HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
Kanalga Telegram’da o‘tish
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
Ko'proq ko'rsatish2 276
Obunachilar
+324 soatlar
+137 kunlar
+3830 kunlar
Postlar arxiv
=> ታላቁ ቅዱስ እንጦንዮስ፦ ሰዎች የሚያብዱበት ዘመን ይመጣል፤ አንተ እንደነሱ ካልሆንክ ‘አብዷል’ ይሉሃል። ከሰው ማበረታቻን አትፈልግ—እግዚአብሔርን ፈልግ።
=> "ራስን በሚያከብሩ ከንቱ ቃላት ልብህ ከፍ አይበል። ሰይጣን የወደቀው በጥላቻ ሳይሆን በራሱ ኩራት ነውና።"
=> ቅዱስ ፓይሲዮስ ዘአቶስ፦ “ዮጋ መንፈሳዊ መርዝ ነው... ስፖርት ሳይሆን መንፈሳዊ ክህደት ነው። የሰውን ማንነት የሚያሳብጡ ዘመናዊ ንግግሮችም እንዲሁ አደገኛ ናቸው።”
=> ቅዱስ ፖርፊሪዮስ፦ “የሰው ቃላት ሰላም ሊሰጡ አይችሉም። ሰላም የሚሰጠው ክርስቶስ ብቻ ነው፤ ቃላቱም መለኮታዊ ስለሆኑ ኃይል አላቸው።”
ሰኔ ፳፬ /24/በዚች ቀን አባ ሙሴ ጸሊም በሰማዕትነት ሞተ። ሰዎች ከገድሉ የተነሣ ይህን ቅዱስ ያደንቁታል እርሱ አስቀድሞ መንግሥተ ሰማያትን ገፍቷት ነበረና እርሱ በሥጋው ጠንካራ በሥራውም ኃይለኛ ነበር ይበላና ይጠጣ ይቀማና ያመነዝር ነበር ይገድልም ነበር። እርሱም ፀሐይን ለሚያመልኩ ሰዎች አገልጋይ ነበረ ብዙ ጊዜም ወደ ፀሐይ እያንጋጠጠ ፀሐይ ሆይ አንተ አምላክ ከሆንክ አነጋግረኝ ይል ነበር ደግሞም በልቡ የማላውቅህ ሆይ ራስህን አሳውቀኝ ይል ነበር። ከዚህም በኋላ በአስቄጥስ ገዳም ያሉ መነኰሳት እግዚአብሔርን ያዩታልም እያሉ ሲነጋገሩ ሰምቶ ወደ አስቄጥስ ገዳም ሔደ። በዚያም አባመቃርስ ተቀብሎ ሃይማኖትን አስተማረውና አጥምቆ አመነኮሰው እንዲህም አለው ታግሠህ የማስተምርህን ከጠበቅህ እግዚአብሔርን ታየዋለህ። ከዚህም በኋላ ብዙ ተጋደለ።በአንዲትም ዕለት አባ ሙሴ ከአረጋውያን ጋራ ወደ አባ መቃርስ ሔደ አባ መቃርስም ከመካከላቸው አንዱ ሰማዕት እንደሚሆን ነገራቸው አባ ሙሴም ምናልባት እኔ እሆናለሁ በሰይፍ የገደለ በሰይፍ ይገደል ዘንድ አለው የሚል ጽሑፍ አለና ብሎ መለሰ። ወዲያውም የበርበር ሰዎች መጡ። ከዚህም በኋላ አባ ሙሴም ከእርሱ ጋራ ያሉትን መነኰሳት ሽሹ አላቸው አንተስ ሲሉት በሰይፍ የገደለ በሰይፍ ይገደላል እነሆ ያቺን ቀን ስጠብቃት ነበር አላቸው። ወዲያውኑም የበርበር ሰዎች ገብተው በሰይፍ ገደሉት መሸሽ ስለ አልፈለጉ ከእርሱ ጋራ ሰባት መነኰሳትም ተገደሉ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239
ወጣ ገባ እያሉ የሚያስቸግሩንን መናፍስቶች ለመቆጣጠር ይኼንን እናድርግ!! ውስጣችን ያደፈጠን መንፈስ እንዲጋለጥ ለማድረግ ይኼን አስተውሉ! ብጹዕ አቡነ ጴጥሮስ https://youtu.be/rQYvb_mT0V4
» አባ ጲሜን እንዲህ አለ፦ "በጸሎት ጊዜ ሰይጣን መቶ ኃጢአቶችህን ቢያስታውስህ፣ አንተ ደግሞ ክርስቶስን መቶ አንድ ጊዜ አስበው።"
» ቅዱስ ቴዎፋን ገዳማዊው፦ "በጸሎት ጊዜ የሚመጣ ውስዋሴና ፈተና፣ ቅጥሯ እንደገና በሚገነባበት ወቅት ጠላት ከተማን እንደሚያጠቃው ነው። ይህም ነፍስህ እየተጠናከረች መምጣቷን ያሳያል። ጠላት የሚገባው በዝንጋኤ ነው። አእምሮህ ሲባዝን፣ ቀስ ብለህ ሰብስበህ ወደ ጸሎትህ ተመለስ፤ ይህ ራሱ የመንፈሳዊ ጥንካሬ ጅማሬ ነው።"
» ቅዱስ ኤቫግሪየስ:- "አእምሮ በተፈጥሮው ወደ እግዚአብሔር ይሳባል፤ አጋንንት ግን ልክ ጣፋጭ መዓዛን እንደሚከቡ ዝንቦች፣ ትዝታዎችንና ውስዋሴዎችን ይጠቀማሉ።"
» ታላቁ ቅዱስ እንጦንዮስ፦ "ጸሎት ስትጀምር ለፈተና ተዘጋጅ። ከትህትና ጋር የተባበረ ጸሎት ግን አጋንንትን ያቃጥላል።"
» ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፦ "ሰይጣን በጸሎት ሰዓት በአእምሮህ ላይ የተለያዩ ሐሳቦችን ለመዝራት ከጎንህ ይቆማል፤ አንተ ግን በትህትና ከጸናህ አፍሮ ይሸሻል።"
«በትህትናና በፍቅር ስንጸልይ እግዚአብሔር በታላቅ ኃይል ይሠራል፤ አጋንንት እንኳን ይሸሻሉ። ይህም በእኛ ምክንያት ሳይሆን በእኛ ውስጥ ባለው በክርስቶስ ምክንያት ነው።»
«When we pray with humility and love, God works with great power; even demons flee. And this is not because of us, but because of Christ who dwells in us.» ቅዱስ ፓይሲዮስ አቶሳዊው
የቅድስት ቤተክርስቲያን ሀዘኗ የሚያበቃው መቼ ይሆን! ጌታ ሆይ እባክህን ይቅር በለን በእውነት! በሮቤ ወረዳ የገደብሳ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ካህን በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደሉ፡፡
በምሥራቅ አርሲ ሮቤ ወረዳ ቤተ ክህነት የገደብሳ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ የሆኑት ካህን ቀሲስ ተስፋዬ ረታ ሰኔ 21 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 1፡30 አካባቢ በታጣቂ ኃይሎች በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸው ተገልጿል።
ለማኅበረ ቅዱሳን ሚዲያ በደረሰን መረጃ ባለቤታቸው በተመሳሳይ ሁኔታ መገደላቸው የተገለጸ ሲሆን አካባቢው ካህኑ የተወለዱበት እና ከዲቁና ጀምሮ በአሁኑ ወቅትም በቤተ ክርስቲያኑ በቅስና ማእረግ እያገለገሉ ነበር ተብሏል፡፡
የካህኑ የቀብር ሥነ ሥርዓት በትናንትናው ዕለት ሰኔ 22 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 5፡00 ሰዓት በሮቤ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን መፈጸሙን የደረሰን መረጃ ያመላክታል፡፡
በአሁኑ ሰዓት በወረዳው እየተባባሰ የሚገኘውን አፈና እና ግድያን በመፍራት እና በመስጋት በአካባቢው የሚኖሩ ምእመናን ከተማውን ለቀው እየተሰደዱ መሆኑ ታውቋል፡፡
MKTV እንደዘገበው! ቀሲስ ተስፋዬ ረታ የሰባት ልጆች አባት ሲሆኑ ልጆቻቸውም ምንም አይነት ሥራ መሥራት የማይችሉ እና ሕጻናት በመሆናቸው ለመጠለያ ይሆናቸው ዘንድ የወረዳው አስተዳደር 200 ካሬ ሜትር መስጠቱን የተናገሩት መረጃ ሰጪያችን የሚመለከታቸው አካላት በሙሉ በጋራ ሆነው አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ሲሉ ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡
ጣቢያችን ጉዳዩ ከተከሰተበት ሰዓት አንስቶ ስለጉዳዩ ተጨማሪ መረጃዎችን ለመሰብሰብ የወረዳው የፀጥታ ኃይል ኀላፊን ለማግኘት በተደጋጋሚ በእጅ ስልካቸው ላይ ብንደውልም መልስ ማግኘት ሳንችል ቀርተናል፡፡
ዩትዩብ:- https://www.youtube.com/@haileG2239
በመልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ እና በቀሲስ ሄኖክ ወ/ማርያም!
#_በካናዳ_በካልጋሪ_ከተማ!
ሸር በማድረግ መልእክቱን አዳርሱ!
ተወዳጆች ሆይ በ July 11, 12, እና 13 አርብ ቅዳሜ እና እሑዱ በቶሮንቶ ያለኝን ጉባኤ ካበቃሁ በኋላ፤ ለሁለት ሳምንታት July 18, 19, እና 20 አርብ ቅዳሜ እና እሑድ፤ እንዲሁም በሳምንቱ July 25, 26, 27, አርብ ቅዳሜ እና እሑዱ ከመልአከ መንክራት መምህር ግርማ ወንዱሙ ጋር በአንድ ላይ ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ ይኖረናል።
በተለይ ውጭ ሀገር ያላችሁ እሳቸው እና እኔን በአንድ ላይ እንድናገለግላችሁ ጉጉት እና ፍላጎት ያላችሁ ብዙዎች ናችሁ። የእኛም የእናንተም ሐሳብ በእግዚአብሔር ቸርነት፣ በድንግል ማርያም ጸሎት ተሳክቶ፣ በአንድ ላይ ልናገለግላችሁ ዝግጁ ነን።
ወለላይቱ እመቤት እቅፍ ድግፍ አድራጋ በሰላም ሁላችንንም በእለተ ቀኑ ታገናኘን!
"ሥራቸውም አንድ ስለነበር .. በአንድ ላይ ሠሩ" የሐዋ. ሥራ 18፥3
ሴኔ 23-10-17 ዓ.ም
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
ባሎች እንዲህ ይበል፦ «በክንዶቼ ተቀብዬሻለሁ፤ እወድሻለሁም፤ ከራሴ ሕይወት ይልቅ አንቺን አስበልጥሻለሁ። ይህ ያለው ሕይወት አላፊና ከንቱ ነውና፥ ከሁሉ በላይ የጋለ ምኞቴ ዳግም እንደማንለያይ ርግጠኞች ሆነን ያንን ዘላለማዊ ሕይወት ከአንቺ ጋር ማሳለፍ ነው።» — ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
“Let the husband say, ‘I have taken you in my arms, and I love you, and I prefer you to my life itself. For the present life is nothing, and my most fervent desire is to spend eternity with you in such a way that we may be assured of never being separated.’” — St. John Chrysostom
«የዕለቱን ወንጌል እናንብብ! ሰኔ 23»
+++ ከመጥምቁም ከዮሐንስ ዘመን ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ መንግሥተ ሰማያት ትገፋለች፥ ግፈኞችም ይናጠቋታል። ነቢያት ሁሉና ሕጉ እስከ ዮሐንስ ድረስ ትንቢት ተናገሩ፤ ልትቀበሉትስ ብትወዱ፥ ይመጣ ዘንድ ያለው ኤልያስ ይህ ነው። የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ። ነገር ግን ይህን ትውልድ በምን እመስለዋለሁ? በገበያ የሚቀመጡትን ልጆች ይመስላሉ፥ እነርሱም ባልንጀሮቻቸውን እየጠሩ። እንቢልታ ነፋንላችሁ ዘፈንም አልዘፈናችሁም ሙሾ አወጣንላችሁ ዋይ ዋይም አላላችሁም ይሉአቸዋል። ዮሐንስ ሳይበላና ሳይጠጣ መጣ፥ እነርሱም። ጋኔን አለበት አሉት። የሰው ልጅ እየበላና እየጠጣ መጣ፥ እነርሱም። እነሆ፥ በላተኛና የወይን ጠጅ ጠጭ፥ የቀራጮችና የኃጢአተኞች ወዳጅ ይሉታል። ጥበብም በልጆችዋ ጸደቀች። በዚያን ጊዜ የሚበዙ ተአምራት የተደረገባቸውን ከተማዎች ንስሐ ስላልገቡ ሊነቅፋቸው ጀመረ እንዲህም አለ። ወዮልሽ ኮራዚ፤ ወዮልሽ ቤተ ሳይዳ፤ በእናንተ የተደረገው ተአምራት በጢሮስና በሲዶና ተደርጎ ቢሆን፥ ማቅ ለብሰው አመድም ነስንሰው ከብዙ ጊዜ በፊት ንስሐ በገቡ ነበርና። ነገር ግን እላችኋለሁ፥ በፍርድ ቀን ከእናንተ ይልቅ ለጢሮስና ለሲዶና ይቀልላቸዋል። አንቺም ቅፍርናሆም፥ እስከ ሰማይ ከፍ አልሽን? ወደ ሲኦል ትወርጃለሽ፤ በአንቺ የተደረገው ተአምራት በሰዶም ተደርጎ ቢሆን፥ እስከ ዛሬ በኖረች ነበርና። ነገር ግን እላችኋለሁ፥ በፍርድ ቀን ከአንቺ ይልቅ ለሰዶም አገር ይቀልላታል። በዚያን ጊዜ ኢየሱስ መልሶ እንዲህ አለ። አባት ሆይ፥ የሰማይና የምድር ጌታ፥ ይህን ከጥበበኞችና ከአስተዋዮች ሰውረህ ለሕፃናት ስለ ገለጥህላቸው አመሰግንሃለሁ፤ አዎን፥ አባት ሆይ፥ ፈቃድህ በፊትህ እንዲህ ሆኖአልና። ሁሉ ከአባቴ ዘንድ ተሰጥቶኛል፤ ከአብ በቀር ወልድን የሚያውቅ የለም፥ ከወልድም በቀር ወልድም ሊገለጥለት ከሚፈቅድ በቀር አብን የሚያውቅ የለም። እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ። ቀንበሬን በላያችሁ ተሸከሙ ከእኔም ተማሩ፥ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤ ቀንበሬ ልዝብ ሸክሜም ቀሊል ነውና።
«የማቴዎስ ወንጌል 11፡12-30»
ሰኔ ፳፫ /23/በዚች ቀን በእስራኤል ሁሉ ላይ የነገሠ የዳዊት ልጅ የሰሎሞን የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው። የዚህ የሰሎሞንም የእናቱ ስም ቤርሳቤህ ነው ዳዊትም ሕግ ተላልፎ ከእሷ ጋራ ስለ መበደሉ ባሏንም ስለ ማስገደሉ ጌታ በገሠጸው ጊዜ ንስሓ ገብቶ መሪር ልቅሶን አለቀሰ ጌታም ንጹሕ ስለሆነ ንስሓው ይቅር አለው ። ከዚህም በኋላ በእግዚአብሔር ፈቃድ እርሷን አገባትና ሰሎሞንን ወለደችው ንጉሥ ዳዊትም ከእርሱ በኋላ ልጅዋ ሰሎሞን እንዲነግሥና በዙፋኑ ላይ እንዲቀመጥ ቃል ገባላት። ከብዙ ጊዜ በኋላ በእግዚአብሔር ፊት እንደማልኩልሽ አሁንም በዚች ቀን እንደዚሁ እንዳደርግ ሰውነቴን ከመከራዬ ሁሉ ያዳናት የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ሕያው ነው ብሎ ማለ ። ቤርሳቤህም አንገቷን ደፍታ በግምባርዋ በመሬት ወድቃ ለንጉሡ ሰገደች ጌታዬ ንጉሥ ዳዊት ለዘላለም ኑር አለች። ካህኑ ሳዶቅንና ነቢዩ ናታንንም ጠርቶ ሰለሞንን እንዲያነግሱ አዘዛቸውና አነገሱት። እግዚአብሔር ለሰለሞን ጥበብን ሰጠው። በንግስና ጊዜውም የእግዚአብሔርን ቤተመቅደስ ሰራ። ሰሎሞንም አርባ ዘመን ነገሠ ከመንገሡም በፊት ዐሥራ ሁለት ዓመት ኖረ መላ ዕድሜውም ሃምሳ ሁለት ዓመት ነበር። በመጨረሻም በሰላም አረፈ። ይህም ጥበብ የተሰጠው ንጉሥ ሰሎሞን ጥቅም ያላቸው ብዙዎች መጻሕፍትን ደርሶአል ። እሊህም ትንቢትና ትምህርት ያለባቸው ምሳሌዎችና መኃልዮች ናቸው። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን ጸሎት ይማረን ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239
ሰይጣን በጭራሽ እንድታውቁት የማይፈልገው ነገር!! ጠላታችን ሰይጣን እንዳትደርሱባቸው የሚፈራቸው ምሥጢራት!! ጸሎት በአጋንንት ውጊያ ወቅት #ጸሎት #መዝሙር
https://youtu.be/1EsqB30YQJ0?si=UZMMoC0d62GCutOx
🙏 ካናዳ ያላችሁ ተዘጋጅታችኋል! ላልሰሙት አሰሙ በካናዳና በአቅራቢያው ለሚገኑ በሰሜን አሜሪካን በካናዳ ካል ጋር የተዘጋጀ መንፈሳዊ አገልግሎት!
የመልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ አገልግሎት በምዕራብ በካናዳ ሃገረ ስብከት በካልጋሪ መካነ ሰላም መድኃኒአለም ቤተ ክርስቲያን ከ (July ,18 19 20, 2025 ወይም ሐምሌ 2017.ዓ.ም መርሐ ግብሩ ይጀመራል ወንጌል ሁል ጊዜ አዲስ ነውና ላልሰሙት አሰሙ ትውልድ ይዳን ለበለጠ መረጃ ይደውሉ +4033544410, +15872279769, +14036040477
ሸር ያድርጉ ለሁሉም እንዲደርስ!
እግዚአብሔር ታላቅ ነገር ሊሰጠን ሲል እነዚህን ምልክቶች ታያላችሁ! ልታውቁትና ልትጠነቀቁት የሚገቡ ነገሮች! https://youtu.be/tXTs8Nl5YD0?si=8FBJKi6xFQ4h5A4j
በስህተት የተወረወረ መተት በገዛ ልጆቿ ላይ ያስከተለውን ጣጣ ተመልከቱ!! ሳይገባን ጸበል ለጸበል የምንዞር ሰዎች ይኼንን አዳምጡ!! #ethiopia #ጸሎት https://youtu.be/AWluwcHUS1Q
የዕለቱን ወንጌል እናንብብ! ሰኔ 21
+++ ኢየሱስም ወደ ፊልጶስ ቂሣርያ አገር በደረሰ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን። ሰዎች የሰውን ልጅ ማን እንደ ሆነ ይሉታል? ብሎ ጠየቀ። እነርሱም። አንዳንዱ መጥምቁ ዮሐንስ፥ ሌሎችም ኤልያስ፥ ሌሎችም ኤርምያስ ወይም ከነቢያት አንዱ ነው ይላሉ አሉት። እርሱም። እናንተስ እኔን ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? አላቸው። ስምዖን ጴጥሮስም መልሶ። አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ አለ። ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው። የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ በሰማያት ያለው አባቴ እንጂ ሥጋና ደም ይህን አልገለጠልህምና ብፁዕ ነህ። እኔም እልሃለሁ፥ አንተ ጴጥሮስ ነህ፥ በዚችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ፥ የገሃነም ደጆችም አይችሉአትም። የመንግሥተ ሰማያትንም መክፈቻዎች እሰጥሃለሁ፤ በምድር የምታስረው ሁሉ በሰማያት የታሰረ ይሆናል፥ በምድርም የምትፈታው ሁሉ በሰማያት የተፈታ ይሆናል። ያን ጊዜም እርሱ ክርስቶስ እንደ ሆነ ለማንም እንዳይነግሩ ደቀ መዛሙርቱን አዘዛቸው።
(የማቴዎስ ወንጌል 16፡13-20)
«ምእመናን በቤታቸው የተባረከ ዘይት ይኑራቸው። ይህንንም ሲጠቀሙ እንደ አስማት ወይም ድግምት ሳይሆን፣ በእምነትና በጸሎት ይሁን። ጸጋው በራሱ በዘይቱ ውስጥ ሳይሆን፣ የምእመናንን ጸሎት በሚሰማው በእግዚአብሔር ኃይል ውስጥ ነውና። ይኼም ማለት ማንኛውም ምእመን በሕመም ወይም በመንፈሳዊ ተጋድሎ ጊዜ የእግዚአብሔርን ምሕረት እየጠራ ራሱን ወይም የሚወዷቸውን ሰዎች መቀባት ይችላል።»
«Let the faithful keep blessed oil at home. Use it with faith, and not as a magic charm, but with prayer. For the grace is not in the oil itself, but in the power of God who hears the faithful. This means Any believer can anoint themselves or loved ones in times of sickness or spiritual struggle, invoking God's mercy.»
(አባታችን ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
=> ቅዱስ ፓይስዮስ እንዲህ ብሏል፡- “ትንሽ ያልተፈታ ግጭት እንኳን አጋንንት ትዳርን እንዲያፈርሱ ቦታ ሊሰጣቸው ይችላል። ሁልጊዜ ከመተኛታችሁ በፊት ታረቁ።”
=> እርስ በርሳችሁ እንዲህ ተባባሉ፡- “በቃል፣ በሐሳብ፣ ወይም በድርጊት ዛሬ አንተን/አንቺን አስከፍቼህ/ሽ እንደሆነ ይቅር በለኝ/በይኝ።”
ሰኔ ፳፩ /21/በዚች ቀን ከምስር አገር ቅዱስ ጢሞቴዎስ በሰማዕትነት ሞተ። ይህም ቅዱስ አስቀድሞ ከእንዴናው ገዥ ከአርያኖስ ጭፍራዎች ውስጥ ነበር ሰው ሁሉ ጣዖታትን እንዲያመልክ የሚያዝ የዲዮቅልጥያኖስ የመልእክት ደብዳቤ በተነበበ ጊዜ ይህ ቅዱስ ከሕዝቡ መካከል ተነሥቶ የንጉሡን ደብዳቤ ወስዶ ከሕያው እግዚአብሔር ልጅ ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ሌላ አምላክ የለም ብሎ የከሀዲውን ንጉሥ የመልእክት ደብዳቤ ቀደደ። መኰንኑም ድፍረቱን አይቶ ጽኑ ስቃይን አሰቃየው እርሱም የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ርዳኝ እያለ ይጮኽ ነበር። ጌታችንም ትዕግሥቱን አይቶ መልአኩን ልኮ ከሥቃዩ አድኖ ጤነኛ አደረገው ወደ መኰንኑም ቀርቦ ከሕያው እግዚአብሔር ልጅ ከአንዱ ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ሌላ አምላክ የለምና አንተ ከሀዲ እፈር አለው። ያን ጊዜም ይዞ ጽኑ ሥቃይን አሠቃየው በመጋዝም መግዞ ሰቀለው ከዚያም በኋላ ሥጋው እንደ ሰም ቀልጦ እንደ ውኃ እስቲፈስ በብረት ምጣድ ውስጥ አበሰለው ከከተማ ውጪም ጣሉት። ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ያለምንም ጉዳት አንሥቶ ጤነኛ አደረገው። ወደ መኰንኑም ተመልሶ ከሕያው እግዚአብሔር ልጅ ከጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በቀርሌላ አምላክ የለምና አንተ ከሀዲ እፈር ብሎ ጮኸ። ይህንንም ድንቅ ተአምር አይተው ቁጥር የሌላቸው ብዙ አሕዛብ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አምነው በሰማዕትነት ሞቱ። መኰንኑም ማሠቃየቱ በሰለቸው ጊዜ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ። የድል አድራጊነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239
ዛሬው ዕለት የሰኔ ጎሎጎታን ጸሎት ሳትጸልዩ በጭራሽ እንዳትውሉ! የሰኔ ጎሎጎታ ጸሎት በረከቶች! ሰኔ 21 ለምን ይከበራል? #hailegebrielreacts19 https://youtu.be/2a2Q8N6FkxY
በዛሬው ዕለት የሰኔ ጎሎጎታን ጸሎት ሳትጸልዩ በጭራሽ እንዳትውሉ! የሰኔ ጎሎጎታ ጸሎት በረከቶች! ሰኔ 21 ለምን ይከበራል? #hailegebrielreacts19 https://youtu.be/2a2Q8N6FkxY
