fa
Feedback
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

رفتن به کانال در Telegram

Addis abeba Ethiopia

نمایش بیشتر
5 082
مشترکین
-11024 ساعت
-1 9137 روز
-2 77030 روز
آرشیو پست ها
<< አርበኛ መሞት ማን አስተማረው ታላቁ ጴጥሮስ ነው ባርኮ የሰጣቸው >> ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በ 1928 ዓ.ም ጣሊያን ኢትዮጵያን በወረረ ጊዜ ማይጨው ድረስ ዘምተው ነበር። አርበ
<< አርበኛ መሞት ማን አስተማረው ታላቁ ጴጥሮስ ነው ባርኮ የሰጣቸው >> ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በ 1928 ዓ.ም ጣሊያን ኢትዮጵያን በወረረ ጊዜ ማይጨው ድረስ ዘምተው ነበር። አርበኞች አዲስ አበባን ለመቆጣጠር ጥቃት ሲያደርጉ ከሰላሴ ጦር ጋር ወደ አዲስ አበባ መጡ። ጥቃቱን ከሽፎ አርበኞቹ ሲያፈገፍጉ አቡነ ጴጥሮስ አዲስ አበባ ቀርተው ተማረኩ። በእስር ላይ ሆነው ህዝቡ ለኢጣሊያ እንዲገዛ እንዲሰብኩ ተጠይቀው ነበር እርሳቸው ግን እንኳንስ ህዝቡ መሬቱን እንዳይገዛ በመግዘታቸው በቀድሞ የማስታወቂያ ሚኒስቴር አጥር ስር የፋሽስት ጣሊያን ጦር በመትረየስ ጥይት ተደብድበው የተሠውት ከ 87 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ዕለት ሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ.ም ነበር። የብፁዕ አቡን ጴጥሮስ ሞት ለአርበኞቹ የትግል እንቅስቃሴ በይበልጥ አቀጣጥለው። <<< ሰማዕቱ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ >>> ...ጸሐፊው ሲገልጥ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ቁመታቸው ረዘም፣ ፊታቸው ዘለግ ያለ፣ መልካቸው ጠየም ያለ ዐዋቂነታቸውና ትሕትናቸው ከገጻቸው የሚነበብ ሲሆን በዚህ ጊዜ ለብሰውት የነበረው ልብሰ ጵጵስና ጥቁር ካባ ያውም በጭቃ የተበከለ ነበር። በዚህ ሁኔታ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ወደ ችሎት ቀረቡ። ለፍርድም የተሰየሙት ዳኞች ሦስት ሲሆኑ እነዚህም ጣልያኖችና የጦር ሹማምንት ናቸው። የመካከለኛው ዳኛ ኮሎኔል ነበር። የቀረበባቸውም ወንጀል ሕዝብ ቀስቅሰዋል፣ ራስዎም ዐምፀዋል፣ ሌሎችንም እንዲያምፁ አድርገዋል የሚል ነበር። ዳኛውም «ካህናቱም ሆኑ የቤተ ክህነት ባለሥልጣኖች ሊቀ ጳጳሱ አቡነ ቄርሎስም የኢጣልያን መንግሥት ገዥነት አምነው አሜን ብለው ሲቀበሉ እርስዎ ለምን ዐመፁ? ለምን ብቻዎን አፈንጋጭ ሆኑ?» ሲል ጠየቃቸው። አቡነ ጴጥሮስም የሚከተለውን መለሱ።.... ይቀጥላል... #ታሪክን_ወደኋላ

ሰበር ዜና የምስራቅ ኢትዮጵያ የሸኔ የሎጀስቲክና ኃላፊና ቃል አቀባይ ሀረር ከተማ በቁጥጥር ስር ውሏል። በአካውንቱ ብቻ 15 ሚሊየን ብር በላይ ተገኝቶበታል
+2
ሰበር ዜና የምስራቅ ኢትዮጵያ የሸኔ የሎጀስቲክና ኃላፊና ቃል አቀባይ ሀረር ከተማ በቁጥጥር ስር ውሏል። በአካውንቱ ብቻ 15 ሚሊየን ብር በላይ ተገኝቶበታል

የመከላከያ ሠራዊት ለሕዝብ ጥቅም እና ለሀገር ክብር ራሳቸዉን አሳልፈዉ የሰጡ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ስብስብ ነው። ከ 3 ሺ ዓመታት በላይ  ባስቆጠረው የኢትዮጵያ የነጻነት ታሪክ ውስጥ ለእናት ሃገራችንና ለሕዝቧ ዘመን የማይሽረዉ እንደ ዓለት የፀና የአሸናፊነትን ታሪክ በስሙ የጻፈ ከመከላከያ ሰራዊት የቀደመ አለኝታ ተቋም ኑሯት አያዉቅም ወደፊትም አይኖርም። ሀገራችን ኢትዮጵያ ጠላት በድንበሯ፤  ጀግና በማሕጸኗ ነጥፎባት አያውቅም የሚባለው ሰንደቅ ዓላማውን ይዞ የሚሰዋ እና የሚያሸንፍ ጀግና የመከላከያ ሰራዊት ስላላት መሆኑ እሙን ነው። ኢትዮጵያ  ስታዝን የሚያጽናኑ፣ ስትወጋ የሚጠግኑ እና ወደ ኋላ ስትቀር የሚያዘምኑ ወታደሮች ባለቤት ናት። ቅኝ ገዥዎች ሲያሻቸው በአፈሙዝ ሳይችሉ በእርዳታ ስም  ዓይናቸውን የሚጥሉባት እና ጎረቤቶቿ በስጋት እና በፍርሃት በሚመለከቷት ባለ ገናና ታሪክና ሉዓላዊት ሀገር ኢትዮጵያ ዘንድ ወታደር ሆኖ መመረጥ መታደልም ክብርም ነው። የሀገር መከላከያ ሰራዊት ሀገር አብዝታ የምታምነው ወገን ከሚመካባቸው ተቋማት አንዱ ነው። የዚህ ስብስብ አካል የሆነ ወታደር ስትሆን አባቶች ሀገራቸውን፣ እናቶች ክብራቸውን እና ታዳጊዎች ተስፋቸውን በአንተ ላይ ይጥላሉ። ይሁን እንጅ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የራሳችን ሀይል በራሳችን ገንብተን እና አዘምነን ሉዓላዊነታችን እና ተፈሪነታችን ይበልጥ በምናጸናበት በዚህ ጊዜ እዚህም እዚያም የሚታዩ አውቀው በድፍረት ሳያውቁ በስህተት ባልታወቀ መንገድ የመከላከያ ሰራዊትን ክብር በማይመጥን መልኩ ስም በማጥፋት በግል እና በህቡዕ የሚንቀሳቀሱ አካላት መኖራቸውን እየተመለከትን ነው። ፈርጀ ብዙ በሆነ መንገድ  የሁሉም የሚዲያ አማራጮችን በመጠቀም በሃሰተኛ ፕሮፓጋንዳ ስሙን ለማጥፋትም ያለ እረፍት እየተሠራ ነው። የሃገር መከላከያ ሰራዋት ስም ሲጠፋ፣ ደጀን ሕዝብ ሲያጣና ሲዳከም የሚጠቀሙት ጠላቶቻችን እንጂ የእኛ ሕዝብ አለመሆኑን በመገንዘብ የጠላቶቻችን ረዥም እጅ መጠቀሚያ ከመሆን ልንቆጠብ ይገባል። የሃገር መከላከያ ሰራዊትን ክብር መንካት ከሃገር ክህደት ትይዩ የሚቆም ወንጀል መሆኑንም መገንዘብ ያስፈልጋል። እነዚህ ሀይሎች ያልተረዱት ሌላው ሀቅ ኢትዮጵያ ከውስጥም ይሁን ከውጭ የሚቃጣባት የትኛዉም አይነት ጥቃት በብርሀን ፍጥነት መመከት የሚችል፤ በፕሮፓጋንዳም የማይፈታ የመከላከያ ሰራዊት መገንባቷን ነው። እነዚህ ሃይሎች  የሃገር መከላከያ ሰራዊትን ከሕዝብ ጋር ለማጋጨት ወይም ለመነጠል የትኛውንም ርቀት ቢጓዙ አይሳካላቸውም ምክንያቱም ሕዝብ የእውነት ሚዛን ነው። ከሃገር መከላከያ ሰራዊት ውጭ የሆነች ሃገር እንደማትፀና ጠንቅቆ ያውቃልና። ስለሆነም ከራሳችን አብራክ የወጣዉ የሃገር መከላከያ ሰራዊት  ለሕዝባችን ዘላቂ ሰላምና ልዕልና የቆመ መሆኑን በመረዳት፣ ከሕዝባችን ጋር ምንም ጥል የሌለው መሆኑ ብቻ ሳይሆን እንደ ዓይኑ ብሌን  የሚጠብቀው ማኅበረሰብ ላይ አደጋ የመጣል ተልእኮ የሌለው መሆኑን በመገንዘብ የዘላቂ ሰላም ተልእኮውን መደገፍ ይጠበቅብናል። አቶ ግዛቸው ሙሉነህ እንደፃፉት

#ፍቅር ይዞኝ  እንጂ#       💚💛💓💚💛💓 መች አስቤው እንደስራ፣   💚 መች ቆጥሬው እንደስራ፣   💛 ጨው ባለው በርሀውስጥ፣   💓 መንከራተቴ ያለእፎይታ፣ ቀጥ ባለ ተራራላይ፣   ላብ ማፍሰሴ ጠዋት ማታ፣                            የቤተሰቤ  ዓይን ባይኔላይ፣              ያለእረፍት ሲመላለስ፣              ልቻለሁ ከሀገሬ አይበልጡም፣               እያልኩኝ የምንከላወስ። ዘመን በዘመን ሲቀየር፣ በዓል አውዳመት ሲመጣ፣ ለንጀራ ብዬነውዴ?       ከበርሃ የማልወጣ?        ከዘመድ አዝማድ የማልበላ፣        ከአብሮ አደጎቼ  የማልጠጣ?       የያዘ ይዞኝ  እንጂ፣      የሀገሬ ፍቅር  ሚ ሉት ልክፍት፣     እኔ ሁለት  ሆድ የለኝ፣ እስክሞት  የሚያከራት ተኝ፤ ላቤ በዝቶ በጀርባኤላይ የጨው  አመድ መስሎ   እስኪታይ፣                                 ከእረፍት  እንቅልፍ ተፋትቼ፣           የማጣው  የቅፅበት ፋታ፣            ቀናት በእግሬ  የምኳትን፣           ጫማሄን  ከእግሬ ሳልፈታ። ቀዝቃዛ ውሃ  ነፋሻ አየር ስሙ እንኳንእየናፈቀኝ። ጨዋማ ውሃ እየጠጣሁ በድካም  ጨው የሚያልበኝ።                        ለጀራ ብዬ አይደለም                        ርቄ ከመአል ማዶ                       በቀበሮ ጎድጓድ ሆኝ                       ምሰማው  የወገን መርዶ😢😢                      ለእንጀራኤ ብዬነውዴ                    በህእቴ ሰርግ የማልገኘው                     በወንድሜ ደስታ የማልመጣ።                   ከሀገሬ  አስተሳስሮኝጂ                   ወጥ አቶ አደር የመሆኔ እጣ፡                 ለጀራኤ ብዬ አይደለም                           የምቃጠል  በበረሀ፡               የሚያነደኝ   ቦንብ ፈንጂ።       ቃልኪዳን   ከሆነችው። ከሀገሬ  ፍቅር   ይዞኝእንጂ     ኢ 🇪🇹ት🇪🇹ዮ🇪🇹ጵ 🇪🇹ያ 🇪🇹 ዬ ኢ 🇪🇹ት🇪🇹ዮ🇪🇹ጵ 🇪🇹ያ 🇪🇹 ዬ ኢ 🇪🇹ት🇪🇹ዮ🇪🇹ጵ 🇪🇹ያ 🇪🇹 ዬ ኢ 🇪🇹ት🇪🇹ዮ🇪🇹ጵ 🇪🇹ያ 🇪🇹 ዬ በሳምሶን

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሀምሌ16 ቀን 2015 ዓ.ም         "የጓዳዊነትና ጓደኝነት ዝንቅ በእኛ ቤት" በተለያዩ የሞያ መስኮች ከእኛ ከወታደሮቹ ቤት ውጭ ማለቴ ነው.. የሞያ ባልደረባዊ ጉድኝት ላይ ህጸጾች ሲነገሩ እሰማለሁ። በተለይ በስራ ህይወት የማያቋርጡ የተለያዩ የዕድገት፣ የሽልማት፣ሌሎች ጥቅማ ጥቅሞች አሉና፤እነዚህ ጥበባዊና መርህ መር የተግባቦት አውድ ካልተፈጠረላቸው ማሻኮታቸው አይቀሬ ይሆናል። እርግጥ ነው እኛ ቤት ጥቅምን የተገነ፣መጠቀምን ያለመ አስተሳሰብና ዕምነት የለም።የእኛ ቤት ለሌሎች በመኖር በነፍስ ክፍያ በሚደመደም ከራስ ግላዊ ፍላጎት የተቆራረጡ ቆራጦች መኖሪያ ነውና ከሌላው ጋር ለማናፃጸር ከበድ ቢል አይገርምም። እኛ ቤት በጣም ብዙ ነገሮች የራሳቸው የተለየ ቀለም አላቸው። ከውትድርናው ዓለም በህብራዊ ውበት የተንቆጠቆጠው ቤታችን ማዶ ባለው ተለምዷዊ ህይወት ሁላችንም የምናውቀው የጓደኝነትም ሆነ ሌላ ግንኙነቶች በመደበኛነት የሚታወቁ ናቸው። በእኛ በወታደሮቹ  አብሮነታዊ ጉድኝቶቻችን ጓደኝነትም ጓዳዊነትም ተዛንቀው ይገኛሉ።ትርጉማቸውም በእኛ ቤታዊ ልዩ ቀለም ላይ ይመሠረታሉና በዚሁ ቁምነገር ዙሪያ ጥቂት እንባባል። ጓዳዊነት በእኛ ቤት የሞያዊ አንድነታችን ህብር ማጽኛ፣በንጹህ ልብና በቀና አዕምሮ የሚያስተሳስረን የአንድነታችን ፍቅራዊ ጥብቅ ሃረግ ነው። ጓዳዊነት፦ የዕድሜ፣የቅጥር ዘመን፣የማዕረግ፣የክፍል ሌላም ሌላም ልዮነት ሳይገድበው በውትድርና ህይወት ውስጥ መኖር፣ሀገርና ህዝብን በማገልገል ሂደት ውስጥ መገኘት የሚያቀዳጀን ቁርኝት ነው። በክፍላችንም ከክፍላችን ውጪም የትም ሆነ የት ወታደር ከሆነ ጋር ሁሉ በዓይን ጥቅሻ የምንግባባበት ልዩ ጉድኝት። በጓዳዊ ጉድኝት ውስጥ ጥብቅ መርህ አለ።መርሁ "ምንድነው" ካላችሁኝ? 'ከይሉኝታ፣ከተራ መሸነጋገልና ማስመሰል የራቀና ስህተትን በመተራረም ኮስታራ ዑደት ላይ የተመሰረተ እና በጣም ልዩ መሆኑ።'እላችሁለሁ። ከውትድርናው ዓለም ቤታችን ውጭ የጓዳዊነትን ዓይነት በፍጹም ግልጸኝነት ላይ የተመሰረተ፤"ይህን ብለው ምን ይለኝ? ምንስ ይሰማው ይሆን?"ከሚል ፈራ ተባዊ ጥርጣሬ የተላቀቀ ፍጹም ጤናማ የሆነ ጉድኝት ማግኘት ይከብዳል ባይ ነኝ። በዚህ ጓዳዊነት ይሉት የእኛ ቤት ጉድኝት ብዙ አስገራሚ ገጠመኞችን ማንሳት ይቻላል።የዛሬው ጭውውታችን የእኛን ጓዳዊነትና ጓደኝነት ዝንቅ እውነታ በጨረፍታ ማሳየት ስለሆነ ሌላ ጊዜ በገጠመኞቹ እንመለስበታለን። ስናጠቃልለው ጓዳዊነት በእኛ፤ የውትድርናን ህይወት እስከተጋራን በየትኛውም ቦታና ሁኔታ ተዋወቅንም አልተዋወቅን አንዱ ስህተት ፈጥሮ ሲገኝ ሌላኛው የማረም ግዴታውን እየተወጣ ሞያዊ ክብርን አስጠብቆ ማዝለቅ የሚያስችል ግሩም የእኛ ቤት የጉድኝት ዘይቤ እንደሆነ የቀጠለ የህይወታችን አካል ነው። ሌላኛው በግላዊ ምርጫ  እንደማንኛውም ሰው የምንፈጥረው ጓደኝነት ነው።የሚገርመው በእኛ ቤት ይህ በግል ምርጫ የምንመሰርተው ጓደኝነትም የራሱ የሆነ የተለየ ቀለም ያለው መሆኑ ነው። ከእኛ ወታደሮቹ ቤት ውጭ ያለው ጓደኝነት ብዙ ገደቦች አሉት።አንዱና ዋነኛው በውጭኛው አለም ምን የቅርብ ቅርብ ጓደኛሞች ቢኮን በተለየ አጋጣሚ ካልሆነ በስተቀር የየራስ ህይወትና ኑሮ ስለሚኖሩ የእኛን የተለየ እንዲሆን ያደርገዋል። የእኛ ቤት ጓደኝነት በአንድ ቤት እየተኖረ፣አንድ አይነት ምግብ እየተበላ፣በአንድ ዓይነት ሁለንተናዊ መስተጋብር የሚከወን ዘውትራዊ ተመሳስሎ ያለው ነው። ታዲያ ወዳጆቼ! በእኛ ቤት ጓደኝነት ምንም እንኳን በግል ነጻ ፈቃድ ላይ ተመስርቶ ቢፈጠርም፤ከሞያዊ መርህ ውልፊት ሊል አይገባውም። በዚህ ቀልድ የለም።በጓደኝነት ግላዊ ጉድኝት ውስጥ ነጻነቱ እንደተጠበቀ ሆኖ፤በስመ-ጓደኝነት አንዱ የአንዱን ስህተት ባለማረም "እከከኝ ልከክልህ" ይሉት ያልተገባ መልክን ካበጀ፤ ይህ ጓደኝነት ጥያቄ ውስጥ ይወድቃል።እንዲህ ያለው ጓደኝነት "ርካሽ" ተብሎም በጓዶች ጓዳዊነት መርህ ይፈረጃል። የእኛ ቤት እንዲህ ነው።መኖራችን ሁሉ ከግላዊነት የወጣ፣ማንኛውም ፍላጎታችን ከቆምንለት ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊያንን ከመጠበቅ ቁርጠኛ ዓላማችን በታች የሆነ ነው። ሁሌም ድንቅ የሚለኝ የእኛን ቤት ህይወት ያጣጣመ ማንኛውም ወታደር ከአገልግሎት በሁዋላ በየትኛውም ህይወትና ሞያዊ መስክ ቢሰማራ፤የኖረበትን የውትድርና ቤት 'የጓዳዊነትንና የጓደኝነትን ዝንቅ ቃና' ፈጽሞ መርሳት አለመቻሉ ነው። ምን ስኬታማና የተመቸ አኗኗር መስርቶ ቢኖርም፤የኖረበት የውትድርና ቤቱ በፍቅርና በደስታ ያጣጣመውን በፍፁም ግልጸኝነት የተመሠረተ ጓዳዊነትም ሆነ ጓደኝነት አይረሴ 'ትዝታው' ሆኖበት፤ጣፋጭ ጣዕሙን ሁሌም ይናፍቀዋል። በእርግጥም በፍጹም ግልጸኝነት የሚመሰረት ጉድኝት ከወዴት ይኖራል ብትሉኝ? በልበ-ሙሉነት "እኛ ወታደሮች ቤት" እላችሁዋለሁ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 08 ቀን 2015 ዓ.ም              "አሳምሮ ይገባኛል!!" በዜግነታዊ ዕምነት ሀገር መውደድ፣ስለ ሀገር መልካምን ሁሉ መሻት መፈለግ መመኘት ተገቢም ተጠባቂም የሆነ ሰናይ ሃሳብ ነው። ነገር ግን የሆነ እንከን ብቅ ባለ ቁጥር የዳር ተመልካች በመሆንና እንደ ጲላጦስ እራስን "ከደሙ ንጹህ" ባደረገ ምልከታ ከሳሽና ወቃሽ ሆኖ መገኘት ሀገርን ከመውደድ ጋር ተቆራኝቶ  መታየት አለበት ብዬ አላምንም። እንኳንና ሀገር የመሰለ ግዙፍና ግኑን ሀሳብ በማህበራዊ ግላዊ የአኗኗር ዘይቤያችን እኮ በዙሪያችን ያሉ አብዝተን የምንወዳቸው ሰዎችን ስናስብ፤ፍጹም ህጸጽ አልባና ፍጹም ስለሆኑ አይደለም። ይህንን ከጓደኝነት፣ከፍቅር ጥምረት፣ከትዳር አጋር፣ከልጅ ወዘተ..አያይዘን ለመመልከት ብንሞክር በየዕለት ግንኙነታችን የሚከሰቱ የፍላጎት፣የነገሮች አተያይ፣ሌላም ሌላም ምክንያቶች የሚወልዷቸው ግጭቶች ይከሰታሉ። ታዲያ በየተከሰቱ ግጭቶች ሁሉ እስከ መጨረሻው በሚዘልቅ ስሜታዊነት በሚፈጥራቸው፣ንዴት በሚከስታቸው፣እራስን ብቻ "ትክክል ነኝ" በሚል እቡይነት ህይወታችንን ብንመራ በዙሪያችን አንድም ሰው ሊኖር አይችልም። ሰዎች ነንና ትዕግስት በሚያላብስ አስተውሎት፣ህጸጽን በሚያርም ብስለት፣አዕምሯችን በሚያቀብለን ለአብሮነት በሚጠቅሙ በጎ ሀሳቦችን በመጠቀም መተካከም ስለምንችል ነው በዙሪያችን የሚኖሩ ግላዊ ጉድኝቶቻችንን መጠበቅ እና ማዝለቅ የቻልነው። ወደገዘፈው የሀገር ሃሳብ ስንመጣ ታዲያ ግላዊ ማህበራዊ መስተጋብራችንን ጤናማ እንዲሆን ከምንጠቀመው ዕውቀት፣ጥበብ አርቆ አሳቢነትና መልካምነት ስለ ሀገር ሲሆን አልቀን መጠቀም ግድ ይለናል። ታዲያ በማህበራዊ ሚዲያዎች ከግላዊ ፍላጎት ባልተላቀቀ ፣ጥላቻ ወለድና  ከእውነተኛነት ጋር በእጅጉ የተራራቁ አሉባልታ ነዢዎች በጽሁፎቻቸው፣ በንግግራቸው እርስ በርስ የሚያባላ፣ሰላምን የሚነሳ፣ አንዱን ቅዱስ ሌላኛውን ዲያቢሎስ በሚያደርግ የሰው ልጅ ለሆነ ሁሉ የማይበጁ ግልብና ፍቅርን አብሮነትን የገፉ ክፉ ሃሳቦችን የሚያራምዱ አካላት መነሻቸው ሀገር ወዳድነት ነው ሊባል ይችላል? አልፈው ተርፈው የሀገር ምልክት፣የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የሀገር ብሄራዊ ጥቅም ማረጋገጫ የሆነውን የመከላከያ ተቋም ማንጓጠጥ፣በሴራ ሽረባ የሀሰት አቧራ ማቡለል "ኢትዮጵያን ከሚል" የትኛውም ዜጋ ይጠበቃል? እኔ የኢትዮጵያ ወጥቶ-አደር አሳምሮ ይገባኛል።ለሀገሬ በጽናት የቆምኩ ነኝና የትኛውም በቀቀናዊ ጥላቻ ወለድ የሀሰት አቧራ በቀላሉ የሚያፍነኝ አይደለሁም። እናም ለኢትዮጵያዬ ህልውና በነፍስ ዋጋ ክፍያ ባላንጣዎቿን ስፋለም ከግል ፍላጎቶቼ መሟላት ጋር ተያይዞ ሳይሆን፤ሀገሬን ከነህመሟ ስለምወድ ስለማፈቅራት ነው።       "ክብር ስለኢትዮጵያ ተዋዳቂው ወታደር"

አሜሪካ ለዩክሬን ክላስተር ቦንብ መላኳ ተገለጸ አሜሪካ ለዩክሬን ከ120 በላይ አገራት የተከለከለውን ክላስተር ቦንብ መላኳ ተገለጸ፡፡ አሜሪካ ከሰሞኑ ክላስተር ቦንብ ለዩክሬን ለመስጠት እንደምትፈልግ
አሜሪካ ለዩክሬን ክላስተር ቦንብ መላኳ ተገለጸ አሜሪካ ለዩክሬን ከ120 በላይ አገራት የተከለከለውን ክላስተር ቦንብ   መላኳ ተገለጸ፡፡ አሜሪካ ከሰሞኑ ክላስተር ቦንብ ለዩክሬን ለመስጠት እንደምትፈልግ መግለጿን ተከትሎ ዓለም አቀፍ ተቃውሞዎች በርትተው የነበረ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት የጦር መሳሪያው ዩክሬን እጅ መግባቱ ተነግሯል፡፡ የዩክሬን ባለስልጣናት ክላስተር ቦንቡን የምንጠቀመው የጠላት ጦር በተከማቸባቸው ውስን አካባቢዎች እንደሆነ አስታውቀዋል፡፡ የደቡባዊ ዩክሬን ጦር ቃል አቀባይ ቫለሪን ሸርሸን መሳሪያዎቹን በሩሲያ ግዛት ውስጥ አንደማይጠቀሙ ገልጸው ነገር ግን  የሩሲያ ጦር በብዛት የተከማቸባቸውን ቦታዎች ምሽግ ለመስበር ጥቅም ላይ ይውላሉ ብለዋል፡፡ ሩሲያ በበኩሏ ክላስተር ቦንቦቹ ጥቅም ላይ የሚውሉ ከሆነ ምላሹ ተመሳሳይ እንደሚሆን ማስጠንቀቋን አልጃዚራ ዘግቧል፡፡ ይህን የአሜሪካን ድጋፍ  ካናዳ፣ ስፔን እና እንግሊዝ የክላስተር ቦምቡ ጥቅም ላይ እንዳይውል የተደረሰውን ዓለም አቀፍ ስምምነት የጣሰ ነው በሚል ተቃውመውታል፡፡ ክላስተር ቦንብ በአየር የሚጣል ወይም ከመሬት የሚተኮስ ፈንጂ ሲሆን አንዱ ቦንብ በውስጡ በርካታ ትናንሽ ቦንቦችን የያዘ አደገኛ መሳሪያ ነው፡፡ ክለስተር ቦንቡ ሲተኮስ ትናንሾቹ ቦንቦች ከተያዙበት ተተኳሽ በመውጣት በሰፊ መሬት ላይ ተሰራጭተው የአንድ የእግር ኳስ ሜዳ ስፋት ባለው መሬት ላይ ያለን ኢላማ የማውደም አቅም እንዳላቸውም ተመላክቷል፡፡

ሰላም እንዴት አደራችሁ የቻናላችን ቤተሰቦች🌤 ዛሬ አዲስ ቀን ነው ፤ ያሰባችሁት ፣ ያቀዳችሁት የሚሰምርበት የተዋበ ቀን ይሁንላችሁ ! ከዚህ ሰዓት ጀምሮ መረጃዎችን ወደ እናንተ ማድረስ አንጀምራለን
ሰላም እንዴት አደራችሁ የቻናላችን ቤተሰቦች🌤 ዛሬ አዲስ ቀን ነው ፤ ያሰባችሁት ፣ ያቀዳችሁት የሚሰምርበት የተዋበ ቀን ይሁንላችሁ ! ከዚህ ሰዓት ጀምሮ  መረጃዎችን ወደ እናንተ ማድረስ አንጀምራለን ! ሰላም ለእናት ሀገር ኢትዮጵያ 💚💛❤️ የሚገርም ጁምዓ ተመኘሁላችሁ....🙌

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ2026ቱ የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ለማለፍ በምድብ ማጣሪያው የሚገጥማቸው ሀገራት ይፋ ሆነዋል *********************** በኮትዲቫሯ መዲና አቢጃን ዛሬ ይፋ በሆነ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ2026ቱ የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ለማለፍ በምድብ ማጣሪያው የሚገጥማቸው ሀገራት ይፋ ሆነዋል *********************** በኮትዲቫሯ መዲና አቢጃን  ዛሬ ይፋ  በሆነው ድልድል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በምድብ አንድ ከግብፅ፣ ቡርኪና ፋሶ፣ ጊኒ ቢሳዎ፣ ሴራሊዮን እና ጂቡቲ ጋር ተደልድሏል። በምድብ ሁለት ናይጄሪያ እና ደቡብ አፍሪካ የሚገኙት ድልድል በአመዛኙ ጠንካራው ምድብ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል። 54 የአፍሪካ ሀገራት በ9 ምድቦች ውስጥ የማጣሪያ ጨወታቸውን የሚያደርጉ ሲሆን ከየምድባቸው ቀዳሚ ሆነው የሚያጠናቅቁ 9 ሀገራት 48 ብሔራዊ ቡድኖች ለመጀመሪያ ጊዜ በሚሳተፉበት የአሜሪካ፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ የጣምራ አዘጋጅት የዓለም ዋንጫ ላይ በቀጥታ የሚያልፉ ይሆናል። በሰለሞን አባቡ

የግብጽ እና የኢትዮጵያ መሪዎች በሱዳኑ ግጭት እና በህዳሴ ግድብ ዙሪያ መነጋገራቸዉ ተገለጸ፡፡ የግብጹ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አል-ሲሲ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ በሱዳን ስላለዉ ግጭት እና
የግብጽ እና የኢትዮጵያ መሪዎች በሱዳኑ ግጭት እና በህዳሴ ግድብ ዙሪያ መነጋገራቸዉ ተገለጸ፡፡ የግብጹ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አል-ሲሲ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ በሱዳን ስላለዉ ግጭት እና በህዳሴ ግድብ ዙሪያ በካይሮ መነጋገራቸዉን አናዶሉ ዘግቧል፡፡ የሁለቱ አገራት መሪዎች ዉይይት የሱዳን የጎረቤት አገራት መሪዎች በሱዳኑ ግጭት መፍትሄ ዙሪያ ከሚያደርጉት ጉባኤ በፊት የተደረገ መሆኑንም የዜና ወኪሉ አክሎ ጠቅሷል፡፡ በግብጽ ፕሬዝዳንት በኩል የወጣ መግለጫ እንደሚያሳየዉ ሁለቱ መሪዎች በሱዳን ያለዉን ግጭት ማቆም በሚቻልበት ሁኔታ ዙሪያ ፣ የሁለትዮሽ ግንኙነትን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ እና በታላቁ የህዳሴ ግድብ ዙሪያ መነጋገራቸዉን ያሳያል፡፡ ግብጽ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ከአባይ ወንዝ ከምታገኘዉ የዉሃ መጠን አብላጫዉን ድርሻ ይወስዳል በሚል እንደ ቋሚ ስጋት የምትቆጥረዉ ሲሆን፣  በግድቡ አሞላል እና አሰራር ዙሪያ አሳሪ ስምምነት እንዲኖር ትፈልጋለች፡፡ ኢትዮጵያ በበኩሏ ግድቡ ለምታደርገዉ የዕድገት ጉዞ ወሳኝ መንገድ መሆኑን በማንሳት ፣ የታችኛዉ ተፋሰስ አገራት የሆኑትን ግብጽን እና ሱዳንን የዉሃ ድርሻ በምንም ዓይነት መልኩ እንደማይጎዳ ትገልጻለች ሲል ዜና ወኪሉ አክሏል፡፡ ለዓመታት በግድቡ አሞላል እና አሰራር ዙሪያ ሲደረግ የነበረዉ ዉይይት መፍትሄ ማምጣት አለመቻሉንም ገልጿል፡፡ ዕሮብ ዕለት ጠቅላይ ሚኒስቴር ዐብይ አህመድ የሱዳን የጎረቤት አገራት መሪዎች ጉባኤን የሚሳተፉ የኢትዮጵያ ልኡካንን መርተዉ ወደ ግብጽ ሄደዋል፡፡ ሱዳን በፈጥኖ ደራሽ ሃይሉ እና በመንግስት ጦር መካከል ከሚያዚያ ጀምሮ በተፈጠረ ግጭት እስካሁን 3ሺህ ንጹሃን የተገደሉ ሲሆን በሺዎች የሚቆጠሩ ደግሞ መጎዳታቸዉ የአናዶሉ ኤጀንሲ ዘገባ ያመለክታል፡፡ በእስከዳር ግርማ ሐምሌ 06 ቀን 2015 ዓ.ም

Federal Defense Forces July 5, 2015 The construction of the Airborne Training School which is being built is nearing completion, the battalion engineer said. The head of the project, Major Engineer Likadu, stated that the construction of the Airborne Training School under construction at Bischoftu has been completed 99%. It is stated that the construction of the training school, which was started near the former Airborne School by the Defense Engineer Chief Department on March 24, 2013, with a budget of 170 million birr, will be completed soon. The school has various offices, student classrooms, medical clinic, hall, recreational club, housing for students and leaders and coaches at all levels, and it is built in a convenient way for theoretical and practical lessons in the field. Ethiopian Roads Authority is also carrying out internal asphalt road work. In addition to the construction of the Airborne Training School, the two main entrance doors and the patient waiting area of ​​the Defense Specialized Referral Hospital in Bischoftu have also been constructed, the head of the project said. The head of construction of the project, Shambel Engineer Teka Jamal, said that they have worked with determination from the top management to the lower staff to complete the construction. A project is said to be effective when it is completed with the required quality level in the allocated budget, he said. Lt. Col. Haile Gabriel, who joined the Air Force in 1959 and is still sharing his military knowledge, said that he was lucky to see a modern Air Force Training School built during my lifetime. Abdu Shemsun and Tilahun Shambel, among the workers, said that they have gained additional skills in addition to benefiting their families with the income they earn from working in the project. Information is life, join us by sharing this information with your friends 👉Join the Telegram channel to get important information quickly 👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/CommandoAndAirborneCommand Subscribe us 👇 https://www.youtube.com/@theredtigers_4034

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 05 ቀን 2015 ዓ.ም እየተገነባ የሚገኘው የአየር ወለድ ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ግንባታ በመጠናቀቅ ላይ መሆኑን ሻለቃ ኢንጂነር ፍቃዱ ያዘው ገለፁ። በቢሾፍቱ  በመገንባት ላይ የሚገኘው የአየር ወለድ ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ግንባታ 99% መጠናቀቁን የገለፁት የፕሮጀክቱ ኃላፊ ሻለቃ ኢንጂነር ፍቃዱ ያዘው ናቸው። በቀድሞው የአየር ወለድ ትምህርት ቤት አቅራቢያ በመከላከያ መሐንዲስ ዋና መምሪያ መጋቢት 24 ቀን 2013 ዓ.ም 170 ሚሊየን ብር በጀት ተይዞለት  ግንባታው የተጀመረው ማሠልጠኛ ትምህርት ቤት በቅርቡ እንደሚመረቅም ተገልጿል። ትምህርት ቤቱ  የተለያዩ ቢሮዎችን ፣የተማሪዎች መማሪያ ክፍሎችን ፣የህክምና መስጫ ክሊኒክ ፣አዳራሽ ፣መዝናኛ ክበብ፣ የተማሪዎችና  በየደረጃው ላሉ አመራሮች እና አሰልጣኞች መኖሪያ በአጠቃላይ በንድፈ-ሀሳብና በተግባር  በመስክም ጭምር ለሚሰጡ ትምህርቶች  ምቹ ተደርጎ የተገነባ  ከመሆኑም በላይ 5 ኪሎ ሜትር  ዙሪያውን በግንብ የታጠረ ነው። በኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የውስጥ ለውስጥ የአስፓልት መንገድ ስራም በመከናወን ላይ ይገኛል። ከአየር ወለድ ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ግንባታ በተጨማሪ ቢሾፍቱ የሚገኘው የመከላከያ ስፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታል ሁለት  ዋና መግቢያ  በሮችና የህሙማን ማቆያ ቦታ ግንባታዎችም መከናወናቸውን የፕሮጀክቱ ኃላፊ ገልፀዋል። ግንባታውን ለማጠናቀቅ ከበላይ አመራር እስከታችኛው ሰራተኛ ድረስ በቁርጠኝነት መስራታቸውን የገለፁት ደግሞ የፕሮጀክቱ ኮንስትራሽን ኃላፊ ሻምበል ኢንጂነር ተካ  ጀማል ናቸው። አንድ ፕሮጀክት ውጤታማ ነው የሚባለው በተመደበለት በጀት በተያዘለት መርሀ-ግብርና በተፈለገው ጥራት ደረጃ ሲጠናቀቅ ነው ያሉት ሻምበል ኢንጂነር ተካ ከዚህ አንፃር ሲገመገም ምርጥ አፈፃፀም ላይ ይገኛል ብለዋል። በ1959  ዓ/ም አየር ወለድን የተቀላቀሉትና  አሁንም ወታደራዊ ዕውቀታቸውን በማካፈል ላይ የሚገኙት ሌተናል ኮሎኔል ደስታ ኃይለ ገብርኤል በህይወት እያለሁ የዘመነ አየር ወለድ  ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ተገንብቶ በማየቴ እድለኛ ነኝ ብለዋል። ከሰራተኞች መካከል አብዱ ሸምሱና ጥላሁን ሻምበል  በፕሮጀክቱ ተቀጥረው በመስራታቸው በሚያገኙት ገቢ ቤተሰቦቻቸውን ከመጥቀም ባለፈ ተጨማሪ ሙያዎችን ማግኘታቸውን ተናግረዋል።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 27 ቀን 2015 ዓ.ም የመሠጠት ጥግ የአገልጋይነት ልክ አፍላ የወጣትነትን ጊዜ፣ ለአንዴ ብቻ የሚኖሯት ውድ ህይወትን ወዶና ፈቅዶ ለሀገር መሥጠት የሚቻለው ወታደር ሲ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 27 ቀን 2015 ዓ.ም        የመሠጠት ጥግ የአገልጋይነት ልክ አፍላ የወጣትነትን ጊዜ፣ ለአንዴ ብቻ የሚኖሯት ውድ ህይወትን ወዶና ፈቅዶ ለሀገር መሥጠት የሚቻለው ወታደር ሲኮን፤ ከራስ በላይ በህዝብና ሀገር ከፍታ ማመን ሲቻል ነው። የአካሌ መጎደል የሀገር ስብራት ይጠግናል ፤የደሜ መፍሰስ የወገንን እንባ ያብሳል፤ የኔ ድካም የሀገረ መንግስት ጥንካሬ ይሆናል ፤ብሎ ለመሳብ ሰው መሆን ብቻ አይበቃም። በውትድርና ህይወት ከመከላከያ አብራክ እንደገና መወለድንና ማደግን ይጠይቃል። ላብ ደምን እንደሚያድን ጠንቅቆ የሚያውቅ ፤ይሄን ዕውቀቱን ወደ እምነት መቀየር በሁሉም የአየር ፀባያት፤ የመሬት ገፆች፤ በቀንና ሌሊት መሠልጠን የሚቻለው ሀገርን መረዳት በውትድርና ሙያ እሳቤ በወታደራዊ እምነትና አስተሳሰብ መሟላት ሲቻል ብቻ ነው። ከወላጅ እናት፣ ከሚያፈቅሯት ሚስት ፣ከሚያሳሱ የወላዷቸው እንቦቃቅላ ህፃናት ለበርካታ ጊዜያት መለየት፤ በበዓላት፣ ደስታና ሐዘን ከወዳጅ ዘመድ መሀል አለመገኘት የውትድርና ህይወት መረር እውነት ነው። የራሱ መጉደል የታላቅ ሀገርና ሚሊዮን ህዝቦቿ ሙላት እስከሆነ ድረስ ለሌላው የሚያስገርመውን የሚያመውን ያህል ለወታደር አያስገርመውም አያመውም። ወታደርነት የመሠጠት ጥግ ነው። የአፍቃሪነት ትልቅ አብነት የቁርጠኝነት አናት፤ የፅናት ከፍታ ጫፍ ፤የአገልጋይነት መንፈስ የመጨረሻ ማሳያ ሙያ ነው።  የመሠጠት ልክ የአገልጋይነት ጫፍ ነው ወታደርነት። በፈይሳ ናኔቻ

    ስለ ኢትዮጵያ ወታደሮች ከአሜሪካ ወታደሮች!! ከምንም ነገር በፊት ሁሉም ሰው ሁሉም ኢትዮጵያዊ እንደሚለው ኢትዮጵያዊነት ኩራት ነው፤ ሚስጥር ነው፡፡ “ኢትዮጵያዊነት በ5 አምዶች የታነፀ መኖሪያ እልፍኝ ነው፡፡ ጥልቅና ሰፊ ዕውቀት ፣ መዛል የሌለበት ትጋት ፣ በትዕግስት የታሸ ጀግንነት ፣ ርኩሰት የሌለበት ቅድስና ፣ ግብዝነት የሌለበት ሚስጢራዊ ህይወት ማለት ነው ኢትዮጵያዊነት፡፡” ኢትዮጵያን ለመውረር የመጣ ማንኛውም የውጪ ሀገር ባንዳ  ጀግኖች ኢትዮጵያዊያን እንዴት እንደመለሱት  ታሪክ ለማወቅ ብዙ ማንበብ እና መረጃ ለመሰብሰብ  መኳተን አይሻም፡፡ ምክንያቱም አበው ፋሽስት ኢጣልያ ሀገራችንን ለመውረር ሲመጣ በአንድ ጊዜ በመውጣት ለጦርነት ሳይሆን ለሠርግ ጥሪ የሚሄዱ የሚመስል ጀግና ህዝብ መሆኑን ይህ ብቻ ሳይሆን  ዚያድ ባሬ ኢትዮጵያን ለመውረር በምስራቅ በኩል ሲመጣ ካራማራ ላይ የተፈፀመው ኢትዮጵያዊ ጀግነት በወቅቱ አለምን ጉድ ያሰኘ እንደነበረ ማወቅ በቂ ነው፡፡ ሰሞኑን በሶማሊያ ኪስማዩ ልዩ ተልዕኮ የሚፈፅሙት የአሜሪካ ወታደሮች ከኢትዮጵያ 7ኛ ሞተራይዝድ ሠላም አስከባሪ ሻለቃ አመራሮች ጋር በወቅታዊ የፀጥታ ጉዳይ ዙሪያ ውይይት አድርገዋል። በዚህ የውይይት መድረክ ላይ በኪስማዩ የሚገኙት የአሜሪካ ወታደሮች አስተባባሪ ሻምበል ሄረን ኤቨን ስለ ኢትዮጵያ ወታደሮች  ጀግንነት እና አሸናፊነት እንዲህ ሲል ገልጿል።  የቀደሙት የኢትዮጵያ ወታደሮች ጀግና መሆናቸውን እኔ በዕድሜ ባልደርስበትም ከተለያዩ መፅሃፍቶች እና ከታላላቅ ሠዎች አንደበት ሠምቻለሁ አድዋ  ተራራ ላይ ኢጣሊያንን በኋላ ቀር መሳሪያ ድል ማድረጋቸውን እንዲሁም በካራማራ ደግሞ  የዚያድ ባሬን ጦር  የመለሰ የማይደፈር  እና ጀግና ሠራዊት እንደነበር አውቃለሁ ። አሁኑም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት እንደ ቀደሙት አባቶቹ ጀግንነቱን እና አልበገር ባይነቱን በተለያዩ የሶማሊያ ቦታዎች በተንቀሳቀስኩበት ስፍራዎች በአይኔ በብረቱ ማረጋገጥ ችያለሁ የቅርቡን እንኳን ለአብነት ብናነሳ በዶሎ አልሸባብ ላይ የፈፀሙት ጀግንነት ሁነኛ ምስክር መሆን ይችላል። ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ እና በቀጠናው ሠላም ወሳኝ የሆነች ሀገር መሆኗን እኛ የአሜሪካ ወታደሮች በምንፈፅመው የእለት ተእለት ግዳጅ ማረጋገጥ ችለናል። በቀጣይ አልሸባብን ከመላው ሶማሊያ ለማጥፋት እና የተረጋጋች እንዲሁም ሠላም የሰፈነባት ሶማሊያን ለመገንባት የአሜሪካ ወታደሮች እና የኢትዮጵያ ወታደሮች እንዲሁም ከአትሚስ ወታደሮች  በጋር የሚፈፅሙት ግዳጅ ወሳኝ ነው ብለዋል። እዚህ መጥተን በአትሚስ ጥላ ስር ከሚገኘው የኢትዮጵያ 7ኛ ሞተራይዝድ ሠላም አስከባሪ ሻለቃ ጋር በመነጋገራችን እና ስለ ኢትዮጵያ ባህል እና ወግ ስላስተዋወቃችሁን በአሜሪካ ወታደሮች ስም ማመስገን እወዳለሁ ሲሉ ተናግረዋል። የአሁኑም ትውልድ ከአበው በወረሰው በትዕግስት በታሸው ጀግንነት በአሸባሪው የአልሸባብ ቡድን  ላይ እርምጃ እየወሰደ  ጎረቤት ሀገርን ሶማሊያን ሠላምና መረጋጋት የሰፈነባት ሀገር ለማድረግ ከላብ ጠብታ እስከ ህይወት መስዋዕትነት ጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት ዋጋ እየከፈለ ይገኛል።፡ “ኢትዮጵያ በጀግኖች ልጆቿ ታፍራና ተከብራ ትኖራለች ” ከተማ