ኢትዮጵያ ትቅደም
316
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kunlar
Ma'lumot yo'q30 kunlar
- Kanalning o'sishi
- Post qamrovi
- ER - jalb qilish nisbati
Ma'lumot yuklanmoqda...
Obunachilar o'sish tezligi
Ma'lumot yuklanmoqda...
Repost from 4-3-3 ስፖርት በ ኢትዮጵያ™
የ2014 የ12ኛ ክፍል የመልቀቂያ ፈተና ከወሰዱበ 980 ሺሕ ተማሪዎች ውስጥ፣ ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያገኙ ተማሪዎች 28 ሺሕ ብቻ መሆናቸውን አዲስ ማለዳ ሰምታለች፡፡
@Bisrat_Sport_433et @Bisrat_Sport_433et
🎁 ይጋብዙ እና ገንዘብ ይስሩ !
- አንድ ሰው ሲጋብዙ 2 ብር ይሰራሉ ።
🔰 መጋበዣ ሊንክ : https://t.me/Abissyina_Inviting_Bot?start=MTZiN
✅ ዛሬውኑ ጀምሮ ገንዘብ ያካማቹ እና በቴሌብር ይቀበሉ ።
አስቸኳይ ማስጠንቀቂያ 😲😲
በስመ አብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
የፊታችን መጋቢት 29 የሚካሄደው የህዝብ ቆጠራ ምክንያት በማድገግ የተለያዩ ሀይማኖቶች የኦርቶዶርስን እምነት ሊያጠፉ ይፈልጋሉ !!!
እናም ቆጠራ በሚካሄድበት ጊዜ
😟😟 አስተውሉ 😟😟
በክርስቲያን እምነት ውስጥ ከ 35,000 በላይ የሚሆኑ እምነቶች አሉ እናም ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ በማለት እምነታችን እንዳይጠፋ እንጠብቅ፣ ማለትም ለምዝገባ ሲመጡ እኛ ኦርቶዶክሶች ነን ብላቹ አስመዝግቡ እንጂ ክርስትያን ነን አትበሉ።
አስቡት እስቲ አሁን የመንግስት ሰራተኖች እረፍታቸው በሰንበት (እሁድ) ነው እረፍታቸው ግን የሀይማኖታችን ቁጥር ካነሰ ይቀየራል ለምሳሌ ሙስሊሞች አርብ ጁማቸው ነው የእነሱ ቁጥር ከበለጠ የመንግስት ሰራተኖች እረፍታቸው የሚሆነው አርብ ቀን ነው ።
እናስብ ሀይማኖታችን እንዳይጠፋ!
ጥር 11 የሚከበረው የኢየሱስ ክርስቶስ በዓል ሊቀር ይችላል እባካችሁ ሀይማኖታችንን እንጠብቅ
ቢያንስ አንድ ኦርቶዶክስ ለጓደኞቹ 10 ሰው ቢልክ ሀይማኖቱን ይጠብቃል
ድንግል ማርያም እናቴ አንቺ ጠብቂን በእግዚአብሔር ስም እለምናቹአለሁ ሁላችሁም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ናችሁ ቢያንስ ቢያንስ ለ10 ሰዎች ከተቻለ ከዚያም በላይ ለምትችሉት ሁሉ ይህን መልዕክት በመላክ ኦርቶዶክሳዊ ግዴታችንን እንወጣ ።የሁላችንም ግዴታ ነው በዚ ምክንያት እኛን ለመበታተን ጠላት አድብቶ ይሰራል እኛ ዛሬም ነገም እስክንሞት ድረስ ኦርቶዶክሶች ነን ስለዚህ ሼር ለሁሉም ይድረስ !!።
Telgram ethiopian member #Group price
5k -------1500birr
10k --------2500 birr
20k--------- 4500 birr
50k--------- 11,500 birr
100k --------20,000 birr
✍️Add lemasedereg ena werefa lemasiyaz tkekelegna ye sera sewoch becha
Inbox us @Ethio_member_adder
@Ethio_member_adder
@Ethio_member_adder
All prices are slightly negotiable,,,
Xerat fxenet tamagnenet🤝🤝
የ ሶሻል ሚዲያ ተጠቃሚነት በሰፋበት በዚ ሰአት ከ ሌሎች ጎልተው እንዲታዩ ያሎትን ቻንነልም ሆነ ግሩፕ ሜምበር እኛ በ ተመጣጣኝ በጥራት እናሳድግሎታለን።
✅ TELEGRAM CHANNEL
1k 160 birr
5k 800 birr
10k 1500 birr
....
TELGRAM GROUP
1K .........100 BIRR
5K..........500 BIRR
10K.........1000 BIRR
.....
INSTAGRAM
1k-------150BIRR
5K------650 BIRR
10K-----1200
TIKTOK
FACEBOOK
INSTAGRAM
TWITTER
YOUTUBE
በ አጠቃላይ ሁሉንም የ SOCIAL MEDIA እናሳድጋለን።
አድ ለማስደረግ እና ወረፋ ለማሲየዝ በቴሌግራም @nurilgn_hagere
@nurilgn_hagere ያግኙን።
✅ ጥራት መለያችን ነው።
Our marketing Group @ethio_shopify
🎁 ይጋብዙ እና ገንዘብ ይስሩ !
- አንድ ሰው ሲጋብዙ 1 ብር ይሰራሉ ።
🔰 መጋበዣ ሊንክ : https://t.me/HULU_Inviting_Bot?start=MTZiN
✅ ዛሬውኑ ጀምሮ ገንዘብ ያካማቹ እና በቴሌብር ይቀበሉ ።
ቴሌግራም ያለ Vpn እና Proxy እየሰራ አደለም ይህን ነፃ Proxy ተጠቅመው Connect ያርጉ ወይ Vpn ይጠቀሙ ።
https://t.me/proxy?server=russia-dd.proxy.digitalresistance.dog&port=443&secret=ddd41d8cd98f00b204e9800998ecf8427e
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#MadingoAfework
ድምጻዊ ማዲንጎ አፈወርቅ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።
ተወዳጁ ድምጻዊ ማዲንጎ አፈወርቅ ባደረበት ህመም ምክንያት ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት የቅርብ ወዳጆቹን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያዊያንን የወራት አሰያየም ትርጉም
በመጀመሪያ የምናገኘው መስከረም የሚለውን ሲሆን ይህም ቃሉ የግዕዝ ሲሆን ከሪም ከሪሞት ከሚለው አርዕስት ጥሬ ዘር ስም ንዑስ አንቀፅ አባት ዘር የወጣ ነው ትርጉሙም መክረም ማለት ነው ግዕዙ "ምሴተ ክረምት" ይለዋል የክረምት መምሻ የክረምት ጫፍ ማለት ነው በስነቋንቋ ጥናት ብዙ ጊዜ ዝ እና ስ በፀሐፊ ስህተት ይወራረሳሉና መስከረም ተባለ እንጂ በጥንት ጊዜ ይባል የነበረው መዝከረም ነው ይህም የዓመት የዓመቱ ማሰቢያ ወይም አውዳመት ማለት ነው ።
የሁለተኛ ወራችን ስያሜ ደግሞ ጥቅምት ሲሆን ይህም ጠቂም ጠቂሞት ወይም መጥቀም ከሚለው አርዕስት ጥሬ ዘር ስም ንዑስ አንቀፅ አባት ዘር የወጣ ሲሆን ትርጉሙ የተሰራች ስር ማለት ነው በሀገራችን እንደምናውቀው ከሁሉም በተለየ ይህ ወር የስራ ወር ነው እንዲሁም የፍሬ ወር ጭምርም ነው ።
ህዳር የሶስተኛ ወራችን ስያሜ ሲሆን በዕብራይስጥ አዳር እንደማለት ነው ሀዲር ሀዲሮት ከሚለው አርዕስት ጥሬ ዘር ስም ንዑስ አንቀፅ አባት ዘር የወጣ ነው በሀገራችን እንደሚታወቀው የአዝመራ ወር ስለሆነና ጠባቂዎች በዱር የሚያድሩበት ጊዜ ስለሆነ ስያሜው ሊሰጠው ችሏል ።
አራተኛው ወራችን ታህሳስ ይባላል ሀሲስ ሀሲሶት ከሚለው አርዕስት ጥሬ ዘር ስም ንዑስ አንቀፅ አባት ዘር የወጣ ሲሆን ምርምር ማድረግ፣መፈለግ ማለት ነው ይህ ወር ክብር ይግባውና ጌታችን መድሐኒታችን እየሱስ ክርስቶስ የተወለደበት ወር ነው ቅዱስ መፅሐፍ እንደሚነግረን በተወለደ ጊዜ 3 ነገስታት የተወለደው ንጉስ ወዴት ነው እያሉ እየመረመሩ ቤተልሔም ድረስ የመምጣታቸውን ምሳሌ ይዋጃል ።
አምስተኛ ጥር ነው ጠይሮ ጠይሮት ከሚለው አርዕስት ጥሬ ዘር ስም ንዑስ አንቀፅ አባት ዘር የወጣ ሲሆን ምጥቀት ርዝመት ማለት ነው በዚህ ወር ኦዘፍ 11:1-7 እና በመፅሀፈ ኩፋሌ 10:12 እንደምናገኘው በሰናኦር አካባቢ 43 ዓመት የፈጀ ቁመቱ 5432 ክንድ ከሁለት ስንዝር የሆነ ህንፃ ተሰርቶ ነበር ነገር ግን የከላዳዉያን ቋንቋ ተደባልቆባቸው ህንፃቸው ፈርሷል ሊቃውንቱ ርዝመት ያለው ህንፃ የፈረሰበት ሲሉ ጥር ብለውታል ።
የስድስተኛ ወራችን ስያሜ የካቲት ይባላል ይህም ከቲት ከቲቶት ከሚለው ንዑስ አንቀፅ የወጣ ሲሆን ትርጉሙ ማስገባት ማለት ነው ድንቅ ነው የመኸር መካተቻ የበልግ መባቻ እንደማለት ነው ።
መጋቢት ሰባተኛ ወራችን ሲሆን መግቦ መግቦት ከሚለው አርዕስት ጥሬ ዘር ስም ንዑስ አንቀፅ አባት ዘር የወጣ ሲሆን የሌሊቱም የመዓልቱም እኩል የሚሆኑበት ማለት ነው ይህም ቀኑም 12 ሌሊቱም 12 ሰዓት እንሚመሆን የሚያመላክት ነው ።
በስምንተኛው የወራት ስያሜያችን የምናገኘው ሚያዚያ የሚለውን ነው ይህም ምሂዝ ምህዞት ከሚለው አርዕስት ጥሬ ዘር ስም ንዑስ አንቀፅ አባት ዘር የወጣ ሲሆን መቅረብ ማጀብ ማክበር ማለት ነው የሚዛዚት ወይም የሚዜወች የሙሽሮች ወራት ማለት ነው እንደሚታወቀው በሀገራችን የሰርግ ጊዜ በዚህ ወር የሚደረገው ይሄን ተንተርሶ ነው ።
ዘጠነኛው ግንቦት ነው ገንቦ ገንቦት ከሚለው አርዕስት ጥሬ ዘር ስም ንዑስ አንቀፅ አባት ዘር የወጣ ሲሆን የክረምት አቅራቢያ የክረምት ጎን ማለት ነው ሊቃውንት አባቶቻችን ለምን እንደዚህ ብለው እንደሰየሙት ግልፅ ነው ።
አስረኛው ወር ሰኔ ነው በዕብራይስጥ "ሴዋን" ይባላል ሰንይ ሰንዮት ከሚለው አርዕስት ጥሬ ዘር ስም ንዑስ አንቀፅ አባት ዘር የወጣ ሲሆን ይህም ማማር መቆንጀት ማበብ ማለት ነው ።
አስራ አንደኛው ወር ሐምሌ ነው ይህም ሀሚል ሀሚሎት ከሚለው አርዕስት ጥሬ ዘር ስም ንዑስ አንቀፅ አባት ዘር የወጣ ሲሆን መለምለም ማለት ነው ድንቅ ነው የሰኔ እና የሀምሌን ፍቻቸውን ስናይ ከጊዜው ጋር አብረው ይሄዳሉ ።
የአስራ ሁለተኛው ወራችን ስያሜ ነሀሴ ሲሆን ንሂስ ንሂሶት ከሚለው አርዕስት ጥሬ ዘር ስም ንዑስ አንቀፅ አባት ዘር የወጣ ሲሆን በዘይቤው ሲፈታ "ጥብቀት" ማለት ነው የቃሉ ትርጉም በዚህ ወር አዝርዕት ስር የሚሰዱበት በቁመት የሚያድጉበት እንደሆነ የሚዋጅ ነው ።
አስራ ሶስተኛዋ ወራችን ጳጉሜን ትባላለች እንዴት ጳጉሜ እንደተባለች ?
አምስት እና ስድስት እንደምትሆን እናውቃለን ነገር ግን በ600 ዓመት አንድ ጊዜ ሰባት እንደምትሆንስ ያውቃሉ ?
ከሌሎቹ ወራቶች ሰፋ ያለ ዝርዝር እና ትንተና ሰለሚፈልግ ሀሳቡን በአጭሩ ይዘን እንመለስበታለን
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
🇪🇹 ታላቁ ንጉስ ነገስት ኢትዮጵስ 1ኛ
ኢትዮጵስ 1ኛ ከክርስቶስ ልደት በፊት ከ1856 እስከ 1800 ዓመት ኢትዮጵያን የገዛ ታላቅ ንጉሥ ነበር። የራጉኤል (ዮቶር) ልጅ የሆነው አባብሄር በሲና ምድረ በዳ በነበረ ጊዜ ከአይሁድ ነገድ የሆነችውን ሩት አሚን አግብቶ ታላቁን ኢትዮጵስን የወለዱ ሲሆን በታላቅ ስርዓትም በግዮን ወንዝ ዳርቻ ስመ መንግስቱ ሰንደቅ ዠን ተብሎ የነገሰ ነው።
በሱ የስልጣን ዘመን በመላ ኢትዮጵያ በረከት ሆኖ ነበር። ዛፎች ልምላሜና ፍሬ ይሰጡም ነበር። አህዛብ ሁሉ የጣኦት አማልክትን የሰባበሩበት የፈጣሪም መንፈስ በመላ ሀገሪቱ የነገሰበት የበረከት ዘመን ነበር።
ንጉስ ነገስት ኢትዮጵስ (ሰንደቅ ዠን) በብዙ የሀገሪቱ ቦታዎች ታላላቅ ከተሞችንና መንደሮችን የቆረቆረ ነው። በሰባተኛ ዘመነ መንግስቱም ወደ ተራራማው የቴሌጋቫ ምድር ሄደ። በዚህ ምድር ጉምዞች ፣ በአያ ፣ ሽናሻ ፣ አገዎች ፣ ትግሬዎች ፣ ኦማርና አረማዎች ይኖሩበት ነበር። በዛም ታላቂቱን ከተማ ሱቫን ሰራ። በላያ በመባልም ትታወቅ ነበር። አሁንም ቢሆን በላያ የተባሉ ህዝቦች ይኖሩበታል። በዘልማድ የበላያ አገዎች ይባላሉ።
ንጉሥ ኢትዮጲስ የአንድ ሃይማኖትን ስነ ምግባርና ተግባር የሰበከ ታላክ ንጉሥ ነበር። ህዝባዊነትን፣ ምልክናንና ክህነቱን በኢትዮጵያ ያፀና መንፈሳዊ ንጉሥም ነበር። በአስፈሪነቱ ፣ በመንፈሳዊነቱና ታማኝነቱ ለእግዚአብሔርና ለሰው ሁሉ የተመቸ ሰው ነበር።
ንጉሥ ኢትዮጲስ በሶስት አመት ውስጥ ታላቅ የሆነ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ በማሰራት 1200 ንፁሃን ሰወች ያገለግሉ ዘንድ አስገባ። የእግዚአብሔርን ስርዓት የሚጠብቁና የሚአስተምሩ 400 ነብያትንም አስገባ።
ንጉሱ ይህን ሁሉ ያረግ የነበረው እግዚአብሔር በሃገሩ በኢትዮጵያና ህዝቦቿ ላይ ፅንቶ እንዲኖር በማሰብ ነበር። እግዚአብሔርም አላሳፈረውም " ከእንግዲህ ሀገሪቱ ሀገረ እግዚአብሔር ኢትዮጵያ ተብላ ትጠራለች እስከ ዘመነ ምጽአትም ድረስ ኢትዮጵያ እግዚአብሔር የሚመለክባት ምድር ሆና እንደምቀጥል" ለንጉሱና ለካህናቱ ቃል ኪዳን ገባላቸው። በዚህ ንጉሥ መልካምነትና በአባቶቻችን ትጋት ከዛ ጊዜ ጀምሮ የወረደው ሀይለ መንፈስ ቅዲስ በኢትዮጵያ ላይ ስለማይነሳ የእግዚአብሔር ሀገር ልትባል ችላለች። ገናም ስትባል ትኖራለች።
ንጉሥ ኢትዮጵስ የኢትዮጵያን ስም ያከበረና ከፍ ከፍ ያደረገ ሀገሪቱንም ኢትዮጵያ ተብላ እንድትጠራ ያደረገ ታላቅ የሀገራችን ባለውለታ ንጉሥ ነበረ። በዘመኑም ምድሩ ከማለምለምና ከተማ ከመቆርቆር በስተቀር ምንም አይነት ጦርነት ችግር መከራ አልነበረም ነበር።
👉 ታላላቅ ሰዎች ከራሳቸው በላይ ለቀጣዩ ትውልድ በማሰብ የሚተጉ ናቸው። የእነ ንጉስ ኢትዮጵስ ትጋትና ድካም ለኢትዮጵያ የዘላለም ቃልኪዳንና በረከት ያስገኝ ነው። ዛሬ ዓለም ከሃይማኖት ርቃ በተለያየ ፍልስፍና እና ትርምስ ውስጥ ባለችበት ከባድ ወቅት እንኳ ኢትዮጵያ ሳትፈራርስና ፈጣሪዋን ሳትተው ይሄው ብዙ ሺ ዓመታት ተሻግራ ቆማለች፤ ይህም መሆኑ ከታላቁ ኢትዮጵስ 1ኛ ጀምሮ የወረደው ሀይለ መንፈስ ቅዱስ በኢትዮጵያ ላይ ስለማይነሳ ነው። ዛሬ በተለያየ አቋራጭ ከምናካብተው ጊዜአዊ ዝናና ሃብት ይልቅ በሃቅ ቁመን ለትውልድ መትጋትን ከታላቁ ንጉሳችን ኢትዮጵስ 1ኛ እንማር።