HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
Kanalga Telegram’da o‘tish
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
Ko'proq ko'rsatish2 276
Obunachilar
+524 soatlar
+117 kunlar
+3430 kunlar
Postlar arxiv
ግንቦት ፲፭ /15/በዚች ቀን ከዐሥራ ሁለቱ አንዱ ሐዋርያ ስምዖን ምስክር ሆኖ አረፈ። እርሱም ናትናኤል ተብሎ ይጠራል በገሊላ አውራጃ የቃና ሰው ነው የኦሪትና የነቢያትንም መጻሕፍት ተምሮ ያወቀ ነው። መንፈሳዊ ቅንዓትም በውስጡ አለበት ስለዚህም ቀናዒ ተባለ እርሱም ንጹሕ ፊት አይቶ የማያደላ በሃይማኖቱ ዕውነተኛ ነው። አጽናኝ የሆነ የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ በተቀበለ ጊዜ የሀገሩ ሁሉ ቋንቋ ተገለጠለት መለኮታዊ ምሥጢርንም አወቀ ወደ ኵርጅ አገርና ወደ እልብጅህ ከተማ ከሀድያን በድንቁርና ወደሚኖሩበት ሁሉ ገብቶ የሃይማኖትን ብርሃን አበራላቸው። ከተራቃቂዎችና ከሰነፎችም ብዙዎችን መልሶ በክብር ባለቤት ክርስቶስ ሃይማኖት ልባቸውን አበራላቸው። የክርስትና ጥምቀትንም አጥምቆ ነጣቂዎች ተኵላ የነበሩትን የዋሃን በጎች አደረጋቸው። ሁለተኛም ወደሌሎች የከሀድያን አገሮች ወደ በራንጥያ ደሴትም ሒዶ በውስጣቸው ሰበከ። ይዘውም ጽኑዕ ሥቃይን አሠቃዩት እርሱ ግን ኃይልና ብርታትን ተጨመረ በእግዚአብሔርም ኃይል ሙታንን አስነሣ እንዲአጠምቃቸውም ለመኑት የክርሰትና ጥምቀትንም አጠመቃቸው ብዙ ዘመንም ኖረ። ከዚህም በኋላ ከሀድያን ይዘው በዕንጨት ላይ ሰቀሉት በዚህም ምስክርነቱን ፈጽሞ ከወንድሞቹ ሐዋርያት ጋራ የማይጠፋ መንግሥትን ወረሰ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239
=> ዛሬ በጣም ደስ ብሎኛል በእውነት አንደበት ሁሉ የእግዚአብሔርን ሥራ ይመስክር። ታርኩ እንዲህ ነው አንድ ወዳጄ ጎበዝ የሥራ ሰው ነው። በመንፈሳዊ ሕይወቱም ጎበዝ የሚባል ወዳጄ ነው። ታዲያ በሚሰራበት መስሪያ ቤት ውስጥ በጣም ደስ የማይል በብሔር የመለያየት ጉዳይ ተፈጥሮ በሁሉም ነገር ማግለል፣ ከሚፈልጋቸው ነገሮች ማራቅና ከደረጃ ዕድገት ያርቁት ጀመር። ታዲያ ይሄንን ጉዳይ ስንወያይ አይዞህ እግዚአብሔር አይረሳህም ሰዎች የቱንም ያህል ክፉ ቢያደርጉብንም፣ በዘር በጎሳ ብከፋፍሉንም እግዚአብሔር ግን ሰውን በጭራሽ አይረሳም አንተንም አይረሳም ብዬ ነገርኩት።
=> ታዲያ በዚህ ወቅት ሌላ ነገር ደግሞ ተፈጠረ ጭራሽ ከሱ በሥራ ልምድ የምታንስና እንዲሁ የዛ ብሔር ተወላጅ ብቻ ስለሆነች የደረጃ ዕድገት ሰጥተው እሱ ስጠይቅ የነበረውን ቦታ ለሷ ይሰጣሉ። በዚህ ወቅት ወንድማችን ውስጡ ይረበሻል ብሆንም አሁንም አይዞህ እግዚአብሔር መቼም ብሆን አይጥለንም ላንተ እግዚአብሔር የተሻለውን እያዘጋጀ ይሆናል ብዬ አወራሁት። እሱም ተረጋጋና ለሎች የሥራ አማራጮችን መሞከር ጀመሬ። በዚው ወቅት ታዲያ የተለያዩ ቦታዎች ማመልከት ይጀምራል የሚገርመው ይሄ ሁሉ የሚሆነው ታዲያ በአጭረ ቀናትና ወራት ውስጥ ነው።
=> ታርኩን ሳጠቃልለው እግዚአብሔር ረድቶት ወንድማችን ሌላ ቦታ ለእንተርቪው (Interview) ይጠራል Interviewንም በድል እንደተወጣውና የቅጥር ፎርም መጥተህ እንድትሞላ የሚል የስልክ ጥሪ ይደርሰዋል በትላንትናው ዕለት። ይሄንን ስጽፍላችሁ ውስጠ በጣም ደስ ብሎታል ለወንድሜ እግዚአብሔር መልካሙን አደረገለት። ከዚህ የምንማረው ዛሬ በየመስሪያ ቤቱ በጣም ደስ የማይሉ አሳፋር ተግባሮች ይፈጸማሉ ብንዘረዝረው በጣም ብዙ ነው። ነገር ግን ክርስቲያን ሁለም ቢሆን ፈተና ስበዛበት ያፈተና ሌላ መልካም ነገሮችን ይዞ እንደሚመጣና ለተሻለ ነገር እያዘጋጀን እንደሆነ ማወቅ አለበት። አሁንም ወዳጄ እንኳን ደስ አለህ ብያለሁ። ለተቸገራችሁ ሁሉ እግዚአብሔር መንገዱን ይክፈትላችሁ ብርሃኑን ያብራላችሁ። መልካም ቀን ለሁላችሁ ይሁን።
=> በያላችሁበት በተለያየ መንገድ ፈተና የሚደርስባችሁ አይዟችሁ ታልፉታላችሁ! እግዚአብሔር ያሻግራችኋል፣ ብቻ ተስፋ አትቁረጡ በርቱ እንጂ። ዘወትር ንግግራችንና ውይይታችን ከእግዚአብሔር ጋር ይሁን።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
"Be ashamed when you sin, don't be ashamed when you repent [To repent means to have a change of heart and mind. It is not simply a feeling of sorrow, but a psycho/spiritual growth away from evil/death and a turning to God/life]. Sin is the wound, repentance is the medicine. Sin is followed by shame; repentance is followed by boldness [Boldness means to beg God for undeserved mercy]. Satan has overturned this order and given boldness to sin and shame to repentance."
-St. John Chrysostom
#መምህር_ተስፋዬና_ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ_የገለጡት_አስገራሚው_እውነት!! እያወቅን የሚንፈጽማቸውና ሳናውቅ የምንፈጽማቸው ኃጢአቶች!! #ethiopia #ጸሎት https://youtu.be/ARLt1ziXXYs
=> ሚስቶች ሆይ፥ ለጌታ እንደምትገዙ ለባሎቻችሁ ተገዙ፤ ክርስቶስ ደግሞ የቤተ ክርስቲያን ራስ እንደ ሆነ እርሱም አካሉን የሚያድን እንደ ሆነ ባል የሚስት ራስ ነውና። ዳሩ ግን ቤተ ክርስቲያን ለክርስቶስ እንደምትገዛ እንዲሁ ሚስቶች ደግሞ በሁሉ ለባሎቻቸው ይገዙ።
ባሎች ሆይ፥ ክርስቶስ ደግሞ ቤተ ክርስቲያንን እንደ ወደዳት ሚስቶቻችሁን ውደዱ፤ በውኃ መታጠብና ከቃሉ ጋር አንጽቶ እንዲቀድሳት ስለ እርስዋ ራሱን አሳልፎ ሰጠ፤ እድፈት ወይም የፊት መጨማደድ ወይም እንዲህ ያለ ነገር ሳይሆንባት ቅድስትና ያለ ነውር ትሆን ዘንድ ክብርት የሆነችን ቤተ ክርስቲያን ለራሱ እንዲያቀርብ ፈለገ።
=> እንዲሁም ባሎች ደግሞ እንደ ገዛ ሥጋቸው አድርገው የገዛ ሚስቶቻቸውን ሊወዱአቸው ይገባቸዋል። የገዛ ሚስቱን የሚወድ ራሱን ይወዳል፤ ማንም የገዛ ሥጋውን የሚጠላ ከቶ የለምና፥ ነገር ግን የአካሉ ብልቶች ስለሆንን፥ ክርስቶስ ደግሞ ለቤተ ክርስቲያን እንዳደረገላት፥ ይመግበዋል ይከባከበውማል።
=> ስለዚህ ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል ከሚስቱም ጋር ይተባበራል ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ። ይህ ምሥጢር ታላቅ ነው፥ እኔ ግን ይህን ስለ ክርስቶስና ስለ ቤተ ክርስቲያን እላለሁ። ሆኖም ከእናንተ ደግሞ እያንዳንዱ የገዛ ሚስቱን እንዲህ እንደ ራሱ አድርጎ ይውደዳት፥ ሚስቱም ባልዋን ትፍራ። (ኤፌ.5፡22-33)
«በትዳር ሕይወት ላላችሁ እግዚአብሔር ትዳራችሁን ይባርክላችሁ! ያላገባችሁም ደግሞ እንድታገቡ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ መንገዱን ይምራችሁ ያከናውንላችሁም። በዚህ ጉዳይ መወያየትና መነጋገር የምትፈልጉ ቤተሰቦች በውስጥመስመር አናግሩኝ በሀገር ውስጥም ይሁን ከሀገር ውጭም ያላችሁ ቤተሰቦቼ ነጻ ሆናችሁ አናግሩኝ እንደ እግዚአብሔር ፍቃድ እውነትና ትክክል የሆነውን ሁሉ እንነጋገራለን።» ለመወያየት በዚህ ጻፉልኝ https://t.me/haile_gebriel_tube_bot
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
ግንቦት ፲፬ /14/በዚች ቀን ከመንፈሳውያን ሐዋርያት ጋራ አንድነት ያለው የከበረ አባት ጳኩሚስ አረፈ። ይህም ቅዱስ ከአባ ጰላሞን ዘንድ መንኲሶ ሲያገለግለው የምንኵስናንም በጎ ሥራ እየሠራ ብዙ ዘመናት ኖረ። ከዚህም በኋላ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ተገልጾለት እንደ አባቶቻችን ሐዋርያት የአንድነትን ማኅበር ለመሥራት መነኰሳትን እንዲሰበስብ አዘዘው። ከዚህም በኋላ ብዙዎች ሰዎችን ሰብስቦ በየቦታው ብዙ ገዳማትን ሠራላቸው። ይህም አባት ስለዚህ ዓለም ከንቱ ውዳሴና በመካከላቸውም ጥል እንዳይኖር ይመክራቸው ነበር። ሊቀ ጳጳሳት ሐዋርያዊ አትናቴዎስ ወደ ላዕላይ ግብጽ በወጣ ጊዜ ይህን አባት ጳኩሚስን ቅስና ሊሾመው ወደደ። ከእርሱም ሸሸ። የከበረ አትናቴዎስም ልጆቹን የማይናወጽ ቤትን የሠራህ ሆይ ከከንቱ ውዳሴ የራቅህ አንተ ብፁዕ ነህ ልጆችህም ብፁዓን ናቸው ብሎሃል በሉት አባታችሁን አላቸው። አንድ ጊዜም ሲኦልን ያይ ዘንድ ወደደ እነሆ የእግዚአብሔር መልአክም ነጥቆ አውጥቶ በገነት የጻድቃንን ማደሪያ እንዲሁም በሲኦል የሥቃይን ቦታ አሳየው። ይህም አባት በአንድነት ማኅበር ላይ እያጽናናቸውና ሥርዓትንም እየሠራላቸው አበምኔት ሆኖ አርባ ዓመት ኖረ። ከዚህም በኋላ በእርሱ ፈንታ ደቀ መዝሙሩን ቴዎድሮስን ሹሞላቸው በሰላም አረፈ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239
«ሰው በጣም ተስፋ በቆረጠ ጊዜ ሁለም የእግዚአብሔርን ቸርነትና ምህረት ያስብ፤ እንዲሁ ደግሞ በጥሩ መንፈሳዊ ሕይወት ውስጥ በሆንን ጊዜ ደግሞ ዘወትር የእግዚአብሔርን ፈራጅነት እናስብ።»
«ዓለማዊ ትምህርት እና መንፈሳዊ ትምህርት»
(በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
=> ምድራዊያን ባለ ሥልጣናት በሚገባ ማገልገል ይችሉ ዘንድ ልጆቻቸውንን የዚህን ዓለም ሳይንሳዊ እውቀት ለማስተማር የማናፈሰው ሃብተ እና ጉልበት የለም፡፡ እኔ ግን እያልኩ ያለውት በእኛ ዘንድ እንደ ቂል ነገር የማይቆጠረውን ስለ ተቀደሰ ሃይማኖት ሊኖር የሚገባውን እውቀት እና የሰማያዊውን ንጉስ አገልግሎት በተመለከተ ነው፡፡ ትርኢቶችን እንዲመለከቱ እናደርጋቸዋለን፤ወደ ቤተክርስትያን ስለ መሄዳቸውና በዚያ በፈሪሃ እግዚአብሔር ስለ መቆማቸው ግን ብዙም ግድ አይሰጠንም፡፡ በምድራዊ የትምህርት ተቋሞቻቸው ውስጥ ምን እንደ ተማሩ እንጠይቃቸዋለን፤በእግዚአብሔር ቤት ስለ ሰሙት ነገርስ ለምን አንጠይቃቸውም?
=> ተገቢውን ምክርና ተግሳጽ ከተናገረ በኋላ ሐዋርያው አባቶችንም እንዲህ በማለት ይናገራቸዋል፡- “እናንተም አባቶች ሆይ፣ ልጆቻቸሁን በጌታ ምክርና በተግሳጽ አሳድጓቸው እንጂ አታስቆጧቸው” ልጅህ ታዛዥ እንዲሆን ትፈልጋለህን? እንዲህ እንዲሆንልህ ከፈለግህ ከመጀመርያው ጀምሮ በጌታ ምክርና ተግሳጽ አሳድገው፡፡ “ለልጅ ቅዱሳት መጻሕፍትን መስማትና መማር አስፈላጊ ነው? ብለህ አታስብ፤ ከቅዱሳን መጻሕፍት በመጀመሪያ የሚሰማው እናትና አባትህን አክብር የሚለውን ነው፡፡ በዚህም ወላጆችን የሚያከብር ስለሚሆን ዋጋህን ወዲያዉኑ መቀበል ትጀምራለህ፡፡
=> ቅዱሳት መጻሕፍትን መስማት ሲጀምር መጽሐፍ ቅዱስ ማንበብ ለመነኮሳት ነው፤ ልጄን መነኩሴ ላደርገው ነውን? አትበል፤ አይደለም መነኩሴ መሆን የግድ አያስፈልገውም፡፡ ክርስቲያን አድርገው፤ እንዲህ በጣም ጥሩ የሆነን ነገር ለምን ትፈራዋለህ እያንዳንዱ ሰው የመጽሐፍ ቅዱስን ትምህርት ያውቅ ዘንድ ያስፈልገዋል፤ ይህም ለሕፃናት የበለጠ እውነታነት ያለው ነገር ነው፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ የተገለጡ መለኮታዊ እውነታዎችን ካለማወቃቸው የተነሳ የመመለኪያ ጣኦትና አስደናቂ ታሪክ አላቸው የሚባሉ የዓለማውያን ሰዎችን ነገር ሲሰሙ አሳፋሪ ለሆኑ ሥጋዊ ፍላጎቶቻቸውና ፍትወታቸው የተገዙትንና ምኞቶቻቸውን ያገለገሉትን ሰዎች በእነርሱ ዘንድ እንደ ጀግኖች እና ታላላቅ ሰዎች አድርገው ያዩዋቸዋል፡፡ ስለዚህም አእምሮን ለሚያቆሽሹና ሕሊናን ለሚያበላሹ የተለያዩ ዓለማዊ ታሪኮችና መላምቶች የመርዝ ማርከሻ ይሆናቸው ዘንድ ልጆቻቸሁ የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ቃልና ትምህርት በእጅጉ ያስፈልጋቸዋል፡፡
=> ለልጆቻችን ትምህርት ተገቢውን ትኩረት ሰጥተናል የሚባለው በጌታችን ትምህርትና ተግሳጽ ለማሳደግ በእኩል ሁኔታ የምንተጋና የምንቀና ከሆነ ብቻ ነው፡፡ ልጆቻችን ስለ ሃይማኖት ነገር የማይገዳቸው ግዴለሽና ባለጌዎች ሆነው እንዲያድጉ እያደረግን እንዲህ አይነት መራራ ፍሬን እንዴት ልናጭድ እንደቻልን ለምን እንገረማለን፤ ይህ እንዳይደርስብንና እንዳይሆንብን ይልቁንም በጌታችን ተግሳጽና ትምህርት እንዲያድጉ ለማድረግ የቅዱስ ጳውሎስን ትምህርትና ተግሳጽ ሁልጊዜ ልብ እናድርግ፡፡ አርአያ የሚያደርጉትን እናሳያቸው ከመጀመርያው ዘመናቸው ጀምሮ መጽሐፍ ቅዱስን እንዲያጠኑ እናስተምራቸው ፡፡ እናንተ ይህን ነገር ብዙ ጊዜ ይደጋገምብናል፣ እኛም መስማት ሰለቸን ትሉ ይሆናል፡፡ እኔ ማድረግ ያለብኝ ተግባር ከማድረግ መቼም ቢሆን አላቆምም፡፡
ምንጭ፡- ቅዱስ ዮሐንስ አፈወቅር ስለ ልጅ አስተዳደግ ካስተማረዉ የተወሰደ
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
#የቤተክርስቲያን_ሴት_ስለሆነች_ብቻ_መልካም_ሴት_ናት_በጭራሽ_አትበል!! የምቀኛ መንፈስን ከእኛ ለማራቅ ይኼንን እናድርግ!! #hailegebrielreacts19 https://youtu.be/ofQ6Cf52Di8
«ዓለማዊ ትምህርት እና መንፈሳዊ ትምህርት»
(በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
=> ምድራዊያን ባለ ሥልጣናት በሚገባ ማገልገል ይችሉ ዘንድ ልጆቻቸውንን የዚህን ዓለም ሳይንሳዊ እውቀት ለማስተማር የማናፈሰው ሃብተ እና ጉልበት የለም፡፡ እኔ ግን እያልኩ ያለውት በእኛ ዘንድ እንደ ቂል ነገር የማይቆጠረውን ስለ ተቀደሰ ሃይማኖት ሊኖር የሚገባውን እውቀት እና የሰማያዊውን ንጉስ አገልግሎት በተመለከተ ነው፡፡ ትርኢቶችን እንዲመለከቱ እናደርጋቸዋለን፤ወደ ቤተክርስትያን ስለ መሄዳቸውና በዚያ በፈሪሃ እግዚአብሔር ስለ መቆማቸው ግን ብዙም ግድ አይሰጠንም፡፡ በምድራዊ የትምህርት ተቋሞቻቸው ውስጥ ምን እንደ ተማሩ እንጠይቃቸዋለን፤በእግዚአብሔር ቤት ስለ ሰሙት ነገርስ ለምን አንጠይቃቸውም?
=> ተገቢውን ምክርና ተግሳጽ ከተናገረ በኋላ ሐዋርያው አባቶችንም እንዲህ በማለት ይናገራቸዋል፡- “እናንተም አባቶች ሆይ፣ ልጆቻቸሁን በጌታ ምክርና በተግሳጽ አሳድጓቸው እንጂ አታስቆጧቸው” ልጅህ ታዛዥ እንዲሆን ትፈልጋለህን? እንዲህ እንዲሆንልህ ከፈለግህ ከመጀመርያው ጀምሮ በጌታ ምክርና ተግሳጽ አሳድገው፡፡ “ለልጅ ቅዱሳት መጻሕፍትን መስማትና መማር አስፈላጊ ነው? ብለህ አታስብ፤ ከቅዱሳን መጻሕፍት በመጀመሪያ የሚሰማው እናትና አባትህን አክብር የሚለውን ነው፡፡ በዚህም ወላጆችን የሚያከብር ስለሚሆን ዋጋህን ወዲያዉኑ መቀበል ትጀምራለህ፡፡
=> ቅዱሳት መጻሕፍትን መስማት ሲጀምር መጽሐፍ ቅዱስ ማንበብ ለመነኮሳት ነው፤ ልጄን መነኩሴ ላደርገው ነውን? አትበል፤ አይደለም መነኩሴ መሆን የግድ አያስፈልገውም፡፡ ክርስቲያን አድርገው፤ እንዲህ በጣም ጥሩ የሆነን ነገር ለምን ትፈራዋለህ እያንዳንዱ ሰው የመጽሐፍ ቅዱስን ትምህርት ያውቅ ዘንድ ያስፈልገዋል፤ ይህም ለሕፃናት የበለጠ እውነታነት ያለው ነገር ነው፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ የተገለጡ መለኮታዊ እውነታዎችን ካለማወቃቸው የተነሳ የመመለኪያ ጣኦትና አስደናቂ ታሪክ አላቸው የሚባሉ የዓለማውያን ሰዎችን ነገር ሲሰሙ አሳፋሪ ለሆኑ ሥጋዊ ፍላጎቶቻቸውና ፍትወታቸው የተገዙትንና ምኞቶቻቸውን ያገለገሉትን ሰዎች በእነርሱ ዘንድ እንደ ጀግኖች እና ታላላቅ ሰዎች አድርገው ያዩዋቸዋል፡፡ ስለዚህም አእምሮን ለሚያቆሽሹና ሕሊናን ለሚያበላሹ የተለያዩ ዓለማዊ ታሪኮችና መላምቶች የመርዝ ማርከሻ ይሆናቸው ዘንድ ልጆቻቸሁ የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ቃልና ትምህርት በእጅጉ ያስፈልጋቸዋል፡፡
=> ለልጆቻችን ትምህርት ተገቢውን ትኩረት ሰጥተናል የሚባለው በጌታችን ትምህርትና ተግሳጽ ለማሳደግ በእኩል ሁኔታ የምንተጋና የምንቀና ከሆነ ብቻ ነው፡፡ ልጆቻችን ስለ ሃይማኖት ነገር የማይገዳቸው ግዴለሽና ባለጌዎች ሆነው እንዲያድጉ እያደረግን እንዲህ አይነት መራራ ፍሬን እንዴት ልናጭድ እንደቻልን ለምን እንገረማለን፤ ይህ እንዳይደርስብንና እንዳይሆንብን ይልቁንም በጌታችን ተግሳጽና ትምህርት እንዲያድጉ ለማድረግ የቅዱስ ጳውሎስን ትምህርትና ተግሳጽ ሁልጊዜ ልብ እናድርግ፡፡ አርአያ የሚያደርጉትን እናሳያቸው ከመጀመርያው ዘመናቸው ጀምሮ መጽሐፍ ቅዱስን እንዲያጠኑ እናስተምራቸው ፡፡ እናንተ ይህን ነገር ብዙ ጊዜ ይደጋገምብናል፣ እኛም መስማት ሰለቸን ትሉ ይሆናል፡፡ እኔ ማድረግ ያለብኝ ተግባር ከማድረግ መቼም ቢሆን አላቆምም፡፡
ምንጭ፡- ቅዱስ ዮሐንስ አፈወቅር ስለ ልጅ አስተዳደግ ካስተማረዉ የተወሰደ
ግንቦት ፲፫ /13/በዚች ቀን የከበረ አባት በገድል ተጠምዶ የኖረ ብልህ አርሳንዮስ አረፈ። ይህም ቅዱስ ከሮሜ አገር ሰዎች ከባለጸጎችና ከታላላቆቿ ነው። የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት አስተምረው ዲቁናን አሾሙት። በመንፈሳዊ ትምህርቱም ፍጹም ሁኖ አምላካዊ ትሩፋትን የሚሠራ ሆነ። በሮሜ አገርም ታላቁ ቴዎዶስዮስ በነገሠ ጊዜ ልጆቹን አኖሬዎስንና አርቃዴዎስን የሚያስተምርለት ጥበበኛ ደግ ሰው ፈለገ። ይህንንም ቅዱስ ወደ ንጉሥ ወሰዱት። ንጉሡም ልጆቹን አኖሬዎስንና አርቃዴዎስን እንዲያስተምርለት አዘዘው እርሱም ታዝዞ የንጉሡን ልጆች እንደሚገባ ሊያስተምር ጀመረ። ንጉሥ ቴዎዶስዮስም በአረፈ ጊዜ ልጆቹ አኖሬዎስ በሮሜ አገር አርቃዴዎስም በቊስጥንጥንያ ነገሡ። እግዚአብሔርም ለአርሳንዮስ ከዚህ ዓለም ውጣ አንተም ትድናለህ አለው። ይህንንም ቃል በሰማ ጊዜ ፈጥኖ ተነሣ እንጂ አልዘገየም ወዲያውኑ ልብሱን ለውጦ ወደ እስክንድርያ አገር ሔደ። ከዚያም የከበረ የአባ መቃርስ ገዳም ወደ አለበት ወደ አስቄጥስ በረሀ ደርሶ በጾም በጸሎት በመስገድ በመትጋት በአርምሞና በትሩፋት ሁሉ ፍጹም ተጋድሎን ተጋደለ። ይህም አባት ድንቆች ተአምራትን ያደርጋል የብዙዎች ሰዎችን ገድል እግዚአብሔር ገልጦለታልና። እድሜው በሙሉ መቶ አመት ሆነ። በሮሜም አርባ ዓመት ኖረ። በአስቄጥስ ገዳም ሠላሳ አምስት በምስር ገዳም ሃያ ዓመት በእስክንድርያ ሦስት ዓመት ከዚህም በኋላ ወደ ምስር ገዳም ተመልሶ በዚያ ሁለት ዓመት ተቀምጦ በሰላም አረፈ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239
#አምልኮ_የሚፈጸምለት_ዕጣንና_ስንደል_የሚጨስለት_የመቃብር_ሥፍራ_በአዲስ_አበባ!! አስከፊው የከልከልዮስ የመቃብር መንፈስና ሴራው ሲገለጥ!! #በማለዳ_ንቁ!! https://youtu.be/GxdIbcNy1ZI
+3
እንኳን አደረሳችሁ [ ግንቦት ፲፪/12 ]
√ ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት
√ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ (ከ344-404 ዓ.ም)
√ ብፅዕት ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ
√ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት (ፍልሰተ ሥጋሁ ወዐጽሙ) እና ሌሎችም.... የቅዱሳን በረከታቸው ይድረሰን።
የቅዱሳን አባቶቻችን እና እናቶቻችን ጸሎታቸው፥ ምልጃቸው፣ ረድኤታቸው፣ ጸጋና በረከታቸው አይለየን። አሜን።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
#ይኼ_ድራማ_ይዞብን_የመጣውን_ጉድ_ደግሞ_ተመልከቱልኝማ!! በድራማዎቻችን ውስጥ ያደፈጠው የአጋንንት ሴራ ሲገለጥ!! Haile Gebriel Reacts19 #ድራማ https://youtu.be/7OkmdgxTmcU
«የስውሯ ማሪያም ምስክርነት»
«ምስክርነት ለእናቴ ስውሯ ማርያም ያደረገችልኝ ብዙ ነው ማንም በሌለኝ ሰዓት ረዳችኝ ፊቴ ሙሉ ሰውነቴ ቆሳስሎ በዙሪያዬ የነበሩት ጓደኞቼ ሁሉ እርቀውኝ ቀንም ለሊትም ነበር ማለቅስ ትምህርቴን 12ኛ ክፍል ጨርሼ መማር አልቻልኩም እናቴም እኔን ማስተማር አቅም አልነበራትም ሳለቅስ አብራኝ ሁና ከማልቀስ ውጪ በቃ አብጄ የምሄድ ነበር የሚመስላት በቃ ብዙ ነበር ህመሜ አንድ ቀን ለሊት FB ገብቼ ሳይ ስለ ስውሯ ማርያም አየሁ ስዕል አድኗን አውርጄ ለኔም ድረሽልኝ እያልኩ ሰቅስቅ ብዬ እያለቀስኩ ለመንኳት ፀበል አምጥቼ እናቴ በቃሽ በይኝ እያልኩ እጠጣለሁ እቀባዋለሁ ስውሯ ማርያም እናቴ አላሳፈረችኝም ታሪኬን ቀይረችው የእናቴንም የኔንም እንባ አበሰችልን። ያ ሁሉ ቁስል ለምፅ እንኳን ሳይኖር ደርቆ ስራም ተወዳድሬ ተቀጠርኩ የቀን እየሰራሁ ትምህርቴን የማታ እየተማርኩ አሁን ከ1 ወር በኋላ እመረቃለሁ እልልልልል ብላችሁ አመስግኑልኝ 🙏 እኔን የሰማችኝ እናተንም ፀሎት ትስማችሁ🙏🙏 አይ የኔ ፍላጎት እኮ አያልቅም ለእናቴ ማደረግ ያለብኝ ነገር አለ ስውሯ ማርያም እናቴ የለመንኳትን እድታሳካልኝ በፀሎታችሁ አሰቡኝ🙏»
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
