የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
Kanalga Telegram’da o‘tish
5 082
Obunachilar
-11024 soatlar
-1 9137 kunlar
-2 77030 kunlar
Postlar arxiv
#ተጨማሪመረጃ
አሜሪካ ኢትዮጵያ ከዚህ በኋላ ምንም የፋይናንስ ድጋፍ ክልከላ እንደማይደረግባት ትናንት ምሽት አስታውቃለች!!
የፕሬዝዳንት ጆ ባይደን አስተዳደር በኢትዮጵያ ላይ ያሳለፈውን "የሰብዓዊ መብት ጥሰት" ፍረጃ ማንሳቱን ለኮንግሬሱ እንዳሳወቀ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ሰነድን ጠቅሶ ፎሬይን ፖሊሲ ጋዜጣ ዘግቧል። የባይደን አስተዳደር ውሳኔውን ለኮንግሬሱ ያሳወቀው የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት በቅርቡ ባካሄደው ግምገማ፣ ኢትዮጵያ ተከታታይነት ባለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ውስጥ እየተሳተፈች እንዳልሆነ ድምዳሜ ላይ ደርሷል በማለት መሆኑን ዘገባው ጠቅሷል።
ውሳኔው አሜሪካ በሰሜኑ ጦርነት ሳቢያ ለኢትዮጵያ መስጠት ያቋረጠቻቸውን ዕርዳታዎች እንደገና እንድትቀጥል በር የሚከፍት እንደነምነ ተነግሯልል። ለሀገሪቱ ኮንግረስ የተላከው ይህ የውስጥ ማስታወሻ አሜሪካ ይህንን ክስ በማንሳቷ ከዚህ በኋላ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ ኢትዮጵያ ከዋሽንግተንም ሆነ ከሌሎች ዓለም አቀፍ አበዳሪዎች ገንዘብ እንዳታገኝ ሲያደርግ የነበረውን መከላከል እንደሚያቆም ያመላክታል።
የአሜሪካ ውሳኔ ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይ ኤም ኤፍ) እና ከዓለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍና ብድር እንድታገኝ የሚያስችል እንደሆነም ተመላክቷል። ውሳኔው አሜሪካ በሰሜኑ ጦርነት ወቅት የሻከረውን የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ለማደስ ፍላጎት እንዳላት ያሳያልም ነው የተባለው።
👉አጫጭር የዝውውር መረጃዎች
⚽️ፖርቱጋላዊው የሊቨርፑል አማካይ ፋቢዮ ካርቫልሆ በአንድ አመት የውሰት ውል የቡንደስሊጋውን ክለብ አርቢ ሌይፕዚግ ተቀላቅሏል።
⚽️ኔዘርላንዳዊው የአያክስ አምስተርዳም ተከላካይ ጁሪየን ቲምበር በ36.2 ሚሊየን ፓወንድ አርሰናልን ለመቀላቀል መስማማቱን ተከትሎ በቀጣይ ቀናት የህክምና ምርመራውን እንደሚያደርግ ይፋ ተደርጓል።
⚽️አስቶን ቪላ በ35 ሚሊየን ፓወንድ ስፔናዊውን የ26 አመት ተከላካይ ፓኦ ቶሬስ ከቪላሪያል ለማስፈረም መስማማቱ ተገልጿል።
⚽️ቼልሲ ኢኳዶሪያዊውን አማካይ ሞይሰስ ካይሴዶ ከብራይተን ሆቭ አልቢየን ለማስፈረም የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ መቀጠሉ ታውቋል።
⚽️ኤሲ ሚላን አሜሪካዊውን ኢንተርናሽናል ክርስቲያን ፑልሲች ከቼልሲ ለማስፈረም እንቅስቃሴ መጀመሩ ተነግሯል።ሮሰነሪዎቹ ቀደም ብሎ ከምዕራብ ለንደኑ ክለብ ሩበን ሎፍተስ ቺክን ማስፈረማቸው ይታወሳል።
⚽️ፓብሎ ማሪ በሰባት ሚሊየን ዩሮ በቋሚ ዝውውር አርሰናልን በመልቀቅ የሴሪ አው ተሳታፊ ክለብ ሞንዛ ንብረት ሆኗል።
።
⚽️ፓሪስ ሴንት ዠርመንን ለማሰልጠን የተስማማው ስፔናዊ አሰልጣኝ ልዊስ ኤነሪኬ የማንቺስተር ሲቲውን አማካይ በርናንዶ ሲልቫ የማስፈረም ፍላጎት አለው ተብሏል።
⚽️ሴኔጋላዊው አጥቂ ኒኮላስ ጃክሰን በስምንት አመት የኮንትራት ውል ቪላሪያልን በመልቀቅ ቼልሲን ተቀላቅሏል።
።
⚽️የቼልሲው ስፔናዊው የቀኝ ተከላካይ ሴዛር አዝፔልኩዌታ በነጻ ዝውውር አትሌቲኮ ማድሪድን ለመቀላቀል ተስማምቷል።
⚽️የሮማው አሰልጣኝ ጆዜ ሞውሪንሆ ከቀድሞ ክለባቸው ማንቺስተር ዩናይትድ ብራዚላዊውን አማካይ ፍሬድ የማስፈረም ፍላጎት እንዳላቸው ይፋ ተደርጓል።
⚽️ፓትሪክ ቪዬራ የፍሬንች ሊግ ዋን ተሳታፊውን ክለብ ስትራስቡርግ ለማሰልጣን ተስማምቷል።
መረጃ ህይወት ነው፣ ይህንንም መረጃ ለጓደኞቻችሁ#Share በማድረግ ተባበሩን🙏
👉ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ
👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/CommandoAndAirborneCommand
ሰብስክራይብ ያድርጉን
👇
https://www.youtube.com/@theredtigers_4034
የኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ በበጀት ዓመቱ ተልዕኮውን በላቀ ብቃት መፈፀሙን አሥታወቀ፡፡
በበጀት አመቱ የኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ የተሠጠውን ተልዕኮ በላቀ ብቃት በመወጣት ከፍተኛ አመኔታ ማትረፉን የዕዙ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ ገልፀዋል፡፡
በበጀት አመቱ የዕዙ የሠራዊት አባላት አስፈላጊውን መስዋዕትነት ሁሉ በመክፈል ግዳጃቸውን በጀግንነት በመፈፀም ህዝባዊ ድጋፍ እና አመኔታን ማትረፋቸውን ተናግረዋል።
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ የሠራዊት አባላት ለየትኛውም የአየር ፀባይ፣ የመሬት አቀማመጥ እና ሁኔታ ሳይበገሩ የሚያጋጥሙ ፈተናዎችን ሁሉ በፍጹም ኢትዮጵያዊ ወኔ አልፈው የተሰጣቸውን ሀገራዊ ተልዕኮ በዲሲፕሊን እና በጀግንነት መወጣት ችለዋል።
እንደ ክፍል ለተመዘገበው ውጤት አመራሩና አባላቱ እንዲሁም አጠቃላይ ድጋፍ ሰጪ ስታፉ ክፍሉ በየሙያ ዘርፉ በመናበብ ያለ ዕረፍት የሰሩት ስራ የውጤቱ ሁነኛ ማሳያ ማሆኑንም አሥረድተዋል።
የኮማንዶ እና አየር ወለድ ማሰልጠኛ ማዕከልም ሃይል በማባዛት እና የክፍሉን የውጊያ አቅም በመገነባት ለውጤታማነቱ እውን መሆን ትልቁን ድርሻ እንደሚወስድ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ አብራርተዋል፡፡
ለሀገሩ ሉአላዊነት እና ለህዝቦች ሰላም ዛሬም እንደትላንቱ የትኛውንም ዋጋ በመክፈል ኢትየጵያን እና ህዝቦቿን ከውስጥ እና ከውጪ ፀረ ሠላም እና ፀረ ልማት ሃይሎች መጠበቅ እንደሚገባም ጄኔራል መኮንኑ አሳስበዋል።
ጽንፈኛው የሸኔ ታጣቂ ቡድኖች ላይ ባለ ቀይ መለዮ ለባሹ ሪፐፕሊካን ጋርድ እየወሰደ ያለው እርምጃ ዛሬም ቀጥሏል:: ምስል 1
ሰበር ዜና ‼️
#EthioAmerican : የአሜሪካን መንግስት በኢትዮጵያ ላይ ጥሎት የነበረውን የሰብአዊ መብት ጥሰት ክሶች ማምሻውን ሙሉ በሙሉ አንስቷል:: ይህንን ተከትሎም ለኢትዮጵያ የተያዘው የልማት ፈንድ እንደሚለቀቅላት ታውቋል።
ኢትዮጵያ ብሪክስን ለመቀላቀል በይፋ ጥያቄ ማቅረቧ ተገለጸ!
ኢትዮጵያ ብሪክስን ለመቀላቀል በይፋ ጥያቄ ማቅረቧን የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር አስታውቋል።የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ የሰጡ ሲሆን፤ በመግለጫቸውም ኢትዮጵያ ጥቅሞቿን ሊያስጠብቁ ከሚችሉ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር መስራቷን ትቀጥላለች ብለዋል።
ኢትዮጵያ በብራዚል፣ ሩሲያ፣ ሕንድ፣ ቻይና እና ደቡብ አፍሪካ የተመሰረተው ብሪክስን ለመቀላቀል በይፋ ጥያቄ ማቅረቧ ተገልጿል።
"ብሪክስ ከኢትዮጵያ ለቀረበለት ጥያቄ አወንታዊ ምላሽ እንደሚሰጠን እንጠብቃለን።" ያሉት አምባሳደር መለስ፤ ከሌሎች ብሔራዊ ጥቅሞችን ሊያስጠብቁ ከሚችሉ ተቋማት ጋር መስራታችንን እንቀጥላለንም ብለዋል።
አባል አገራት ያቀረቡትን የእንቀላቀል ጥያቄ ምላሽ እንደሚሰጥ ተገልጿል።ሳውዲ አረቢያ፣ አረብ ኢምሬትስ፣ ኢራን፣ ቱርክ፣ ግብጽ እና አልጀሪያ ብሪክስን ለመቀላቀል ጥያቄ ካቀረቡ አገራት መካከል ዋነኞቹ ናቸው።
"ለእኔ ሁለመናዬ ናት"
የእናቴ ልክ የልጆቼ መልክ የሁለንተናዬ አብራክ ናት።
የልጅነት መቦረቂያ፣ የወጣትነት መድመቂያ፣ የእርጅና ዘመን መጦሪያዬ ናት። የሥጋ እና መንፈስ ቀለቤ የጨቅላነት ወተት የጉልምስና ጉልበት የእርጅናዬ በረከት እላታለሁ ኢትዮጵያዬን።
መወለድ ማደግ፣ ማግባት መውለድ ፣ማርጀትና መምት ብቻውን ሙሉ ሰው አያደርገኝም። ሙሉ የሆንኩት ስም ኖሮኝ የተጠራሁበት ታሪክ ሠርቼ የምወደስባት እውነት ገድፌ የምወቀስባት እሷ የከፍታዬ ሰገነት የመፋረጃዬ መድረክ ናት።
ባላት አቅም አስተምራ ፣ኩላ ድራ፣ ለወግ ማዕረግ ያበቃችኝ እናቴ ናት። ምን እናት ብቻ የሠርግ አደራሽ የትዳሬ ጎጆ የመቃብር ሥፍራ ጭምር እንጂ።
እሷ የአባቶቼ ልክ የእናቶቼ አብራክ የልጆቼም መልክ ናት። ሠርቼ ብሸለም አጥፍቼ ብቀጣ የሚያምርብኝ፣ ትንፋሿ የሚፈውሰኝ፣ አየሯ የሚያድሰኝ፣ ከፍታዋ የሚያነሳኝ ዝቅታዋ የሚጥለኝ ከአፈር የሚደባልቀኝ ስጦታዬ ናት።
ደላኝ ብዬ የማልረሳት፣ ከፋኝ ብዬ የማልተዋት ማንም የማይሰጠኝ ፣ማንም የማይከለክለኝ ፣የፈጣሪዬ ስጦታ ናት። ስጦታዬ ስላት በገንዘብ የምትተመን ቁስ ፣በማንም የምትተነተን ጉዳይም አይደለችም ሀገሬ።
የትውልዴ ውርስ ፣የማትሸጥ የማትለወጥ ቅርስ ፣የምተነፍሳት አየር ፣የምመገባት ምግብ፣ የምጠጣት ውሃ፣ የምስቃት ሳቅና የማነባት እምባዬ ናት። ስኖርም ንብረት ሳልፍም እኔነቴን የምትሆን የሆነች።
አንደበት ቋንቋዬ ፣እምነት ሐይማኖቴ መሆኗን አውቃለሁ። እሷ ህዝብህ ናት ወገንህ ፣የብስና አየርህ ፣ሐይቅህና ወንዝህ ፣ደምህና ወዝህ እንደሆነች እወቅ የማለኝ መካሪ አልፈልግም። ነፍሴ በአየሯ አፅሜ ከአፈሯ እንዲሆን እመኛለሁ።
ቁጥሬ በሚሊዮኖች የሚቆጠ፣ ተስፋዬ ብርሃናማ የሆነና የማይቀር፣ እቅዴ የሚተገበር ታሪክ አምሮ ተውቦ ዘመናትን የሚሻገር ነው። እኔ ደግሞ ወታደር ነኝ። ወጥቼ አድሬ አቅጄ ተግብሬ የማኖራት ሞቴ ህይወት የሚሆናት ስመ ትልቅ ዓይነተ ብዙ ህብሯ ደማቅ ምስጢሯ ረቂቅ እውነቴ ሐብቴ ንብረቴና ማንነቴ ናት።
ለሠማይና ምድር፣ የብስና አየሯ ለሠላማዊ ውሎና አዳሯ ባህር የምቀዝፍ ፣ በአየር ላይ የምንሳፈፍ ፣በምድር ላይ ቆላ ደጋ ወይናደጋ ፣በረሃ ፣አቀበት ሜዳ ሳልል ለክብሯ የምሰለፍ፣ ለክብሯ በክብር የምሰየፍ አሊያም ታሪክ ሠርቼ ለትውልዴ የኔ የሆነችውን ሀገሬ ኢትዮጵያ ይበልጥ አመቻችቼ የማልፍ ጀግና ነኝ። እኔ ወታደሯ እሷ ደግሞ የእናቴ ልክ የልጆቼ መልክ የሁለንተናዬ አብራክ ናት። ኢትዮጵያ!
ዘጋቢ ፈይሳ ናኔቻ
ከፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል የተገለፀ መረጃ 👇
ለሸኔ የሽብር ቡድን የትጥቅ ድጋፍ ለማድረግ ሲጓዙ የነበሩ ሁለት ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ሥር ማዋሉን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታውቋል።
ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር ሊውሉ የቻሉት ሰኔ 20 ቀን 2015 ዓ.ም መነሻቸውን ከአዲስ አበባ ከተማ ለቡ አድርገው የሠሌዳ ቁጥሩ ኮድ 2-አአ B25609 በሆነ ቶዮታ ኮሮላ መኪና አንድ ብሬን እና 263 የክላሽንኮቭ ጠመንጃ ጥይቶችን ጭነው ሲጓዙ ሆለታ ከተማን እንዳለፉ በፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል በተደረገ ጠንካራ ክትትል መሆኑ ታውቋል።
ተጠርጣሪዎቹ ከህገ-ወጥ የጦር መሣሪያው በተጨማሪ ለእኩይ ዓለማቸው ማስፈፀሚያ ሐሰተኛ የአዲስ አበባ ከተማ የነዋሪ መታወቂያ፣ የልደት ምስክር ወረቀት፣ ልዩ ልዩ ማህተሞች እና ሀሰተኛ ሰነዶችን ይዘዋል። ጉዳያቸውም በምርመራ እየተጣራ እንደሚገኝ የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታውቋል።
ኅብረተሰቡም እነዚህ ህገወጥ መሣሪያዎች በሸኔ የሽብር ቡድን እጅ ቢገቡ ኖሮ በንፁሃን ዜጎቻችን ላይ የሚያደርሱት ከፍተኛ መሆኑን ተገንዝቦ መሰል የወንጀል ተግባራትን ሲመለከት ለፀጥታ አካላት በፍጥነት ጥቆማ በመስጠት እያደረገ ያለውን ተሳትፎ አጠናክሮ እንዲቀጥል የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረኃይል ጥሪ ማቅረቡን ከፌድራል ፖሊስ ገፅ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ለሸኔ የሽብር ቡድን የትጥቅ ድጋፍ ለማድረግ ሲጓዙ ነበር የተባሉ 2 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ዋሉ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ለሸኔ የሽብር ቡድን የትጥቅ ድጋፍ ለማድረግ ሲጓዙ ነበር የተባሉ ሁለት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ማዋሉን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታውቋል።
ተጠርጣሪዎቹ ሰኔ 20 ቀን 2015 ዓ.ም መነሻቸውን ከአዲስ አበባ ከተማ ለቡ አድርገው አንድ ብሬን እና 263 የክላሽንኮቭ ጠመንጃ ጥይቶችን ጭነው ሲጓዙ ሆለታ ከተማን እንዳለፉ ነው በቁጥጥር ሥር የዋሉት፡፡
ተጠርጣሪዎቹ ከህገ-ወጥ የጦር መሣሪያው በተጨማሪ ለእኩይ ዓለማቸው ማስፈፀሚያ ሐሰተኛ የአዲስ አበባ ከተማ የነዋሪ መታወቂያ፣ የልደት ምስክር ወረቀት፣ ልዩ ልዩ ማህተሞች እና ሀሰተኛ ሰነዶችን እንደያዙ በቁጥር ሥር ውለው ጉዳያቸው በምርመራ እየተጣራ እንደሚገኝ ተጠቁሟል፡፡
ተጠርጣዎቹ በፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል በተደረገ ጠንካራ ክትትል በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የፌደራል ፖሊስ መረጃ ያመላክታል፡፡
ኅብረተሰቡም እነዚህ ህገወጥ መሣሪያዎች በሸኔ የሽብር ቡድን እጅ ቢገቡ ኖሮ በንፁሃን ዜጎቻችን ላይ የሚያደርሱት ከፍተኛ መሆኑን ተገንዝቦ መሰል የወንጀል ተግባራትን ሲመለከት ለፀጥታ አካላት በፍጥነት ጥቆማ በመስጠት እያደረገ ያለውን ተሳትፎ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ ቀርቧል፡፡
የፀጥታ እና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል እንኳን ለ1444ኛው ኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፏል
የፀጥታ እና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል እንኳን ለ1444ኛው ኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፏል።
ሙሉ መልዕክቱ እንደሚከተለው ቀርቧል።
የፀጥታ እና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል በዓሉ በመላው ሀገራችን በሰላም እንዲከበር በቂ ዝግጅት አድርጎ ፀጥታ የማስከበር ሥራውን እየሰራ ይገኛል።
በመሆኑም መላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በዓሉ በሰላም እንዲከበር ከፀጥታና ደህንነት አካላት ጎን በመቆም የዜግነት ድርሻችሁን እንድትወጡ ያሳስባል።
አጠራጣሪ ሁኔታዎች ሲያጋጥሙት በ987፣ 991 እና 816 ነፃ የስልክ መስመሮች
እንዲሁም
በስልክ ቁጥር +251 111 11 01 11፣
+251 115 52 63 03፣
+251 115 52 40 77፣
+251 115 54 36 78 እና
+251 115 54 36 81፣
+251 115 54 36 84፣
+251 115 54 38 04፣
+251 115 31 22 08፣
+251 115 31 22 23፣
+251 115 31 22 47፣
+251 115 31 22 20፣
+251 115 31 20 63፣
+251 115 31 20 33፣
+251 115 31 21 31፣
+251 115 31 22 21፣
+251 115 31 20 42፣
+251 115 31 20 05
ጥቆማዎችን በፍጥነት በመስጠት ወይም በአካባቢው ለሚገኙ የፀጥታ ኃይሎች መረጃውን በአካል በማድረስ ትብብራችሁን አጠናክራችሁ እንዲቀጥሉ የጋራ ግብረ ኃይሉ ጥሪውን እያቀረበ በዓሉ የሰላምና የፍቅር እንዲሆንላችሁ መልካም ምኞቱን ይገልፃል።
ዒድ ሙባረክ!
የፀጥታ እና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል
ሰኔ 20 ቀን 2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የሰራዊቱን 320ሺ ብር ይዞ የጠፋው እየተፈለገ ነው
ከይርጋ ጨፌ መከላከያን የተቀላቀለዉ ተፈላጊ ተመስገን ጴጥሮስ ተይዞ ለህግ እንዲቀርብ የህብረተሰቡ ትብብር ተጠይቋል።
ተፈላጊ ተመስገን ጴጥሮስ ጎበና በኮማንዶ አየር ወለድ እዝ 103ኛ ክፍለጦር የ4ኛ ኮማንዶ ሬጅመንት የፋይናንስ ሰራተኛ ሆኖ ሲሰራ የክፍሉ አባላት ግዳጅ ላይ መሆናቸዉ እንደምቹ አጋጣሚ ተጠቅሞ የሰራዊቱን የቀለብ ገንዘብ 320,000 (ሶስት መቶ ሀያ ሺ ብር) እና የጦርመሳሪያ ይዞ ተሰዉሯል።
ተፈላጊዉ የትዉልድ አካባቢዉ ጌድኦ ዞን ይርጋ ጨፌ መሆኑን የገለፀዉ በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የአየር ወለድ እዝ ጠቅላይ መምሪያ 103ኛ ክፍለጦር 4ኛ ሬጅመንት ተፈላጊዉ በተገኘበት ተይዞ ተላልፎ እንዲሰጣቸዉ ለደቡብ ፖሊስ ጥያቄ አቅርበዋል።
በመሆኑም ደምና አጥንታቸዉ ገብረዉ የህይወት ዋጋ በመክፈል ለኢትዮጵያ ህዝብና ለሀገር ሉአላዊነት ሀሩርና ቁር ከሚፈራረቅባቸዉ የሰራዊቱ አባላት ገንዘብ ይዞ የተሰወረዉ ተፈላጊ ያለበትን የሚያዉቁና በቅርበት የሚያዉቁ ሁሉ በአቅራቢ ለሚገኝ የፀጥታ አካል በማሳወቅ በቁጥጥር ስር እንዲዉል ለማድረግ እንድትተባበሩ እንጠይቃለን ሲል የደቡብ ፖሊስ ጥሪውን አስተላልፏል።
ሰበር ዜና ‼️
የሃገር መከላክያ ሰራዊት ባደረገው ድንገተኛ የማጥቃት ዘመቻ ቁጥራቸው ከ370 በላይ የሆኑ የሸኔ ታጣቂዎች ሲደመሰሱ ከ150 በላይ እጃቸውን ለመንግስት ጸጥታ ሃይሎች ሰጥተዋል። ዝርዝር ዜና ይኖረናል ጠብቁን።
👉 "የህዝብ እና የሀገር ሉአላዊ መገለጫ የሆነውን መከላከያ በተላላኪዎች ማፍረስ አይቻልም‼"
♦ "...ሠራዊታችን አላፊ አግዳሚ ሽፍታ የሚደመስሰው ሳይሆን፤ በፕሮፌሽን የተገነባ የሀገራችን አለኝታ ነው‼"
-ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
የኢትዮጵያ ባህር ኃይል በመሠረታዊ ባሕረኛ ያሰለጠናቸውን አባላት ባስመረቀበት ወቅት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ የዕዝ አዛዦች የዋና መምሪያ ኃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
በዕለቱም የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እንደተናገሩት ጠላቶቻችን እና ባንዳዎች የህዝብ መከታ እና የሀገር አለኝታ በሆነውን የመከላከያ ሠራዊታችን ላይ ስም የማጥፋት ዘመቻዎችን እየፈፀሙ ይገኛሉ።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሠራዊቱን ስም በማብጠልጠል ትርፍ እናገኛለን ብለው የሚያስቡ "ሠራዊቱ ፈርሷል፣ ተበትኗል፣ እርስ ቀርሱ ተጋጭቷል፣ ተደምስሷል" በሚል ዘመቻ ላይ ቢጠመዱም፤ ሠራዊታችን ህዝባዊነቱን ጠብቆ ግዳጁን በጀግንነት የሚፈፅምና እየፈፀመ ነው ብለዋል።
"ሠራዊታችን እንደጠላት ፍላጎት ቢሆን ኖሮ ሀገራችን እና የህዝባችን ደህንነት አደጋ ላይ ይወደቅ ነበር። ሠራዊታችን አላፊ አግዳሚ ሽፍታ የሚደመስሰው ሳይሆን፤ በፕሮፌሽን የተገነባ የሀገራችን አለኝታ ነው" ብለዋል።
የመከላከያ ሰራዊታችንን በከፍተኛ ደረጃ ለመገንባት እየተሠራ ነው ያሉት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፤ በተለይም ባሕር ኃይል ሪፎርሙን መሠረት አድርገን ወደ ቀድሞ ክብሩ በመመለስ የባህር ግዳጆችን እንዲፈፅም ይዘጋጃል ብለዋል።
ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ የመጀመሪ ዙር የባሕር ኃይል ሙያተኛ ተመራቂዎች እና ለሠራዊቱ አባላት ባስተላለፉት መልዕክት በላቀ ቁርጠኝነት ግዳጃችሁን መፈፀም ይጠበቅባችኋል።
የኢትዮጵያ ባህር ኃይል ዋና አዛዥ ሬር አድሚራል ክንዱ ገዙ በበኩላቸው ሀገራችን ኢትዮጵያ ምንም እንኳ የባህር በር ባይኖራትም ከ95 በመቶ በላይ የሆነው ገቢና ወጪ ንግዳችን የሚሳለጠው በባህር ላይ ነው ሲሉ ገልፀዋል።
ሬር አድሚራል ክንዱ ገዙ ከብሔራዊ ጥቅም አኳያ እየተወሳሰበ ከመጣው የውሀ ላይ ውንብዳ እና ተግዳሮቶች አኳያ ሀገራችን ኢትዮጵያ የባህር ኃይል ያስፈልጋታልም ብለዋል።
ብሔራዊ ጥቅማችንን የሚጎዳ ኃይል ከውሃማ አካል ወደ ውሀማ ወይም ከውሃማ አካል ወደ የብስ ሊቃጡ የሚችሉ ስጋቶችን የባህር ኃይላችን ይከላከላል።
ባህር ኃይል ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን እጩ መኮንኖች ከዩንቨርሲቲ ተመልምለው በተለያዩ የውጭ ሀገራት ትምህርታቸውን የተከታተሉ 80 በመቶ የሚሆኑ የ4ኛ አመት 20 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ የ3ኛ አመት የባህር ኃይል ካዴት በትምህርት ላይ ይገኛሉ ሲሉ ገልፀዋል።
ተመራቂ መሠረታዊ ባህረኛ በአንድ ተዋጊ መርከብ ላይ በሚኖሩ ሙያዎች ተለይተው በየሙያ ዘርፉ ሰልጥነው የአለም አቀፉን የማሪታይም ስታንዳርድ አሟልተው ለምረቃ የበቁ ናቸው ብለዋል።
ከባሕር ኃይሉ እድገት ጋር አብሮ እንዲያድግ ታሳቢ በማድረግ ቀሪ ስልጠና የሚቀራቸው የማሪን ኮማንዶ ሻምበሎችን በመመስረት ላይ እንገኛለን ብለዋል።
የባሕር ኃይል መሠረታዊ ባሕረኞች ስልጠና ማዕከል ግንባታ በከፍተኛ ትጋት እና ፍጥነት እየተገነባ መሆኑን ገልፀዋል። ማዕከሉ ሲጠናቀቅ የኢትዮጵያ ባሕረኞችን ብቻ ሳይሆን ከጎረቤት ሐገር ተማሪዎችን በመቀበል በወታደራዊ መስክ የራሱን ሚና ይወጣል።
የኢትዮጵያ በሕር ኃይል የስልጠና ስራዎችን በማጠናቀቅ በየትኛውም የውሃ አካል ላይ ግዳጅ ተቀብሎ ለመስራት በሚያስችለው ቁመና ላይ ይገኛል ብለዋል።
የ ' ቅጥር ደመወዝ ' አልበቃ ቢላት ፤ ፊቷን ወደ " ሊስትሮነት " ያዞረችው የምህድስና ምሩቋ ምንታምር በለጠ
" ስሜ ምንታምር በለጠ እባላለሁ።
በሊስቶር ስራ ነው የምተዳደረው አዲስ አበባ፤ ቦሌ አካባቢ ።
የተወለድኩት በአማራ ክልል ፣ ዳንግላ ከተማ ነው። ተወልጄ የተማርኩትም እዛው አካባቢ ነው።
እናት አባቶቼ አቅመ ደካማ ነበሩ። አሁን ላይ በህይወት የሉም ሁለቱም። እህቶች እና ወንድሞች አሉኝ።
ዩኒቨርሲቲ የገባሁት በ2007 ዓ/ም ነው በ2011 ዓ/ም በቴክስታይል ኢንጂነሪንግ በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተመርቄያለሁ።
ከተመረቅኩ በኃላ ስራ ፍለጋ ነበር የወጣሁት ፤ ስራ ቶሎ ማግኘት ከባድ ስለነበር ወደ ሐዋሳ ነው የሄድኩት።
ሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ ገባሁ፤ በ2500 ብር ደመወዝ ስራ ጀመርኩ የስራ ድርሻዬ የጥራት ደረጃ ማስጠበቅ ቁጥጥር ነበር እሰራበት የነበረው ጨርቃ ጨርቅ ነው፣ ጋርመት ቲሸርቶች ሱሪ ይሰራል እሱ ላይ ጥራት መቆጣጠር ነበር የኔ ስራ።
እዚያ ሁለት ዓመት ሰራሁ ፤ ከዛ በጦርነቱም በ #AGOA / አጎዋ ምክንያት እየቀነሱ ነበር ድርጅቶቹ ሰራተኞችን ፤ ከእሱ ወጥቼ ወደ አዲስ አበባ መጣሁ።
አዲስ አበባ መጥቼ እንደጠበኩት ስራ አላገኘኹም። እየፈለኩኝ ነበር አንዳንድ ቦታዎችም ገብቻለሁ ፤ ደሞዝ የማይሰጥ ድርጅትም አጋጥሞኝ ያውቃል፤ ብዙ ተግዳሮቶችን አሳልፌያለሁ።
ሰው ቤት በተመላላሽነት ምግብ መስራትም ጀምሬ ነበር መጨረሻ ላይ ሊስትሮ / ጫማ ማስዋብ ጀመርኩ።
ዲግሪ ይዣለሁ ፤ ያሳፍራል ዲግሪ ጥቅም የለውም፤ በዲግሪ ስራ ማግኘት አልቻልኩም። ባገኝም ህይወቴን Survive የማያደርግ ፣ የቤት ኪራይ የማይከፍል ፣ ቤተሰብ የማያስተዳድር ፣ ህይወቴን የማይቀይር ደመወዝ ነው ያለው።
ቤተሰብ መርዳት ቀርቶ እራስን መቀየሪያ የለም ፤ እኔ ዩኒቨርሲቲ ስማር የገዛሁትን ልብስ ነው እስካሁን የምለብሰው ፤ ምናልባት ይሄን ሊስትሮ ከሰራሁ በኃላ ልገዛ እችላለሁ።
ከጥዋቱ 11:30 ከቤቴ እወጣለሁ ፤ ታክሲ ይዤ እዚህ ስራ ቦታዬ ላይ 12:30 ደርሳለሁ ፤ ከጥዋቱ 12:30 ጀምሮ እስከ ምሽቱ 12:40 ድረስ ስራ ቦታዬ ላይ እገኛለሁ።
ደስ ብሎኝ ነው የምሰራው፤ የራሴ መመሪያ አለኝ ፤ በጥዋት ተነስቼ መጥቼ እሰራለሁ፤ ለኔ መስሪያ ቤቴ ድርጅቴ ነው።
ወጣቱ ተስፋ መቁረጥ የለበትም ፤ ያኔ ተስፋ ቆርጬ እራሴን አልጎዳሁም አማራጭ ሳጣ ወደ ሊስትሮ ዝቅ ብዬ መስራት እንዳለብኝ አእምሮዬ ነገረኝ ፤ ይህንን በመስራቴ በጣም ደስተኛ ነኝ።
ይሄን ወጥሬ ስለምሰራ እራሴን ለመቀየረ፣ ወደዓላማዬ ፣ ወደ መንገዴ ያስገባኛል።
ከዚህ በኃላ የተሻለ ነገር መስራት አስባለሁ። ከዚህ ቀጥሎ ከሞያዬ ጋር ስለሚያያዝ ወደ ፋሽን ፣ ጋርመንት ፣ ስፌት ሞያ ሰልጥኜ ፣ ትንሽዬ ማሽንም ይሁን ገዝቼ ወደዛ የማዘንበል እቅድ አለንኝ። "
BBC AMHARIC
-----------------------
መረጃ ህይወት ነው፣ ይህንንም መረጃ ለጓደኞቻችሁ#Share በማድረግ ተባበሩን🙏
👉ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ
👇👇👇👇👇👇👇
#ጀነራል_ሙሁዚ_ኬኒሩጋባ
ፑቲንን መከላከል ካስፈለገ ኡጋንዳ ወታደሮቿን ወደ ሞስኮ ትልካለች -የኡጋንዳ ፕሬዝዳንት ልጅ
ኡጋንዳ በዩክሬን ግጭት ላይ በተባበሩት መንግስታት ምክረ-ሀሳብ ድምጽ ከመስጠት ተቆጥባለች
በሳለፍነው አርብ ምሽት የሩሲያው የቅጥረኛ ወታደር ቡድን ዋግነር ከዩክሬን ወደ ሩሲያ ገብቶ ሮስቶቭ የተሰኘችውን ከተማ አብዛኛው ክፍል መያዙን ተከትሎ በትናትናው እለት በሩሲያ ውጥረት ነግሶ ውሏል።
ዋግነር በመሪው ይቪግኒ ፕሪጎዥን በኩል የአመጽ ጥሪ ማስተላለፉን ተከትሎም በትናትናው እለት በሩሲያ ጦርና በዋግነር ቡድን መካከል ግጭቶች ተከትሰተው ነበር።
ይህንን ተከትሎም የኡጋንዳ መሪ ዩዌሪ ሙሴቬኒ ልጅ ሙሁዚ ካይኔሩጋባ የ"ኢምፔሪያሊስት" ስጋት ሲያጋጥም የኡጋንዳ ወታደሮች ሞስኮን እንደሚከላከሉ ተናግረዋል።
"ከፈለግክ የፑቲን አፍቃሪ ብለህ ጥራኝ፤ እኛ ኡጋንዳዊያን ሞስኮ በኢምፔሪያሊስቶች ስጋት ውስጥ ከወደቀች ወታደሮችን መላክ አለብን" በማለት በትዊተር ገጻቸው አስፍረዋል።
በትዊተር ላይ አወዛጋቢ መግለጫዎችን መስጠት የሚታወቁት የ48 ዓመቱ ካይኔሩጋባ በዚህ ወር ለ2026 ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ እንደሚወዳደሩ አስታውቀዋል።
ኡጋንዳ በዩክሬን ግጭት ላይ በተባበሩት መንግስታት ድምጽ ከመስጠት ተቆጥባለች።
ሩሲያ ዩክሬንን የወረረችበትን አንደኛ ዓመት አስመልክቶ ሞስኮ ወታደሮቿን ከሀገሪቱ እንድታስወጣ የሚጠይቀውን ድምጽም እንዲሁ።
በአህጉሪቱ ከቅኝ ገዢዎች ጋር ይታገሉ የነበሩትን የነጻነት እንቅስቃሴዎችን በመደገፍ ሩሲያ ከአፍሪካ ጋር ጠንካራ ግንኙነት ነበራት።
ተንታኞች ሙሁዚ ካይኔሩጋባ የ78 አመቱ የአባታቸው ዩዌሪ ሙሴቬኒ ተተኪ እንደሆኑ አድርገው ይቆጥሯቸዋል።
