uz
Feedback
አዶናይ

አዶናይ

Kanalga Telegram’da o‘tish

በዚህ ቻናል በኩል የታረደውን የእግዚአብሔር በግ እያከበርን ፣ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት በውስጥ ሰውነታችንን በሀይል እንበረታለን። መንፈስ ቅዱስ ከኛ ጋር ነው 🥰 @AdonaiComments_bot

Ko'proq ko'rsatish
7 499
Obunachilar
-424 soatlar
-137 kunlar
-8030 kunlar
Postlar arxiv
ለደቂቃም ቢሆን አንተን የሚሸፍን ህይወት አይኑረኝ...

እግዚአብሔር አብርሃም ቤት ይስሃቅን ባይሰጥም መስዋዕት ይቀርብለታል እግዚአብሔር እዮብ ጋር ዝም ቢልም ይታመናል እግዚአብሔር ሙሴ ቤት የተናገረውን ባይፈፅምም ይመለካል እግዚአብሔር ዳዊት ጋር ቢቀጣም ይወደዳል ይህ እግዚአብሔር በህይወታችን ምንም አይነት ነገር ባያደርግ፣ ጠረተነው ዝም ቢል ፣ ፈልገነው ባይገኝም በኛ ልብ ውስጥ ያለው የአምላክነት ቦታ ግን በፍፁም አይቀንስም ! ባያድንም የሚመለክ አምላክ ነው ያለን ። @thedayofpentecost @thedayofpentecost

አለማወቃችን እንጂ በህይወታችን ያለ እግዚአብሔር ህልውና የኖርንባቸውን ቀኖች ያህል የከሰርናቸው ቀኖች የሉንም ። የኪሳራዎች ሁሉ ኪሳራ ፣ የማጣቶች ሁሉ ማጣት ያለ እግዚአብሔር ህልውና መኖር መጀመር ነው !

🎙️መንፈስ ቅዱስ ህይወቱ በፍፁም ሊክደው የማልችለውን የመንፈስ ቅዱስ አብሮነት እና ምህረት ያየ ሰው ማለት እኔ ነኝ 😭
መንፈስ ቅዱስ የእውነት ወዳድ መሆን ይችልበታል።
@thedayofpentecost @thedayofpentecost

ኃጢአት እኮ አይደለም 😏 አሁን የእውነት በቀን 6 ሰዓት ስልክ Scroll እያደርጉ ማዋል ወይም ተከታታይ ፊልም ቁጭ ብሎ መኮምኮም ኃጢአት ነው ? መቼም ናቸው አትሉኝም ነገር ግን አሁን አሁን እየገባኝ የመጣው እውነት ቢኖር የብዙዎችን መንፈሳዊነት እያደከሙ ያሉት ነገሮች እንደነዚህ በድፍኑ ኃጢአት ሳይሆኑ በየቀኑ እኛ በቀላሉ በምናደርጋቸው ነገሮች ምክንያት ነው ፤ ሁሉም ሰው ቢሆንለት በመንፈሳዊ ህይወቱ መጠንከር ይፈልጋል ችግሩ ግን እነኚን ነገሮች ያለመጠን ሳይመርጥ በአንዱ አይምሮ ውስጥ ከመንፈሳዊ ነገሮች ጋር ቀላቅሎ ለማስቀመጥ መሞከሩ ነው 😔 አሁን ሁላቹም የሆነ ቀን ዝም ብለን አይምራችን ውስጥ ያለ ገደብ የሚገቡትን ሃሳቦች ለማስተዋል ብንሞክር ምን ያህል ነፍሳችንን የሚያቀጭጩ ትናንሽ የሀሳብ መርዞች እንደምንወስድ ባስተዋልን ነበር፤ ብቻ ባጭሩ ከአንዳንድ ነገሮች ለመቆጠብ የግድ እነኛ ነገር ኃጢአት ናቸው የሚል ታርጋ እንኪለጠፍባቸው መጠበቅ የለብንም ፤እግዚአብሔር ሀሳቦች ውጪ በየቀኑ ልባችን ውስጥ ለሚገቡት ነገሮች መጠን ሊኖረን ይገባል፤ ካልሆነ ግን ኃጢአት አይደለም ብለን የጀመርናት ትንሿ ጉዳይ ቀስ በቀስ የኃጢአት ባህር ውስጥ እኛን መክተቷ አይቀርም።
የመርዝ ትንሽ የለውም እናስተውል!
@thedayofpentecost @thedayofpentecost

🎙️ አስር ጊዜ ባይህ 😭
አስር ጊዜ ባይህ አስሬ ፈራለው ፥ ሁል ጊዜም ባገኘህ እደነግጣለሁ ፤ እንደ ቤተኛ ቅርብ እንደ እንግዳ ብርቄ ፥ ደጋግመህ ብትመጣ ሽርጉድ እላለሁ ወገቤን ታጥቄ፤
@thedayofpentecost @thedayofpentecost

ጌታን ሳታገኙት ከወር በላይ መቆየቱ ግን አይከብድም 😔 ? እንኳን ወሩ ቀኑም ቢሆን እኮ ካለሱ ከባድ ነው ! @thedayofpentecost
ጌታን ሳታገኙት ከወር በላይ መቆየቱ ግን አይከብድም 😔 ? እንኳን ወሩ ቀኑም ቢሆን እኮ ካለሱ ከባድ ነው ! @thedayofpentecost

ካለህበት ቦታ ተነስ 😁 የአባቴ ልጆች እኔ ወንድማቹ ሰሞኑን ቤተ ክርስቲያን የገጠመኝን ላወራቹማ ስሙኝ... 🥰 ሰዓቱ የእግዚአብሔር ቃል የምንሰማበት ሰዓት ነበር እና አንድ የእግዚአብሔር ሰው መድረኩን ይዞ የጌታ ቃል በሚገርም መልኩ መስበክ ጀመረ እኔና አንድ ወንድሜ ደግሞ ከበስተዋላ ጥግ ላይ ተቀምጠን ስብከቱን እየሰማን ነው ከጎኔ ደግሞ አንድ ልቤ ያረፈባቸው ቢበዛ የ ስድስት አመት ልጅና አባት ተቀምጠዋል፤ ሰባኪው በሰዓቱ እንደማንኛው ኢትዮጵያዊ ሰባኪ ከጎናቹ ያለው ሰው ያዙ እና እንዲህ በሉት ማለት ያበዛል😀( ይቺም ደግሞ ቃል ሆና እንዳሰነጥቋት Just የተለመደ ስለሆነ ነው) እና ከጎኔ ያለውን ወንድሜን እንዲ እንዲያ ስለው ቆየውና ፤ ከስድስት አመት ልጇቸው ጋር ተቀምጠው የነበሩትን አባት አየት ሳደርጋቸው ከጎናቹ ሰባኪው በሉ የሚሉትን ሰው አጥተው ያንኑ ከጎናቸው ያለውን ልጃቸውን እጁን ይዘው ሰባኪው በሉ ያለው ቃል በሙሉ ሲነግሩት አስተዋልኩ በመሀል ላይ ግን ሰባኪው ከጎንህ ያለውን ሰው ካለህበት ቦታ ተነስ በልና ንገረው ብሎ ሲያውጅ እኚህ አባትም እንደለመዱት ልጃቸውን ይዘው በሉ የተባሉትን ቃል ቢሉት ልጃቸው ግን ከወንበሩ ተነስቶ አባ ልወጣ ፈቀድክልኝ ብሏቸው አረፈው😁 አባት ልጃቸውን ምን ማለት እንደፈለጉ ሊያስረዱት ቢሞክሩም ልጃቸው ግን ልቡ ውጪ ውጪውን ያይ ስለነበር ሊሰማቸው አልፈለገም ኃላ ላይ ግን አባት ሳይፈልጉ ልጃቸውን ቆጣ ብለው ወንበሩ ላይ አስቀመጡት... ምን ልላቹ መሰላቹ 🥰 አንዳንዴ እግዚአብሔር አንዳንድ ነገሮች የማይነግረን እኛ ለራሳችን በሚመቸን መልኩ ተርጉመን እንዳንረዳውና እንዳንጠፋበት ስለሚፈልግ ነው፤ እኚህ አባት ልጃቸውን በቅጡ እንዲህ በል ለማለት በአይምሮ ሳያሳድጉት ስለነገሩት ልጃቸው ማጥፋቱን ሳያውቀው ጥፍተኛ ሆኖ ተገኘባቸው፤ እግዚአብሔር ግን ይህ ህይወት በእኛ እንዲፈጠር አይፈልግም ለዚህም ነው ከእርሱ ለምንሰማቸው ነገሮች መጀመሪያ ሳያሳድገን ምንም ነገር የማያደርግልን፤ የተወደዳቹ ምንም ያህል ልጆች ብትሆኑም የታሰበላቹ ሁሉ ግን ይነገራቿል ማለት አይደለምአንዳንድ የእግዚአብሔር ዝምታዎች የእናንተን ማደግ ነው የሚጠብቁት። @thedayofpentecost @thedayofpentecost

Repost from አዶናይ
ካለህበት ቦታ ተነስ 😁 የአባቴ ልጆች እኔ ወንድማቹ ሰሞኑን ቤተ ክርስቲያን የገጠመኝን ላወራቹማ ስሙኝ... 🥰 ሰዓቱ የእግዚአብሔር ቃል የምንሰማበት ሰዓት ነበር እና አንድ የእግዚአብሔር ሰው መድረኩን ይዞ የጌታ ቃል በሚገርም መልኩ መስበክ ጀመረ እኔና አንድ ወንድሜ ደግሞ ከበስተዋላ ጥግ ላይ ተቀምጠን ስብከቱን እየሰማን ነው ከጎኔ ደግሞ አንድ ልቤ ያረፈባቸው ቢበዛ የ ስድስት አመት ልጅና አባት ተቀምጠዋል፤ ሰባኪው በሰዓቱ እንደማንኛው ኢትዮጵያዊ ሰባኪ ከጎናቹ ያለው ሰው ያዙ እና እንዲህ በሉት ማለት ያበዛል😀( ይቺም ደግሞ ቃል ሆና እንዳሰነጥቋት Just የተለመደ ስለሆነ ነው) እና ከጎኔ ያለውን ወንድሜን እንዲ እንዲያ ስለው ቆየውና ፤ ከስድስት አመት ልጇቸው ጋር ተቀምጠው የነበሩትን አባት አየት ሳደርጋቸው ከጎናቹ ሰባኪው በሉ የሚሉትን ሰው አጥተው ያንኑ ከጎናቸው ያለውን ልጃቸውን እጁን ይዘው ሰባኪው በሉ ያለው ቃል በሙሉ ሲነግሩት አስተዋልኩ በመሀል ላይ ግን ሰባኪው ከጎንህ ያለውን ሰው ካለህበት ቦታ ተነስ በልና ንገረው ብሎ ሲያውጅ እኚህ አባትም እንደለመዱት ልጃቸውን ይዘው በሉ የተባሉትን ቃል ቢሉት ልጃቸው ግን ከወንበሩ ተነስቶ አባ ልወጣ ፈቀድክልኝ ብሏቸው አረፈው😁 አባት ልጃቸውን ምን ማለት እንደፈለጉ ሊያስረዱት ቢሞክሩም ልጃቸው ግን ልቡ ውጪ ውጪውን ያይ ስለነበር ሊሰማቸው አልፈለገም ኃላ ላይ ግን አባት ሳይፈልጉ ልጃቸውን ቆጣ ብለው ወንበሩ ላይ አስቀመጡት... ምን ልላቹ መሰላቹ 🥰 አንዳንዴ እግዚአብሔር አንዳንድ ነገሮች የማይነግረን እኛ ለራሳችን በሚመቸን መልኩ ተርጉመን እንዳንረዳውና እንዳንጠፋበት ስለሚፈልግ ነው፤ እኚህ አባት ልጃቸውን በቅጡ እንዲህ በል ለማለት በአይምሮ ሳያሳድጉት ስለነገሩት ልጃቸው ማጥፋቱን ሳያውቀው ጥፍተኛ ሆኖ ተገኘባቸው፤ እግዚአብሔር ግን ይህ ህይወት በእኛ እንዲፈጠር አይፈልግም ለዚህም ነው ከእርሱ ለምንሰማቸው ነገሮች መጀመሪያ ሳያሳድገን ምንም ነገር የማያደርግልን፤ የተወደዳቹ ምንም ያህል ልጆች ብትሆኑም የታሰበላቹ ሁሉ ግን ይነገራቿል ማለት አይደለምአንዳንድ የእግዚአብሔር ዝምታዎች የእናንተን ማደግ ነው የሚጠብቁት። @thedayofpentecost @thedayofpentecost

ጥያቄ ?
selam wendme mtlekachew contentoch betam des ylalu😊😊 kezi befit slezi neger bzu gize awrtehal gn degagmeh beand hatiat slemewdek, specially wstachn yale mnfes qdus biweqsenm esun ignore adrgen wediyaw wede hatiatu enmertalen keza degmo kaderegnew buhala ykochenna endegena confess madreg, mecheresha lay aymrowachn yann hatiat normalize yadergbnal...be gl experience adrgewalew, I always repent gn it is normal ylegnal aymroye..I have tried to read verses about it lots of times and get motivated but emelesalew. mn enadrg endi aynet sewoch?
እውነት ነው አንዳንዴ ኃጢአትን በደግግሞሽ ብዛት እና በዙሪያችን ያሉት ሰዎች ነገሩን Normalized ከማድረጋቸው የተነሳ ቀስ በቀስ እኛም ጋር ኃጢአቱ Normal ወደመሆን ሊመጣ ይችላል፤ ነገር ግን ኃጢአት ምንም ያህል በአይምሯችን Normal ነው ብለን ማሰብ ብንጀምርም የኃጢአቱን ውጤት ግን በእኛ አስተሳሰብ ምክንያት መቀየር አንችልም፤ በቀላሉ ለማስረዳት ያህል... የኃጢአት ውጤቱ ሞት ነው አይደል ይህን እውነት እኛም ሰይጣንም እናውቀዋለን❗ ነገር ግን ሰይጣን ሞት ያለበትን ጉዳይ ሰዎች ደጋግመው እንደማያደርጉለት እና የኃጢአት ውጤቱን መቀየር እንደማይችል ስለሚያውቅ በቀጥታ በሰዎች አይምሮ ላይ ሰዎች ለኃጢአት ያላቸውን አመለካከት በተለያዩ መንገዶች መቀየር ላይ ትኩረቱ ያደርጋልከዛም ሰይጣን በቀላሉ አይምራችንን በማሳመን ያ ትናንት ማድረግ የማንፈልጋቸውን ኃጢአቶች Normal አድርጎብን ቀስ በቀስ ያለ እርሱ እገዛ ኃጢአቱን እኛው ራሳችን ማድረግ እንጀምራለን ማለት ነው፤ በዚህም ምክንያት ታዲያ አንድ ሰው ኃጢአት Normal እየሆነበት ከተቸገረ ሰይጣን ቀድሞ አስተሳሰቡ ላይ እየሰራበት ሊሆን ስለሚችል ከዚህ ባህሪ ለመላቀቅ የግድ ያንን ኃጢአት Normal ያደርጉበትን ሀሳቦችና ትምህርቶች በሌላ በእግዚአብሔር ሀሳቦች መቀየር ይኖርበታል ፤ ሌላው ነገር ደግሞ አይምሯችን ነገሮችን Normal የሚያደርገው እኛው ለነገሩ ካለን አቋምና ልምምድ የተነሳ ስለሆነ በቅድስና ዙሪያ የትም ቢሆን ፣ ከማንም ጋር የማንለውጠው የቅድስና አቋም ሊኖረን ይገባል፤ በቀላሉ በኃጢአት ጉዳይ መቼም ቢሆን የማታመቻምቹ አይነት ሰዎች መሆንን ልመዱ @thedayofpentecost @thedayofpentecost

እስከዛሬ እግዚአብሔር በህይወታቹ ያስተማራቹ የማትረሱት Big lesson ምንድነው ?

🎬አንዴ ብቻ 😭 የእድሜ ልክ ጥያቄዬ... @thedayofpentecost @thedayofpentecost

ለምናልባት እንኳን ብዬ ከእርሱ ውጪ ለመኖር ሌላ ቤት አልሰራሁም፤ መስራትም አይፈልግም። ስደክም የመሸሸግበት መደበቂያ አጥሬ ፤ መኖሪያዬም እርሱ ነው። @thedayofpentecost @thedayofp
ለምናልባት እንኳን ብዬ ከእርሱ ውጪ ለመኖር ሌላ ቤት አልሰራሁም፤ መስራትም አይፈልግም። ስደክም የመሸሸግበት መደበቂያ አጥሬ ፤ መኖሪያዬም እርሱ ነው። @thedayofpentecost @thedayofpentecost

Repost from አዶናይ
ይቅር የፈለኩት ይቅር ያለቀስኩበት ይቅር የምድሩ ይቅር ሰውኛው ለኔ ሚበልጥብኝ መንፈስህ ነው ለኔ ሚበልጥብኝ ክብርህ ነው
መንፈስ ያለበት ድንቅ አምልኮ 🔥 @thedayofPentecost @thedayofPentecost

አቁሙ 😠 አቅማቹንና ነጋቹን እንደ ቀልድ እየበሉባቹ ካሉ ነገሮች ለምን ራሳቹን አታድኑም ? ቁም ነገር በሌለው ሳቅና ቀልድ በየቀኑ በየ social mediaw ውድ ጊዜያቹን እንዲሁ ማባከን ኪሳራ እንጂ ትርፍ ያለው አይመስለኝም.... በዚህ እንኳን ቀልዳቹበት ሰርታቹበት እንኳን መለወጥ በማይቻልበት ጊዜ አጉል ስንፍና ውስጥ መቆየታቹን አቁሙ 😠 Social media ላይ ማፍጠጥ አቁሙ... ላለመፀለይ ምክንያት መደርደራቹን አቁሙ.... ለውጣቹ ላይ ሙድ ከሚይዙ ጓደኞቻቹ ጋር ያላቹን ህብረት አቁሙ በቃ በህይወታቹ ላይ ወስኑ ትኩረታቹን ከሰዎች አስተሳሰብና ውሎ ላይ አንስታቹ ራሳቹ ላይ ማድረግ ጀመሩጌታ እንጂ ጊዜ ምህረት አያቅም በጊዜያቹ ተጠቀሙ። @thedayofpentecost @thedayofpentecost

ያለ ምንም ምክንያት ዝም ብላቹ እግሩ ስር የምትገኙበት ጊዜ ይብዛላቹ 🔥

ጌታ ረድቷቹ ዛሬ ሙሉውን መልዕክቴን የምታነቡ ከሆነ ከትዳር በፊት sex ማድረግ ኃጢአት ነው ከሚለው እውቀት ያለፈ ስለ Sex ምንነት የጠለቀ መንፈሳዊ መረዳት ይኖራቿል 😊 ለምን እግዚአብሔር ከትዳር በፊት Sex እንዳናደርግ የሚከለክለን ይመስላቿል ? ለዚህ ጥያቄ መልስ ሊሆኑ የሚችሉ ሁለት ሀሳቦችን ነሳላቿለሁ... ✨ ከትዳር በፊት ከማንኛውም ሰው ጋር አውቃቹም ይሁን ሳታውቁት ፆታዊ ግንኙነት ስታደርጉ፤ በቀጥታ በመንፈስ አለም ከዛ ሰው ጋር ኪዳን ትገባላቹአውቃለሁ ይህ እውነት ለብዙዎቻቹ ላይዋጥላቹ ይችላል ነገር ግን እውነታው Sex በመንፈስ አለም አብረን ግንኙነት ካደረግነው ሰው ጋር ኪዳን ማድረጋችንን ነው የሚያሳየው ፤ በየትኛውም ሰዓት በልባቹ ሀሳብም ይሆን በአካል ፆታዊ ግንኙነት ስትፈጥሩ በመንፈስ አለም ሳታውቁት በመካከላቹ ከዛ ሰው ጋር የጠነከረ ህብረት ትፈጥራላቹ፤ በዚህም ህብረት በኩል ደግሞ ሰይጣን አብራቹ ግንኙነት ያደርጋቹትን ሰው በመጠቀም ሳታውቁት በከፈታቹለት መንፈሳዊ መንገድ በኩል አንዳንዴ በህልም ሌላ ጊዜ ደግሞ በሀሳባቹ ውስጥ በመመላለስም ህይወታቹን ለማበላሸት ሰፊ እድል ያገኛል፤ ለዚህም ነው አሁን ላይ በየ Social media ው እርኩሰት በነፃነት እየተበተነ የብዙ ሰዎች መንፈሳዊ ሀይል ባዶ እየሆነ ያለው። ✨ ሁለተኛው ደግሞ Sex ከአካል ንክኪነት በላይ መንፈሳዊ ህብረትን እንድትፈጥሩ ወይንም አንድ ስጋ እንድትሆኑ ያደርጋል። እግዚአብሔር ወደ ትዳር ከመምጣታቹ በፊት ወይም ከትዳራቹ ውጪ የምታደርጉትን ፆታዊ ግንኙነት እንደ ኃጢአት ከሚያይባቸው ዋነኛው ምክንያቶቹ ውስጥ አንዱ እናንተ ይሄን ያህል አስባቹበት በትዳር ካልተጣመራቹት ሰው ጋር ሳታውቁት መንፈሳዊ ህብረት ወይም አንድነት ፈጥራቹ ዋጋ እንድትከፍሉ ስለማይፈልግ ነው ፤ ለዚህም ነው በወንድና በሴት መካከል የሚደረገውን ፆታዊ ግንኙነት በትዳር ውስጥ ሲሆን የጌታ ፈቃድ የሚፈፀምበት በዛ ውጪ ሲደረግ ግን ዋጋ የሚያስከፍል ኃጢአት የሆነው።
ምናልባት አሁን ላይ በ Social media ሆነ በአካል ሳታውቁት ስህተት ሰርታቹ በህይወታቹ ልክ ያልሆነ ነገር እያስተዋላቹ ያላቹ ሰዎች ካላቹ በቀጣይ በምን አይነት መልኩ ከንደነዚህ አይነት መንፈሳዊ ተጽዕኖዎች ነፃ መውጣት እንዳለባቹ አብረን የምናይ ይሆናል።
@thedayofpentecost @thedayofpentecost

እግዚአብሔር ለታሪካቹ ይጠነቀቃል !
እግዚአብሔር ለታሪካቹ ይጠነቀቃል !