕይወቱን የሚሰዋ ብርቅዬ ክንዳችን ነው። ጀግናው መከላከያ ሠራዊታችንን የነካ የመላው ኢትዮጵያዊ ሁሉ ጠላት ነው‼የዓይናችን ብሌን በሆነው ሠራዊታችን ለአፍታም ቢሆን  አንደራደርም‼ተሳስቶም እንኳን ቢሆን፤ ሳተናው መከላከያ ሠራዊታችንን የነካ፤ በአንድ ነገር ርግጠኛ መሆን ይችላል። ይኸውም ግብዓተ-መሬቱን በብርሐን ፍጥነት እያፋጠነ መሆኑን ነው‼ "የአበራሽን ጠባሳ ያየ፣ በእሳት አይጫወትም" እንደሚባለው፤ ከትናንት ያልተማሩ ፅንፈኞች፣ የመንደር ወጠጤዎች፣ ዘራፊዎችና ሕገ-ወጦች ሠራዊታችንን ቀና ብለው የሚያዩበት አቅምም ሆነ የሞራል ልዕልና የላቸውም። የምስራቅ አፍሪካ ኩራት የሆነው ሠራዊታችን በዘረኞች ልክ የተሰፋ አይደለም። እጅግ በጣም ይሰፋባቸዋል‼️ሠራዊታችን ውስጥ ዘረኝነት ውግዝ ነው‼️በነበልባሎቹ ጀግኖቻችን ልብ ውስጥ የገዘፉት ኢትዮጵያና ሁሉም ሕዝቦቿ ናቸው። ወገንተኝነታቸውም ለኢትዮጵያና ለሕዝቧ ብቻ እና ብቻ ነው‼️የዘረኝነት ተውሳክ የተጣባቸው ፅንፈኞችና ዘራፊዎች እንዲሁም በሕዝብ ደም የሚቆምሩ ሲራራ ቆማሪዎች፤ የዓይናችን ብሌን በሆኑት ጀግኖቻችን ከመጡ፤ አወዳደቃቸው የከፋ እንደሆነ መገንዘብ ይኖርባቸዋል። ምክንያቱም ከጥቂት ሆድ-አደሮች በስተቀር፤ በዓይኑ ብሌንና የክፉ ቀን ደራሹ በሆነው ሠራዊቱ የሚደራደር ኢትዮጵያዊ ስለሌለ ነው‼ ክብር ለሠራዊታችን፤ ክብር ለሁልጊዜ ጀግኖቻችን‼️ #የኢትዮጵያ_ክንድ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 25 ቀን 2015 ዓ.ም የሠራዊቱን ሥም በማጠልሸት እና ህዝብን ከህዝብ ለማጋጨት በተሠማሩ ሃይሎች ላይ መከላከያ የሃይል እርምጃ እንደሚወስድ አሥጠነቀቀ። የመከላከያ ሠራዊት ወቅታዊ በሆኑ ጉዳዮች ለሕዝቡ መረጃ ለመስጠትና ቀጣይ በሚወሰዱ ዕርምጃዎች ዙሪያ ባወጣው መግለጫ በርካታ ማብራሪያዎችን ሰጥቷል። መከላከያ ሠራዊቱ አለም አቀፍ እና ቀጠናዊ ሁኔታዎች እንዲሁም  ስጋቶች ሲኖሩ እንደ አመጣጣቸው የሚመክት ብቁና  ድል አድራጊ ሠራዊት መሆኑና ግጭቶች ሲፈጠሩ ከሀገር ውስጥ አልፎ በውጭም ሠላም እያሰፈነ ያለ ሀገርን ከብተና የታደገ ጀግና ሠራዊት ነው ብለዋል  ኮሎኔል ጌትነት አዳነ በመግለጫቸው፡፡ አሁናዊ በሆኑ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫውን የሰጡት የመከላከያ ሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተሩ ኮሎኔል ጌትነት አዳነ አሁን ላይ ፅንፈኛ ኃይሎች የሠራዊቱን ስም የማጠልሸት፣ ሕዝብን ከሕዝብ የማጋጨትና አሉባልታዎችን የመንዛት ተግባር ላይ ተጠምደዋል ብልዋል። ሠራዊታችን በዓለም አቀፍ ደረጃ ጀግንነቱም ሆነ ህዝባዊነቱ የተመሰከረለት ነው ያሉት ኮሎኔል ጌትነት አዳነ መከላከያ ፅንፈኛ ኃይሎች በሚፈልጉት ሳይሆን ሕዝብና መንግሥት በሚሰጡት ትዕዛዝ መሠረት ሕዝባዊነቱን በተላበሰ መንገድ ግዳጁን በጥንቃቄ እየተወጣ እንደሚገኝም ገልፀዋል። ኢትዮጵያ የውስጥ ሰላሟ እንዳይጠናከር የሚፈልጉ ኃይሎች "መከላከያ ዳር ድንበር ይጠብቅ እንጂ ለምን በክልላዊ ጉዳዮች ይገባል" የሚል ጥያቄ በማንሳት ሕዝቡንና ሠራዊቱን ለመለያየት የሚሠሩ ቡድኖች ሀገሪቱን ለማተረማመስ ባላቸው ፍላጎት በመሆኑ መከላከያ ከውስጥም ከውጭም የሚነሱ የጥፋት  ኃይሎች ላይ ዕርምጃ እንደሚወስድ ዋና ዳይሬክተሩ በመግለጫቸው አንስተዋል። የጥፋት ሀይሎች የተዘረጋውን የሠላም ጥሪ ባለመቀበል ትጥቅ አንግበው የሠላምና የልማት እንቅፋት በሆኑ በኦሮሚያ ክልል አንድ አንድ አከባቢ በሚንቀሳቀሰው የአሸባሪው ሸኔ ሀይል ላይ መከላከያ ሠራዊቱ አሳማኝ እርምጃ እየወሰደ ይገኛል፡፡ ይህን ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል እና በክልሉ የሀገር ሽማግሌዎች አባ ገዳዎችና ወላጆች ከሠራዊቱ ጋር በመሥራታቸው በርካታ ቁጥር ያለቸው የሸኔ አባላት እጅ መስጠታቸውን ኮሎኔል ጌትነት አዳነ ገልጸዋል፡፡ በአማራ ክልል ያለው ሁኔታ መሬት ላይ በተግባር ካለው ክስተት በላይ በማህበራዊ ሚዲያ  ያለው ገዝፎ የታየ ሲሆን በተቋሙ ስለ ፋኖ የሚገለፀው ትክክለኛ መረጃ በተለያየ መንገድ ትርጉም እንደተሰጠው አንስተዋል፡፡ ፋኖ የረጅም ጊዜ ታሪክ ያለውና የሀገር ዕሴት የሆነ ብዙ የተዘመረለት የህዝብ ሀብት ስለመሆኑ በ1966 ዓ.ም የተማሪዎች እንቅስቃሴ ላይ የፋኖ ተሰማራ ዝማሬና በኢትዮ-ኤርትራ እንዲሁም በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በተፈጠረው ችግርም ሀገሬ ልትፈርስ ነው ሲል ከሠራዊቱ ጎን በመሆን በልኩ ዋጋ መክፈሉ አንዱ ማሳያ እንደሆነ ዳይሬክተሩ ኮሎኔል ጌትነት በመግለጫው አስቀምጠዋል፡፡ ጽንፈኛ ሃይሎች በሠራዊቱ ብቻ ሳይሆን በፋኖ ስምም በመነገድ የመከላከያ ሠራዊት አልባሳት ይዘው ወንጀል እንደሚሰሩ ሁሉ የፋኖን የተከበረ የህዝብ ዕሴት ስም ይዘው ግንባር ሳይዘምቱ በማህበራዊ ሚዲያ የሚፎክሩ ስለመኖራቸው የገለፁት ዳይሬክተሩ ይህን ተግባር በሚፈጽሙ አካላት ላይ ሠራዊቱ ምንም ዓይነት ትዕግስት እንደሌለውና እርምጃ እንደሚወሰድ ሊታወቅ ይገባል ብለዋል። በአንድም ሆነ በሌላ መንገድ የግል ፍላጎታቸውን ለማሳካት የሠራዊቱን ስም በማጠልሸትና በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ከፋፋይ ሃሳቦችን በማሰራጨት የተጠመዱ ግለሰቦችም ሆኑ ቡድኖች ላይ መከላከያ ሕጋዊ ዕርምጃ የሚወስድ መሆኑንም አሳስበዋል። የሠራዊቱን ስም በማጠልሸት እና ጥይት በመተኮስ እንዲሁም በተለያዩ ዜዴዎች መከላከያ ሠራዊቱን የሚወጉ የሚዲያ ሞያተኞች፣ አክቲቪስቶች ፣የህግና ሥርዓት ሀዲዱን ስተው በሚመጡ የፖለቲካ ፓርቲና ፖለቲከኞች ሠራዊቱ ራሱን በመከላከል የማያዳግም እርምጃ በመውሰድ ሀገርና ህዝብ የሰጡትን አደራ በመወጣት የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት እንደሚያሥከብር በመግጫው ተናግረዋል።  በቅርቡ በሰሜን ጎንደር  አካባቢ የሸፈቱ ኃይሎች በሠራዊቱ ላይ ተኩስ ከፍተው እንደነበር ያስታወሱት ዳይሬክተሩ በወቅቱ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ዓመታዊ ክብረ በዓል ላይ ለመሳተፍ ወደ ሥፍራው አቅንተው በነበሩት በክቡር ፊልድ ማርሻል ላይ "ከበባ አድርገናል ፣በሄሊኮፕተር ነው ያመለጡት" በሚል የተሰራጨው ሕዝብን የማደናገር መረጃ የሐሰት ተረት ተረት ነው ብለዋል ኮሎኔል ጌትነት። መከላከያ አይደለም የራሱን ደኅንነት ብቻ መጠበቅ የሀገሪቱን  ሠላምና ደኅንነት እየጠበቀ እንዳለ የጥፋት ኃይሎች ሊረዱ ይገባልም ነው ያሉት በመግለጫው። መከላከያ ሠራዊት የ2015 በጀት ዓመት የሥራ አፈፃፀሙን ከላይ እስከ ታች ድረስ በመገምገም በቀጣይ የሚፈፅማቸውን ግዳጆች በብቃት ለመወጣት በአስተማማኝ የዝግጁነት ደረጃ ላይ እንደሚገኝም የመከላከያ ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተሩ ኮሎኔል ጌትነት አዳነ በመግለጫቸው አንስተዋል።

ሰማዕቱ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ #የመጨረሻው_ክፍል_4 በዚያች ሌሊት በአዲስ አበባ ውስጥ በየቤቱ ልቅሶና ዋይታ ሆነ» ሲል ጽሑፉን ይደመድማል። ይህም ጠላት የሰጠው ምስክርነት በካቶሊካዊው ፓፓ ቡራኬ አገ
ሰማዕቱ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ #የመጨረሻው_ክፍል_4 በዚያች ሌሊት በአዲስ አበባ ውስጥ በየቤቱ ልቅሶና ዋይታ ሆነ» ሲል ጽሑፉን ይደመድማል። ይህም ጠላት የሰጠው ምስክርነት በካቶሊካዊው ፓፓ ቡራኬ አገራችንን የወረረውን የፋሺስት ኢጣልያን ጦር አረመኔነትና በአንጻሩ የታየውን የኢትዮጵያን ሕዝብ ጀግንነት ሲያረጋግጥ ይኖራል። በተጨማሪም ደራሲ ጳውሎስ ኞኞ «አቡነ ጴጥሮስ እንዴት ሞቱ?» ሲል ሙሴ ፓይላክን ጠይቋቸው እርሳቸውም የሚከተለውን ተናግረዋል። «አቡነ ጴጥሮስ የተገደሉ ዕለት እዚያው ነበርኩ። መጀመሪያ በእጃቸው ይዘውት የነበረውን መጽሐፍ ቅዱሳቸውን ተሳለሙት። ቀጥለውም የያዙትን መስቀል አማትበው ሕዝቡን ባረኩ። የኪሳቸውንም ሰዓት አውጥተው ካዩ በኋላ መልሰው ከኪሳቸው ከተቱት። ወዲያው ወታደሮች በእሩምታ ተኩሰው ገደሏቸው። ይህ እንደ ሆነ አስገዳዩ ኮሎኔል ተመልካቹን ሕዝብ አጨብጭቡ ብሎ አዘዘና ተጨበጨበ። ማታ ከአስገዳዩ ኮሎኔል ጋር ተገናኝተን ስንጫወት «በዚህ ቄስ መገደል እኮ ሕዝቡ ተደስቷል» አለኝ። «እንዴት?» ብለው «አላየህም ሲያጨበጭብ?» አለኝ። እኔም «ባታውቀው ነው እንጂ የሕዝቡ ባሕል ሲናደድም ያጨበጭባል» አልኩት።«እንዴት?» ቢለኝ እጄን እያጨበጨብኩ አሳየሁት። እሱም አሳየኝ። «ከዚህ በኋላ የሆነው ቢሆን እኔ ትልቅ ማስታወሻ አግኝቻለሁ» ብሎ አቡነ ጴጥሮስ ሲገደሉ ይዘውት የነበረውን መስቀልና መጽሐፍ ቅዱስ፣ የኪስ ሰዓታቸውን ጭምር አሳየኝ። መጽሐፍ ቅዱሱ መሐል ለመሐል በጥይት ተሰንጥቋል። መስቀሉም ልክ በመሐከሉ ላይ ጥይት በስቶት ወጥቷል። የኪስ ሰዓታቸውንም እንዳየሁት እንደዚሁ ጥይት በስቶታል» ብለው ያዩትን መስክረዋል።» /ትንሣኤ፣ቁጥር 58፣1978 ዓ.ም/ ምንጭ፦ ሐመር መጽሔት ግንቦት/ሰኔ ፲፱፻፺፮ ዓ.ም

ሰማዕቱ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ #ክፍል_3 «ይሙት በቃ» የተፈረደባቸው ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በችሎት ፊት ለብዙ ሰዓታት ቆመው ስለዋሉና ደክሟቸው ስለነበር ለመቀመጥ ፈልገው ዳኛውን በትሕትናና በፈገግታ ጠ
ሰማዕቱ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ #ክፍል_3 «ይሙት በቃ» የተፈረደባቸው ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በችሎት ፊት ለብዙ ሰዓታት ቆመው ስለዋሉና ደክሟቸው ስለነበር ለመቀመጥ ፈልገው ዳኛውን በትሕትናና በፈገግታ ጠየቁት። እንዲቀመጡም ፈቀደላቸው። በመጨረሻም የሞታቸው ፍርድ ከተነበበ በኋላ የፈረዱባቸውን ዳኞች ጸልየው በመስቀላቸው ባረኳቸው። ብፁዕነታቸው እስከመቃብር አፋፍ ድረስ የፍርሃትና የድንጋጤ ምልክት ያይደለ ከልብ የሆነ ፍጹም የክብር ትሕትና ይታይባቸው ነበር። የአገራቸው በጠላት መወረር፣ የሕዝባቸው መገደልና መታሰር፣ የቤተ ክርስቲያናቸው መደፈር እስከ ሞት ያደረሳቸው እኒህ እውነተኛ ጳጳስ ለመገደል ሲወሰዱ ጥይት አልፎ ሌላ ሰው እንዳይጐዳ ግንብ ይፈለግ ጀመር። ሩቅ ባለመሔድ ከመካነ ፍትሑ 10 ሜትር ርቆ ግንብ ያለው መግደያ ቦታ ተገኘና ወደዚያ ተወሰዱ። ከገዳዮቹም አንዱ «ፊትዎን ለመሸፈን ይፈልጋሉን?» ሲል ጠየቃቸው። «ይህ የአንተ ሥራ ነው» ሲሉ ብፁዕነታቸው መለሱ። ከመግደያውም ቦታ እንደ ደረሱ ወንበር ቀረበላቸውና ፊታቸውን ወደ ግንቡ ጀርባቸውን ወደ ሕዝቡ አድርገው እንዲቀመጡ ሆኑ። ከዚያ በኋላ ስምንት ወታደሮች በስተጀርባቸው ሃያ እርምጃ ርቀው ተንበርክከው በተንጠቀቅ ቆሙ። ወዲያው አዛዡ «ተኩስ» በማለት ትእዛዝ ሲሰጥ ስምንቱም ተኩሰው መቷቸው። ግን በስምንት ጥይት ሳይሞቱ ቀሩ። መሞታቸውንና አለመሞታቸውን ለማረጋገጥ ዶክተር ተጠራ። ዶክተሩም እንዳልሞቱ አረጋገጠ። ከዚያም ሌላ ወታደር በሦስት የሽጉጥ ጥይት ራስ ቅላቸውን መትቶ ገደላቸው። የብፁዕነታቸው አስከሬን ማንም እንዳይወስደው በአስቸኳይ ከአዲስ አበባ ውጭ ማንም በማያውቀው ቦታ በምሥጢር እንዲቀበር ተደረገ። በዚያች ሌሊት በአዲስ አበባ ውስጥ በየቤቱ ልቅሶና ዋይታ ሆነ» ሲል ጽሑፉን ይደመድማል።.... ይቀጥላል... #ታሪክን_ወደኋላ

ሰማዕቱ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ #ክፍል_2 አቡነ ጴጥሮስም የሚከተለውን መለሱ። «አቡነ ቄርሎስ ግብፃዊ ናቸው፤ ስለኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን የሚገዳቸው ነገር የለም። እኔ ግን ኢትዮጵያዊ ነኝ። ኃላፊነትም
ሰማዕቱ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ #ክፍል_2 አቡነ ጴጥሮስም የሚከተለውን መለሱ። «አቡነ ቄርሎስ ግብፃዊ ናቸው፤ ስለኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን የሚገዳቸው ነገር የለም። እኔ ግን ኢትዮጵያዊ ነኝ። ኃላፊነትም ያለብኝ የቤተ ክርስቲያን አባት ነኝ። ስለዚህ ስለአገሬና ስለቤተ ክርስቲያኔ እቆረቆራለሁ። ከዚህ በቀር ለእናንተ ችሎት የማቀርበው ነገር የለኝም። ለፈጣሪዬ ብቻ የምናገረውን እናገራለሁ። እኔን ለመግደል እንደ ወሰናችሁ ዐውቃለሁ። ስለዚህ በእኔ ላይ የፈለጋችሁትን አድርጉ። ግን ተከታዮቼን አትንኩ» አሉ። ኢጣልያዊው ጋዜጠኛ ቺሮ ፓጃሊ «እኒህ ጳጳስ ሐቀኛ ነበሩ። ነገር ግን ለኢጣልያ ለጋስዮን ታዝዞ የመጣው አስተርጓሚ ዳኞች የሚሉትን ብቻ ከማስተርጐም በቀር ጳጳሱ የሚናገሩትን ሐቀኛ ንግግር አላስተረጐመም። እኔ እንኳን የሰማሁት በአዲስ አበባ ለሠላሳ ዓመት የኖረው የእቴጌ ሆቴል ኃላፊ የነበረው የግሪክ ዜጋ ማንድራኮስ አጠገቤ ተቀምጦ ስለነበር የተናገሩትን ሁሉ ስለገለጠልኝ ነው። እኔ እንደ ሰማሁት ፍርዱን ለመስማት በብዛት የተሰበሰቡት ጣልያኖችና ታዝዞ የወጣው የአዲስ አበባ ሕዝብ ሐቀኛ የሆነውን ንግግራቸውን ቢሰሙ ኖሮ ልባቸው ይነካ ነበር» ይላል። ሆኖም አስተርጓሚው በጳጳሱ ላይ ተጽዕኖ ስላሳደረባቸው እውነተኛ ንግግራቸው ሳይገለጥ እንደ ቀረ ይጽፋል። ቀጥሎም ብፁዕነታቸው በፍርድ ችሎት ላይ እንዳሉ ሕዝቡ ሁሉ ስለእርሳቸው እያዘነ ሳለ መስቀላቸውን አውጥተው እየጸለዩ ሕዝቡን ባረኩ። ወዲያው የሞታቸው ሰዓት መድረሱን ዐውቀው ሰዓታቸውን ከኪሳቸው አውጥተው ተመለከቱ። በዚህ ጊዜ ሁሉ ምንም ፍርሃት አይታይባቸውም ነበር። የሞታቸውን ፍርድ ያነብ የነበረው ኢጣልያዊ ዳኛ ግን ይንቀጠቀጥ ነበር። ታላቅ ፍርሃትም በፊቱ ይታይ ነበር። ይቀጥላል... #ታሪክን_ወደኋላ

<< አርበኛ መሞት ማን አስተማረው ታላቁ ጴጥሮስ ነው ባርኮ የሰጣቸው >> ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በ 1928 ዓ.ም ጣሊያን ኢትዮጵያን በወረረ ጊዜ ማይጨው ድረስ ዘምተው ነበር። አርበ
<< አርበኛ መሞት ማን አስተማረው ታላቁ ጴጥሮስ ነው ባርኮ የሰጣቸው >> ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በ 1928 ዓ.ም ጣሊያን ኢትዮጵያን በወረረ ጊዜ ማይጨው ድረስ ዘምተው ነበር። አርበኞች አዲስ አበባን ለመቆጣጠር ጥቃት ሲያደርጉ ከሰላሴ ጦር ጋር ወደ አዲስ አበባ መጡ። ጥቃቱን ከሽፎ አርበኞቹ ሲያፈገፍጉ አቡነ ጴጥሮስ አዲስ አበባ ቀርተው ተማረኩ። በእስር ላይ ሆነው ህዝቡ ለኢጣሊያ እንዲገዛ እንዲሰብኩ ተጠይቀው ነበር እርሳቸው ግን እንኳንስ ህዝቡ መሬቱን እንዳይገዛ በመግዘታቸው በቀድሞ የማስታወቂያ ሚኒስቴር አጥር ስር የፋሽስት ጣሊያን ጦር በመትረየስ ጥይት ተደብድበው የተሠውት ከ 87 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ዕለት ሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ.ም ነበር። የብፁዕ አቡን ጴጥሮስ ሞት ለአርበኞቹ የትግል እንቅስቃሴ በይበልጥ አቀጣጥለው። <<< ሰማዕቱ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ >>> ...ጸሐፊው ሲገልጥ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ቁመታቸው ረዘም፣ ፊታቸው ዘለግ ያለ፣ መልካቸው ጠየም ያለ ዐዋቂነታቸውና ትሕትናቸው ከገጻቸው የሚነበብ ሲሆን በዚህ ጊዜ ለብሰውት የነበረው ልብሰ ጵጵስና ጥቁር ካባ ያውም በጭቃ የተበከለ ነበር። በዚህ ሁኔታ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ወደ ችሎት ቀረቡ። ለፍርድም የተሰየሙት ዳኞች ሦስት ሲሆኑ እነዚህም ጣልያኖችና የጦር ሹማምንት ናቸው። የመካከለኛው ዳኛ ኮሎኔል ነበር። የቀረበባቸውም ወንጀል ሕዝብ ቀስቅሰዋል፣ ራስዎም ዐምፀዋል፣ ሌሎችንም እንዲያምፁ አድርገዋል የሚል ነበር። ዳኛውም «ካህናቱም ሆኑ የቤተ ክህነት ባለሥልጣኖች ሊቀ ጳጳሱ አቡነ ቄርሎስም የኢጣልያን መንግሥት ገዥነት አምነው አሜን ብለው ሲቀበሉ እርስዎ ለምን ዐመፁ? ለምን ብቻዎን አፈንጋጭ ሆኑ?» ሲል ጠየቃቸው። አቡነ ጴጥሮስም የሚከተለውን መለሱ።.... ይቀጥላል... #ታሪክን_ወደኋላ

ሰበር ዜና የምስራቅ ኢትዮጵያ የሸኔ የሎጀስቲክና ኃላፊና ቃል አቀባይ ሀረር ከተማ በቁጥጥር ስር ውሏል። በአካውንቱ ብቻ 15 ሚሊየን ብር በላይ ተገኝቶበታል
+2
ሰበር ዜና የምስራቅ ኢትዮጵያ የሸኔ የሎጀስቲክና ኃላፊና ቃል አቀባይ ሀረር ከተማ በቁጥጥር ስር ውሏል። በአካውንቱ ብቻ 15 ሚሊየን ብር በላይ ተገኝቶበታል

የመከላከያ ሠራዊት ለሕዝብ ጥቅም እና ለሀገር ክብር ራሳቸዉን አሳልፈዉ የሰጡ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ስብስብ ነው። ከ 3 ሺ ዓመታት በላይ  ባስቆጠረው የኢትዮጵያ የነጻነት ታሪክ ውስጥ ለእናት ሃገራችንና ለሕዝቧ ዘመን የማይሽረዉ እንደ ዓለት የፀና የአሸናፊነትን ታሪክ በስሙ የጻፈ ከመከላከያ ሰራዊት የቀደመ አለኝታ ተቋም ኑሯት አያዉቅም ወደፊትም አይኖርም። ሀገራችን ኢትዮጵያ ጠላት በድንበሯ፤  ጀግና በማሕጸኗ ነጥፎባት አያውቅም የሚባለው ሰንደቅ ዓላማውን ይዞ የሚሰዋ እና የሚያሸንፍ ጀግና የመከላከያ ሰራዊት ስላላት መሆኑ እሙን ነው። ኢትዮጵያ  ስታዝን የሚያጽናኑ፣ ስትወጋ የሚጠግኑ እና ወደ ኋላ ስትቀር የሚያዘምኑ ወታደሮች ባለቤት ናት። ቅኝ ገዥዎች ሲያሻቸው በአፈሙዝ ሳይችሉ በእርዳታ ስም  ዓይናቸውን የሚጥሉባት እና ጎረቤቶቿ በስጋት እና በፍርሃት በሚመለከቷት ባለ ገናና ታሪክና ሉዓላዊት ሀገር ኢትዮጵያ ዘንድ ወታደር ሆኖ መመረጥ መታደልም ክብርም ነው። የሀገር መከላከያ ሰራዊት ሀገር አብዝታ የምታምነው ወገን ከሚመካባቸው ተቋማት አንዱ ነው። የዚህ ስብስብ አካል የሆነ ወታደር ስትሆን አባቶች ሀገራቸውን፣ እናቶች ክብራቸውን እና ታዳጊዎች ተስፋቸውን በአንተ ላይ ይጥላሉ። ይሁን እንጅ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የራሳችን ሀይል በራሳችን ገንብተን እና አዘምነን ሉዓላዊነታችን እና ተፈሪነታችን ይበልጥ በምናጸናበት በዚህ ጊዜ እዚህም እዚያም የሚታዩ አውቀው በድፍረት ሳያውቁ በስህተት ባልታወቀ መንገድ የመከላከያ ሰራዊትን ክብር በማይመጥን መልኩ ስም በማጥፋት በግል እና በህቡዕ የሚንቀሳቀሱ አካላት መኖራቸውን እየተመለከትን ነው። ፈርጀ ብዙ በሆነ መንገድ  የሁሉም የሚዲያ አማራጮችን በመጠቀም በሃሰተኛ ፕሮፓጋንዳ ስሙን ለማጥፋትም ያለ እረፍት እየተሠራ ነው። የሃገር መከላከያ ሰራዋት ስም ሲጠፋ፣ ደጀን ሕዝብ ሲያጣና ሲዳከም የሚጠቀሙት ጠላቶቻችን እንጂ የእኛ ሕዝብ አለመሆኑን በመገንዘብ የጠላቶቻችን ረዥም እጅ መጠቀሚያ ከመሆን ልንቆጠብ ይገባል። የሃገር መከላከያ ሰራዊትን ክብር መንካት ከሃገር ክህደት ትይዩ የሚቆም ወንጀል መሆኑንም መገንዘብ ያስፈልጋል። እነዚህ ሀይሎች ያልተረዱት ሌላው ሀቅ ኢትዮጵያ ከውስጥም ይሁን ከውጭ የሚቃጣባት የትኛዉም አይነት ጥቃት በብርሀን ፍጥነት መመከት የሚችል፤ በፕሮፓጋንዳም የማይፈታ የመከላከያ ሰራዊት መገንባቷን ነው። እነዚህ ሃይሎች  የሃገር መከላከያ ሰራዊትን ከሕዝብ ጋር ለማጋጨት ወይም ለመነጠል የትኛውንም ርቀት ቢጓዙ አይሳካላቸውም ምክንያቱም ሕዝብ የእውነት ሚዛን ነው። ከሃገር መከላከያ ሰራዊት ውጭ የሆነች ሃገር እንደማትፀና ጠንቅቆ ያውቃልና። ስለሆነም ከራሳችን አብራክ የወጣዉ የሃገር መከላከያ ሰራዊት  ለሕዝባችን ዘላቂ ሰላምና ልዕልና የቆመ መሆኑን በመረዳት፣ ከሕዝባችን ጋር ምንም ጥል የሌለው መሆኑ ብቻ ሳይሆን እንደ ዓይኑ ብሌን  የሚጠብቀው ማኅበረሰብ ላይ አደጋ የመጣል ተልእኮ የሌለው መሆኑን በመገንዘብ የዘላቂ ሰላም ተልእኮውን መደገፍ ይጠበቅብናል። አቶ ግዛቸው ሙሉነህ እንደፃፉት

#ፍቅር ይዞኝ  እንጂ#       💚💛💓💚💛💓 መች አስቤው እንደስራ፣   💚 መች ቆጥሬው እንደስራ፣   💛 ጨው ባለው በርሀውስጥ፣   💓 መንከራተቴ ያለእፎይታ፣ ቀጥ ባለ ተራራላይ፣   ላብ ማፍሰሴ ጠዋት ማታ፣                            የቤተሰቤ  ዓይን ባይኔላይ፣              ያለእረፍት ሲመላለስ፣              ልቻለሁ ከሀገሬ አይበልጡም፣               እያልኩኝ የምንከላወስ። ዘመን በዘመን ሲቀየር፣ በዓል አውዳመት ሲመጣ፣ ለንጀራ ብዬነውዴ?       ከበርሃ የማልወጣ?        ከዘመድ አዝማድ የማልበላ፣        ከአብሮ አደጎቼ  የማልጠጣ?       የያዘ ይዞኝ  እንጂ፣      የሀገሬ ፍቅር  ሚ ሉት ልክፍት፣     እኔ ሁለት  ሆድ የለኝ፣ እስክሞት  የሚያከራት ተኝ፤ ላቤ በዝቶ በጀርባኤላይ የጨው  አመድ መስሎ   እስኪታይ፣                                 ከእረፍት  እንቅልፍ ተፋትቼ፣           የማጣው  የቅፅበት ፋታ፣            ቀናት በእግሬ  የምኳትን፣           ጫማሄን  ከእግሬ ሳልፈታ። ቀዝቃዛ ውሃ  ነፋሻ አየር ስሙ እንኳንእየናፈቀኝ። ጨዋማ ውሃ እየጠጣሁ በድካም  ጨው የሚያልበኝ።                        ለጀራ ብዬ አይደለም                        ርቄ ከመአል ማዶ                       በቀበሮ ጎድጓድ ሆኝ                       ምሰማው  የወገን መርዶ😢😢                      ለእንጀራኤ ብዬነውዴ                    በህእቴ ሰርግ የማልገኘው                     በወንድሜ ደስታ የማልመጣ።                   ከሀገሬ  አስተሳስሮኝጂ                   ወጥ አቶ አደር የመሆኔ እጣ፡                 ለጀራኤ ብዬ አይደለም                           የምቃጠል  በበረሀ፡               የሚያነደኝ   ቦንብ ፈንጂ።       ቃልኪዳን   ከሆነችው። ከሀገሬ  ፍቅር   ይዞኝእንጂ     ኢ 🇪🇹ት🇪🇹ዮ🇪🇹ጵ 🇪🇹ያ 🇪🇹 ዬ ኢ 🇪🇹ት🇪🇹ዮ🇪🇹ጵ 🇪🇹ያ 🇪🇹 ዬ ኢ 🇪🇹ት🇪🇹ዮ🇪🇹ጵ 🇪🇹ያ 🇪🇹 ዬ ኢ 🇪🇹ት🇪🇹ዮ🇪🇹ጵ 🇪🇹ያ 🇪🇹 ዬ በሳምሶን

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሀምሌ16 ቀን 2015 ዓ.ም         "የጓዳዊነትና ጓደኝነት ዝንቅ በእኛ ቤት" በተለያዩ የሞያ መስኮች ከእኛ ከወታደሮቹ ቤት ውጭ ማለቴ ነው.. የሞያ ባልደረባዊ ጉድኝት ላይ ህጸጾች ሲነገሩ እሰማለሁ። በተለይ በስራ ህይወት የማያቋርጡ የተለያዩ የዕድገት፣ የሽልማት፣ሌሎች ጥቅማ ጥቅሞች አሉና፤እነዚህ ጥበባዊና መርህ መር የተግባቦት አውድ ካልተፈጠረላቸው ማሻኮታቸው አይቀሬ ይሆናል። እርግጥ ነው እኛ ቤት ጥቅምን የተገነ፣መጠቀምን ያለመ አስተሳሰብና ዕምነት የለም።የእኛ ቤት ለሌሎች በመኖር በነፍስ ክፍያ በሚደመደም ከራስ ግላዊ ፍላጎት የተቆራረጡ ቆራጦች መኖሪያ ነውና ከሌላው ጋር ለማናፃጸር ከበድ ቢል አይገርምም። እኛ ቤት በጣም ብዙ ነገሮች የራሳቸው የተለየ ቀለም አላቸው። ከውትድርናው ዓለም በህብራዊ ውበት የተንቆጠቆጠው ቤታችን ማዶ ባለው ተለምዷዊ ህይወት ሁላችንም የምናውቀው የጓደኝነትም ሆነ ሌላ ግንኙነቶች በመደበኛነት የሚታወቁ ናቸው። በእኛ በወታደሮቹ  አብሮነታዊ ጉድኝቶቻችን ጓደኝነትም ጓዳዊነትም ተዛንቀው ይገኛሉ።ትርጉማቸውም በእኛ ቤታዊ ልዩ ቀለም ላይ ይመሠረታሉና በዚሁ ቁምነገር ዙሪያ ጥቂት እንባባል። ጓዳዊነት በእኛ ቤት የሞያዊ አንድነታችን ህብር ማጽኛ፣በንጹህ ልብና በቀና አዕምሮ የሚያስተሳስረን የአንድነታችን ፍቅራዊ ጥብቅ ሃረግ ነው። ጓዳዊነት፦ የዕድሜ፣የቅጥር ዘመን፣የማዕረግ፣የክፍል ሌላም ሌላም ልዮነት ሳይገድበው በውትድርና ህይወት ውስጥ መኖር፣ሀገርና ህዝብን በማገልገል ሂደት ውስጥ መገኘት የሚያቀዳጀን ቁርኝት ነው። በክፍላችንም ከክፍላችን ውጪም የትም ሆነ የት ወታደር ከሆነ ጋር ሁሉ በዓይን ጥቅሻ የምንግባባበት ልዩ ጉድኝት። በጓዳዊ ጉድኝት ውስጥ ጥብቅ መርህ አለ።መርሁ "ምንድነው" ካላችሁኝ? 'ከይሉኝታ፣ከተራ መሸነጋገልና ማስመሰል የራቀና ስህተትን በመተራረም ኮስታራ ዑደት ላይ የተመሰረተ እና በጣም ልዩ መሆኑ።'እላችሁለሁ። ከውትድርናው ዓለም ቤታችን ውጭ የጓዳዊነትን ዓይነት በፍጹም ግልጸኝነት ላይ የተመሰረተ፤"ይህን ብለው ምን ይለኝ? ምንስ ይሰማው ይሆን?"ከሚል ፈራ ተባዊ ጥርጣሬ የተላቀቀ ፍጹም ጤናማ የሆነ ጉድኝት ማግኘት ይከብዳል ባይ ነኝ። በዚህ ጓዳዊነት ይሉት የእኛ ቤት ጉድኝት ብዙ አስገራሚ ገጠመኞችን ማንሳት ይቻላል።የዛሬው ጭውውታችን የእኛን ጓዳዊነትና ጓደኝነት ዝንቅ እውነታ በጨረፍታ ማሳየት ስለሆነ ሌላ ጊዜ በገጠመኞቹ እንመለስበታለን። ስናጠቃልለው ጓዳዊነት በእኛ፤ የውትድርናን ህይወት እስከተጋራን በየትኛውም ቦታና ሁኔታ ተዋወቅንም አልተዋወቅን አንዱ ስህተት ፈጥሮ ሲገኝ ሌላኛው የማረም ግዴታውን እየተወጣ ሞያዊ ክብርን አስጠብቆ ማዝለቅ የሚያስችል ግሩም የእኛ ቤት የጉድኝት ዘይቤ እንደሆነ የቀጠለ የህይወታችን አካል ነው። ሌላኛው በግላዊ ምርጫ  እንደማንኛውም ሰው የምንፈጥረው ጓደኝነት ነው።የሚገርመው በእኛ ቤት ይህ በግል ምርጫ የምንመሰርተው ጓደኝነትም የራሱ የሆነ የተለየ ቀለም ያለው መሆኑ ነው። ከእኛ ወታደሮቹ ቤት ውጭ ያለው ጓደኝነት ብዙ ገደቦች አሉት።አንዱና ዋነኛው በውጭኛው አለም ምን የቅርብ ቅርብ ጓደኛሞች ቢኮን በተለየ አጋጣሚ ካልሆነ በስተቀር የየራስ ህይወትና ኑሮ ስለሚኖሩ የእኛን የተለየ እንዲሆን ያደርገዋል። የእኛ ቤት ጓደኝነት በአንድ ቤት እየተኖረ፣አንድ አይነት ምግብ እየተበላ፣በአንድ ዓይነት ሁለንተናዊ መስተጋብር የሚከወን ዘውትራዊ ተመሳስሎ ያለው ነው። ታዲያ ወዳጆቼ! በእኛ ቤት ጓደኝነት ምንም እንኳን በግል ነጻ ፈቃድ ላይ ተመስርቶ ቢፈጠርም፤ከሞያዊ መርህ ውልፊት ሊል አይገባውም። በዚህ ቀልድ የለም።በጓደኝነት ግላዊ ጉድኝት ውስጥ ነጻነቱ እንደተጠበቀ ሆኖ፤በስመ-ጓደኝነት አንዱ የአንዱን ስህተት ባለማረም "እከከኝ ልከክልህ" ይሉት ያልተገባ መልክን ካበጀ፤ ይህ ጓደኝነት ጥያቄ ውስጥ ይወድቃል።እንዲህ ያለው ጓደኝነት "ርካሽ" ተብሎም በጓዶች ጓዳዊነት መርህ ይፈረጃል። የእኛ ቤት እንዲህ ነው።መኖራችን ሁሉ ከግላዊነት የወጣ፣ማንኛውም ፍላጎታችን ከቆምንለት ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊያንን ከመጠበቅ ቁርጠኛ ዓላማችን በታች የሆነ ነው። ሁሌም ድንቅ የሚለኝ የእኛን ቤት ህይወት ያጣጣመ ማንኛውም ወታደር ከአገልግሎት በሁዋላ በየትኛውም ህይወትና ሞያዊ መስክ ቢሰማራ፤የኖረበትን የውትድርና ቤት 'የጓዳዊነትንና የጓደኝነትን ዝንቅ ቃና' ፈጽሞ መርሳት አለመቻሉ ነው። ምን ስኬታማና የተመቸ አኗኗር መስርቶ ቢኖርም፤የኖረበት የውትድርና ቤቱ በፍቅርና በደስታ ያጣጣመውን በፍፁም ግልጸኝነት የተመሠረተ ጓዳዊነትም ሆነ ጓደኝነት አይረሴ 'ትዝታው' ሆኖበት፤ጣፋጭ ጣዕሙን ሁሌም ይናፍቀዋል። በእርግጥም በፍጹም ግልጸኝነት የሚመሰረት ጉድኝት ከወዴት ይኖራል ብትሉኝ? በልበ-ሙሉነት "እኛ ወታደሮች ቤት" እላችሁዋለሁ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 08 ቀን 2015 ዓ.ም              "አሳምሮ ይገባኛል!!" በዜግነታዊ ዕምነት ሀገር መውደድ፣ስለ ሀገር መልካምን ሁሉ መሻት መፈለግ መመኘት ተገቢም ተጠባቂም የሆነ ሰናይ ሃሳብ ነው። ነገር ግን የሆነ እንከን ብቅ ባለ ቁጥር የዳር ተመልካች በመሆንና እንደ ጲላጦስ እራስን "ከደሙ ንጹህ" ባደረገ ምልከታ ከሳሽና ወቃሽ ሆኖ መገኘት ሀገርን ከመውደድ ጋር ተቆራኝቶ  መታየት አለበት ብዬ አላምንም። እንኳንና ሀገር የመሰለ ግዙፍና ግኑን ሀሳብ በማህበራዊ ግላዊ የአኗኗር ዘይቤያችን እኮ በዙሪያችን ያሉ አብዝተን የምንወዳቸው ሰዎችን ስናስብ፤ፍጹም ህጸጽ አልባና ፍጹም ስለሆኑ አይደለም። ይህንን ከጓደኝነት፣ከፍቅር ጥምረት፣ከትዳር አጋር፣ከልጅ ወዘተ..አያይዘን ለመመልከት ብንሞክር በየዕለት ግንኙነታችን የሚከሰቱ የፍላጎት፣የነገሮች አተያይ፣ሌላም ሌላም ምክንያቶች የሚወልዷቸው ግጭቶች ይከሰታሉ። ታዲያ በየተከሰቱ ግጭቶች ሁሉ እስከ መጨረሻው በሚዘልቅ ስሜታዊነት በሚፈጥራቸው፣ንዴት በሚከስታቸው፣እራስን ብቻ "ትክክል ነኝ" በሚል እቡይነት ህይወታችንን ብንመራ በዙሪያችን አንድም ሰው ሊኖር አይችልም። ሰዎች ነንና ትዕግስት በሚያላብስ አስተውሎት፣ህጸጽን በሚያርም ብስለት፣አዕምሯችን በሚያቀብለን ለአብሮነት በሚጠቅሙ በጎ ሀሳቦችን በመጠቀም መተካከም ስለምንችል ነው በዙሪያችን የሚኖሩ ግላዊ ጉድኝቶቻችንን መጠበቅ እና ማዝለቅ የቻልነው። ወደገዘፈው የሀገር ሃሳብ ስንመጣ ታዲያ ግላዊ ማህበራዊ መስተጋብራችንን ጤናማ እንዲሆን ከምንጠቀመው ዕውቀት፣ጥበብ አርቆ አሳቢነትና መልካምነት ስለ ሀገር ሲሆን አልቀን መጠቀም ግድ ይለናል። ታዲያ በማህበራዊ ሚዲያዎች ከግላዊ ፍላጎት ባልተላቀቀ ፣ጥላቻ ወለድና  ከእውነተኛነት ጋር በእጅጉ የተራራቁ አሉባልታ ነዢዎች በጽሁፎቻቸው፣ በንግግራቸው እርስ በርስ የሚያባላ፣ሰላምን የሚነሳ፣ አንዱን ቅዱስ ሌላኛውን ዲያቢሎስ በሚያደርግ የሰው ልጅ ለሆነ ሁሉ የማይበጁ ግልብና ፍቅርን አብሮነትን የገፉ ክፉ ሃሳቦችን የሚያራምዱ አካላት መነሻቸው ሀገር ወዳድነት ነው ሊባል ይችላል? አልፈው ተርፈው የሀገር ምልክት፣የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የሀገር ብሄራዊ ጥቅም ማረጋገጫ የሆነውን የመከላከያ ተቋም ማንጓጠጥ፣በሴራ ሽረባ የሀሰት አቧራ ማቡለል "ኢትዮጵያን ከሚል" የትኛውም ዜጋ ይጠበቃል? እኔ የኢትዮጵያ ወጥቶ-አደር አሳምሮ ይገባኛል።ለሀገሬ በጽናት የቆምኩ ነኝና የትኛውም በቀቀናዊ ጥላቻ ወለድ የሀሰት አቧራ በቀላሉ የሚያፍነኝ አይደለሁም። እናም ለኢትዮጵያዬ ህልውና በነፍስ ዋጋ ክፍያ ባላንጣዎቿን ስፋለም ከግል ፍላጎቶቼ መሟላት ጋር ተያይዞ ሳይሆን፤ሀገሬን ከነህመሟ ስለምወድ ስለማፈቅራት ነው።       "ክብር ስለኢትዮጵያ ተዋዳቂው ወታደር"

አሜሪካ ለዩክሬን ክላስተር ቦንብ መላኳ ተገለጸ አሜሪካ ለዩክሬን ከ120 በላይ አገራት የተከለከለውን ክላስተር ቦንብ መላኳ ተገለጸ፡፡ አሜሪካ ከሰሞኑ ክላስተር ቦንብ ለዩክሬን ለመስጠት እንደምትፈልግ
አሜሪካ ለዩክሬን ክላስተር ቦንብ መላኳ ተገለጸ አሜሪካ ለዩክሬን ከ120 በላይ አገራት የተከለከለውን ክላስተር ቦንብ   መላኳ ተገለጸ፡፡ አሜሪካ ከሰሞኑ ክላስተር ቦንብ ለዩክሬን ለመስጠት እንደምትፈልግ መግለጿን ተከትሎ ዓለም አቀፍ ተቃውሞዎች በርትተው የነበረ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት የጦር መሳሪያው ዩክሬን እጅ መግባቱ ተነግሯል፡፡ የዩክሬን ባለስልጣናት ክላስተር ቦንቡን የምንጠቀመው የጠላት ጦር በተከማቸባቸው ውስን አካባቢዎች እንደሆነ አስታውቀዋል፡፡ የደቡባዊ ዩክሬን ጦር ቃል አቀባይ ቫለሪን ሸርሸን መሳሪያዎቹን በሩሲያ ግዛት ውስጥ አንደማይጠቀሙ ገልጸው ነገር ግን  የሩሲያ ጦር በብዛት የተከማቸባቸውን ቦታዎች ምሽግ ለመስበር ጥቅም ላይ ይውላሉ ብለዋል፡፡ ሩሲያ በበኩሏ ክላስተር ቦንቦቹ ጥቅም ላይ የሚውሉ ከሆነ ምላሹ ተመሳሳይ እንደሚሆን ማስጠንቀቋን አልጃዚራ ዘግቧል፡፡ ይህን የአሜሪካን ድጋፍ  ካናዳ፣ ስፔን እና እንግሊዝ የክላስተር ቦምቡ ጥቅም ላይ እንዳይውል የተደረሰውን ዓለም አቀፍ ስምምነት የጣሰ ነው በሚል ተቃውመውታል፡፡ ክላስተር ቦንብ በአየር የሚጣል ወይም ከመሬት የሚተኮስ ፈንጂ ሲሆን አንዱ ቦንብ በውስጡ በርካታ ትናንሽ ቦንቦችን የያዘ አደገኛ መሳሪያ ነው፡፡ ክለስተር ቦንቡ ሲተኮስ ትናንሾቹ ቦንቦች ከተያዙበት ተተኳሽ በመውጣት በሰፊ መሬት ላይ ተሰራጭተው የአንድ የእግር ኳስ ሜዳ ስፋት ባለው መሬት ላይ ያለን ኢላማ የማውደም አቅም እንዳላቸውም ተመላክቷል፡፡

ሰላም እንዴት አደራችሁ የቻናላችን ቤተሰቦች🌤 ዛሬ አዲስ ቀን ነው ፤ ያሰባችሁት ፣ ያቀዳችሁት የሚሰምርበት የተዋበ ቀን ይሁንላችሁ ! ከዚህ ሰዓት ጀምሮ መረጃዎችን ወደ እናንተ ማድረስ አንጀምራለን
ሰላም እንዴት አደራችሁ የቻናላችን ቤተሰቦች🌤 ዛሬ አዲስ ቀን ነው ፤ ያሰባችሁት ፣ ያቀዳችሁት የሚሰምርበት የተዋበ ቀን ይሁንላችሁ ! ከዚህ ሰዓት ጀምሮ  መረጃዎችን ወደ እናንተ ማድረስ አንጀምራለን ! ሰላም ለእናት ሀገር ኢትዮጵያ 💚💛❤️ የሚገርም ጁምዓ ተመኘሁላችሁ....🙌

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ2026ቱ የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ለማለፍ በምድብ ማጣሪያው የሚገጥማቸው ሀገራት ይፋ ሆነዋል *********************** በኮትዲቫሯ መዲና አቢጃን ዛሬ ይፋ በሆነ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ2026ቱ የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ለማለፍ በምድብ ማጣሪያው የሚገጥማቸው ሀገራት ይፋ ሆነዋል *********************** በኮትዲቫሯ መዲና አቢጃን  ዛሬ ይፋ  በሆነው ድልድል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በምድብ አንድ ከግብፅ፣ ቡርኪና ፋሶ፣ ጊኒ ቢሳዎ፣ ሴራሊዮን እና ጂቡቲ ጋር ተደልድሏል። በምድብ ሁለት ናይጄሪያ እና ደቡብ አፍሪካ የሚገኙት ድልድል በአመዛኙ ጠንካራው ምድብ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል። 54 የአፍሪካ ሀገራት በ9 ምድቦች ውስጥ የማጣሪያ ጨወታቸውን የሚያደርጉ ሲሆን ከየምድባቸው ቀዳሚ ሆነው የሚያጠናቅቁ 9 ሀገራት 48 ብሔራዊ ቡድኖች ለመጀመሪያ ጊዜ በሚሳተፉበት የአሜሪካ፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ የጣምራ አዘጋጅት የዓለም ዋንጫ ላይ በቀጥታ የሚያልፉ ይሆናል። በሰለሞን አባቡ

የግብጽ እና የኢትዮጵያ መሪዎች በሱዳኑ ግጭት እና በህዳሴ ግድብ ዙሪያ መነጋገራቸዉ ተገለጸ፡፡ የግብጹ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አል-ሲሲ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ በሱዳን ስላለዉ ግጭት እና
የግብጽ እና የኢትዮጵያ መሪዎች በሱዳኑ ግጭት እና በህዳሴ ግድብ ዙሪያ መነጋገራቸዉ ተገለጸ፡፡ የግብጹ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አል-ሲሲ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ በሱዳን ስላለዉ ግጭት እና በህዳሴ ግድብ ዙሪያ በካይሮ መነጋገራቸዉን አናዶሉ ዘግቧል፡፡ የሁለቱ አገራት መሪዎች ዉይይት የሱዳን የጎረቤት አገራት መሪዎች በሱዳኑ ግጭት መፍትሄ ዙሪያ ከሚያደርጉት ጉባኤ በፊት የተደረገ መሆኑንም የዜና ወኪሉ አክሎ ጠቅሷል፡፡ በግብጽ ፕሬዝዳንት በኩል የወጣ መግለጫ እንደሚያሳየዉ ሁለቱ መሪዎች በሱዳን ያለዉን ግጭት ማቆም በሚቻልበት ሁኔታ ዙሪያ ፣ የሁለትዮሽ ግንኙነትን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ እና በታላቁ የህዳሴ ግድብ ዙሪያ መነጋገራቸዉን ያሳያል፡፡ ግብጽ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ከአባይ ወንዝ ከምታገኘዉ የዉሃ መጠን አብላጫዉን ድርሻ ይወስዳል በሚል እንደ ቋሚ ስጋት የምትቆጥረዉ ሲሆን፣  በግድቡ አሞላል እና አሰራር ዙሪያ አሳሪ ስምምነት እንዲኖር ትፈልጋለች፡፡ ኢትዮጵያ በበኩሏ ግድቡ ለምታደርገዉ የዕድገት ጉዞ ወሳኝ መንገድ መሆኑን በማንሳት ፣ የታችኛዉ ተፋሰስ አገራት የሆኑትን ግብጽን እና ሱዳንን የዉሃ ድርሻ በምንም ዓይነት መልኩ እንደማይጎዳ ትገልጻለች ሲል ዜና ወኪሉ አክሏል፡፡ ለዓመታት በግድቡ አሞላል እና አሰራር ዙሪያ ሲደረግ የነበረዉ ዉይይት መፍትሄ ማምጣት አለመቻሉንም ገልጿል፡፡ ዕሮብ ዕለት ጠቅላይ ሚኒስቴር ዐብይ አህመድ የሱዳን የጎረቤት አገራት መሪዎች ጉባኤን የሚሳተፉ የኢትዮጵያ ልኡካንን መርተዉ ወደ ግብጽ ሄደዋል፡፡ ሱዳን በፈጥኖ ደራሽ ሃይሉ እና በመንግስት ጦር መካከል ከሚያዚያ ጀምሮ በተፈጠረ ግጭት እስካሁን 3ሺህ ንጹሃን የተገደሉ ሲሆን በሺዎች የሚቆጠሩ ደግሞ መጎዳታቸዉ የአናዶሉ ኤጀንሲ ዘገባ ያመለክታል፡፡ በእስከዳር ግርማ ሐምሌ 06 ቀን 2015 ዓ.ም